(ዳጉ ሚዲያ) ከወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ህዝባዊ ተቃውሞ በእስር ላይ ከነበሩት ሰዎች መካከል ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ፥ አቶ ጌታቸው አደመ፥ አቶ አታላይ ዛፌ፥አቶ ተሻገር ወልደሚካኤል እና ንግስት ይርጋ ጨምሮ የ 101 እስረኞቸ ክሳቸው እንዲቋረጥ መደረጉን ለመንግሥት ቅርበት ያላቸው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እና ወ/ት ንግስት ይርጋ
ክሳቸው እንዲቋረጥ ከተወሰነላቸው እስረኞች መካከል 56 በግንቦት ሰባት፥ 41 እንዲሁም ከኦነግ ጋር ተባብራችኋል በሚል ክስ የተመሰረተባቸው ነበሩ።
ብ/ጄነራል ተፈራ ማሞ እና ብ/ጄነራል አሳምነው ጽጌ
በተያያዘ ዜና፤ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የሚል ክስን ጨምሮ በተለያየ ጉዳይ ተከሰው የተፈረደባቸውና በይቅርታ ከእስር እንዲለቀቁ ከተወሰነላቸው መካከል ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞና ብርጋዴር ጀነራል አሳምነው ጽጌን እንደሚገኙብት ተጠቁሟል።