የዋልድባ ገዳም መነኮሳት አባ ገብረ-ሥላሴ ስና አባ ገብረ-ኢየሱስ የፍርድ ቤት ውሎ

ሀብታሙ ምናለ

የፌደራሉ ከፍተና ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት፤ የካቲት 30 ቀን 2010 ዓ. ም. በዋለው ችሎት የዋልድባ መነከሳት ባቀረቡት “የሰብዓዊ ጥሰት በማረሚያ ቤቱ ተፈፅሞብናል ፍርድ ቤቱ ተትዕዛዝ ይስጥልን!” ብለው ያቀረቡትን አቤቱታ ሰምቶ የማረሚያ ቤቱን ምላሽ ለመስማት ሲኾን ማረሚያ ቤቱም ምላሽ የሚለውን በደብዳቤ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡

ፍርድ ቤቱ ማረሚያ ቤቱ የሰጠውን ምላሽ እንደተመለከተው እና ውሳኔ እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡ አባ ገብረ ኢየሱስ ኪዳነ ማርያም “የተከሰስነውም የታሰርነው አንድ ላይ ቢኾነም እኔን ያለምንም ምክንያት ወደ ዞን አምስት በተለምዶ ጨለማ ወይም ቅጣት ቤት ወደሚባለው አዘዋውረውኛል፡፡ ተቀጥቼ ከኾነ ጥፋቴ ተነግሮኝ፤ ቅጣቴ ምን ያህል ቀን እንደኾነ አውቄ ቅጣቴን ልቀበል፤ ያለምንም ጥፋት ዝም ብዬ ነው፡፡ እየተሰቃየኹ ያለኹት ብዙ በደል ደርሶብናል፡፡ ከአመት በላይ ልብስ ሳንቀይር ቆይተን በቅርብ ቀን አንድ ምዕመን ልብስ አምጥቶልኝ እኔ ለመቀየር ችያለሁ፡፡

ነገር ግን አባ ገብረሥላሴ ከተያዙ ጀምሮ ምንም ልብስ ቀይረው አያውቁም። ሰዎች ልብስ ሲያመጡ ማስገባት አይቻልም፡፡ እያሉ እያስመለሱ ከአንድ ዓመት በላይ በአንድ ልብስ ብቻ ሳናወልቅ ቆይተናል፡፡ ኹለታችንም አብረን በአንድ ዞን የነበርነው ያለምክንያት በታትነውናል፡፡ ሰዎች ሊጠይቁን ሲመጡ የተለያየ ዞን በመኾናችን ጠያቂዎቻችን እክል እየገጠማቸው ነው፡፡ ወደነበርኩበት ዞን ልመለስ” ብለው ጠይቀዋል፡፡

ዳኞቹም፡- “ልብስ ለምን አይገባም?” ብለው የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች ሲጠይቁ መልስ መስጠት ባለመቻላቻው “ልብስ ማነው የሚያመጣላችሁ?” ብለው ዳኞች ሲጠይቁ ችሎቱን ሲከታተሉ ከነበሩት ወጣቶች መካከል ለአንዳቸው የሚኾን የምንኩስና ልብስ ገዝተው ይዘው ነበር፡፡ ልብሱን ሲያቀርቡ ዳኞቹ፡- “ጠባቂዎቹን ፈትሹና ስጧቸው!” ቢልም ፍቃደኛ አለመኾናቸውን ሲያሳዩ ዳኞቹ በቁጣ “ተቀበሉና ፈትሻችሁ ስጡ!” በማለት ሲያዙ የማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ወታደራዊ ሰላምታ በመስጠት ወደ ዳኞቹ ተጠግቶ ሊናገር ሲል ዳኞቹ፡- “የተባልከውን ብቻ አድርግ! ምንም ሌላ አያስፈልግም!” በማለት ልብሱ ተፈትሾ ለአባ ገ/ሥላሴ ተሰጥቷቸዋል፡፡

ፍርድ ቤቱም ያቀረቡትን አቤቱታ እና የተሰጠውን መልስ አይተው ውሳኔ ለመስጠት ለመጋቢት 5 ቀን 2010ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ መጋቢት 18 መደበኛ የክስ የሚቀጥል እና ምስክር እንደሚሰማባቸው ይታወቃል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: