የዋልድባ መነኮሳት ክሳቸው ተቋረጦ ከእስር ተለቀቁ

በፌደራል አቃቤ ህግ በሽብር ወንጀል ተከሰው ለበርካታ ወራት ታስረው የነበሩት የዋልደባ መነኮሳት ከእስር ተፈቱ። መነኮሳቱ ከዋልደባ ገዳም ታፍነው ለበርካታ ወራት ታስረው ጉዳያቸው በፍደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሲታይ ቆአይቶ በመጨረሻም ክሳቸው ተቋርጦ ተፈተዋል።

Waldeba Monastry arrested monks
መነኮሳቱ ልደታ ፍርድ ቤት ሳሉ

መነኮሳቱ በአዲስ አበባ በሚገኘው ቃሊቲ ፌደራል ወህኒ ቤት ባሉ የጥበቃና የደህንነት አባላት ተደጋጋሚ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይፈፀምባቸው እንደነበር አብቱታዎቻቸውን ለፍርድ ቤት ሲያቀርቡ እንደነበር ይታወሳል።

መነኮሳቱ አባ ገብረኢየሱስ ኪዳነ ማርያም፥ አባ ገብረሥላሴ ወልደኃይማኖት፥ መርጌታ ዲበኩሉ እንዲሁም አቶ ለገሰ ወልደሐና፥ አቶ ሀብታሙ እንየው ጨምሮ 114 የፖለቲካ እስረኞች ክሳቸው ተቋርጦ ከታሰሩበት ወህኒ ቤት ተለቀዋል።

በመጨረሻም፤ መነኮሳቱ ከእስር በመፈታታቸውን ፈጣሪን በማመስገን አሁንም በርካታ ዜጎች ፍርድ ቤት እንኳ ሳይቀርቡ ለዓመታት በውህኒ ቤት ያሉ እንዳሉ እና ሀገሪቱ ኢትዮጵያ እና ኃይማኖታቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እስር ላይ እንዳሉ በማስታወስ ሁሉም ከእስር ነፃ ካልወጡ ራሳቸውን ከእስር እንደተፉ እንደማይቆጥሩ ተነግረዋል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: