በአውሮፓ ቤልጅየም በተደረገላቸው ግብዣ መሰረት በኢትዮጵያ ጉዳይ ውይይት አድርገው ሲአመለሱ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ታስረው የነበሩት ዶ።ር መረራ ጉዲና ከእስር ተለቀዋል። ዶ/ር መረራ የኦፌኮ /መድረክ ሊቀመንበር ሲሆኑ፤ በአቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ እንዳለ ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጎ ጥር 9 ቀን 2010 ዓ ም ከእስር ተለቀዋል።
ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር ሲለቀቁ በአምቦ የተደረገላቸው ህዝባዊ አቀባበል ላይ
ዶ/ር መረራ ከእስር ሲለቀቁ በርካታ ቤተሰቦቻቸው፥ የትግል አጋሮቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ደማቅ አቀባበል ያደርጉላቸው ሲሆን፤ በተለይም በቡራዩ መኖሪያ ቤታቸው፥ እና በትውልድ አካባቢያቸው አምቦ በርካታ ህዝብ በተገኘበት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር ሲለቀቁ በአምቦ የተደረገላቸው ህዝባዊ አቀባበል ላይ
ከዶ/ር መረራ ፥ የወለጋ ዩኒቨርስቲ መምህር ሩፋኤል ዲሳሳን ጨምሮ በደቡብ ክልል ኮንሶ እና ጌዲዮ ዞን የታሰሩ በርካታ የፖለቲካ እስረኞች መለቀቃችው ታውቋል።
ቀደም ሲል መንግሥት በተለይ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል እየተደረገ ያለውን ህዝባዊ አመፅና ጫና ተከትሎ የፖለቲካ እስረኞችን እንደሚፈታ ቃል መግባቱ ይታወሳል።