ዶ/ር መረራ ጊዱናን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ተፈቱ

በአውሮፓ ቤልጅየም በተደረገላቸው ግብዣ መሰረት በኢትዮጵያ ጉዳይ ውይይት አድርገው ሲአመለሱ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ታስረው የነበሩት ዶ።ር መረራ ጉዲና ከእስር ተለቀዋል። ዶ/ር መረራ የኦፌኮ /መድረክ ሊቀመንበር ሲሆኑ፤ በአቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ እንዳለ ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጎ ጥር 9 ቀን 2010 ዓ ም ከእስር ተለቀዋል።
Dr. Merera _Ambo .jpg
ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር ሲለቀቁ በአምቦ የተደረገላቸው ህዝባዊ አቀባበል ላይ

ዶ/ር መረራ ከእስር ሲለቀቁ በርካታ ቤተሰቦቻቸው፥ የትግል አጋሮቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ደማቅ አቀባበል ያደርጉላቸው ሲሆን፤ በተለይም በቡራዩ መኖሪያ ቤታቸው፥ እና በትውልድ አካባቢያቸው አምቦ በርካታ ህዝብ በተገኘበት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

Dr. Merera _Ambo 1
ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር ሲለቀቁ በአምቦ የተደረገላቸው ህዝባዊ አቀባበል ላይ

ከዶ/ር መረራ ፥ የወለጋ ዩኒቨርስቲ መምህር ሩፋኤል ዲሳሳን ጨምሮ በደቡብ ክልል ኮንሶ እና ጌዲዮ ዞን የታሰሩ በርካታ የፖለቲካ እስረኞች መለቀቃችው ታውቋል።

ቀደም ሲል መንግሥት በተለይ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል እየተደረገ ያለውን ህዝባዊ አመፅና ጫና ተከትሎ የፖለቲካ እስረኞችን እንደሚፈታ ቃል መግባቱ ይታወሳል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: