በኢትዮጵያ ለቀጥይ 6 ወራት የሚቆይ አስቸኳይ አዋጅ ታወጀ

(ዳጉ ሚዲያ) መንግሥት የፖለቲካ እስረኞች የነበሩት ጋዜጠኞችን፥ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን እና የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎችን መፈታት እና የጥቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን ተከትሎ፤ ከትናንት የካቲት 9 ቀን 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ተግባራዊ የተደረና በሚኒስትሮች ምክር ቤት እንደፀደቀ የተነገረለት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጁን ገዥው መንግሥት አስታውቋል።

Siraje Fegessa_State of emergency
የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ

አዋጁም ለቀጣዮቹ 6 ወራት የጸና መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳ ዛሬ የካቲት 10 ቀን 2010 ዓ.ም. በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል። አዋጁም እንደ አስፈላጊነቱ ታይቶ ለተጨማሪ 4 ወራት ሊራዘም እንደሚችልም ተገልጿል።

የአስቸኳይ አዋጁ የመሰብሰብ፥ የመደራጀት፥ መረጃዎችን የመለዋወጥ፥ የመፃፍ፥ የተለያዩ ምልክቶችን ማሳየት፥ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ብርበራ፥ ፍተሻ እና የመሳሰሉ መብቶችን የገደበ መሆኑን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። እንደ እዋጁ ከሆነ፤ የጊዜ ገደብን ጨምሮ መንግሥት የመገናኛ ብዙኃንን ከማገድ እስከመዝጋት የሚደርስ ርምጃን እንዲወስድ የሚፈቅድ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።

ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መውጣት በመንግሥት የተገለፀው፤ በሀገሪቱ የተፈጠረው አለመረጋጋት እንደሆነ ተጠቅሷል። አዋጁንም ከ15 ቀናት በኋላ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እንደሚፀድቅ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ቢናገሩም፤ የምክር ቤቱ አባላት ካልተቀበሉት ውድቅ ሊደረግ እንደሚችል አሊያም ሌላ አማራጭ ስለመኖሩ ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: