የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥፋተኛ መሆኑን አመነ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምንያህል ተሾመ ሰኔ 1 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ጋር በተደረገው ጨዋታ መሰለፉ ስህተት እንደሆነ አመነ፡፡ ፌዴሬሽኑ ብሄራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ አቻው ጋር ከመጫወቱ በፊት ችግር ስለመፈጠሩ ከፊፋ ደብዳቤ ደርሶት እንደነበርም ገልጿል፡፡

የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለችግሩ ተጠያቂ ያላቸውን ግለሰቦች ዝርዝርም ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ መሰረት የብሄራዊ ቡድኑ ቡድን መሪ አቶ ብርሀኑ ከበደ ፣ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ፣ ረዳት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ፣ የቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ እና የፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች ጥፋተኛ ተብለዋል።
ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በጥፋተኞቹ ላይ በቅርቡ ተገቢውን ቅጣት በመውሰድ የቅጣት ውሳኔውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡
ፌዴሬሽኑ በተፈጠረው ችግር ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ገልፆ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርታ ጠይቋል፡፡
የቡድኑ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በተፈጠረው ስህተት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው ፥ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ለሚካሄደው ጨዋታ ከወዲሁ መዘጋጀት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ጨዋታውም አሸንፈን ወደ አለም ዋንጫ እንደምንሳተፍ እርግጠኛ ነኝ ብለዋል ፡፡
በፊፋ ህግ መሰረት ተገቢ ያልሆነ ተጨዋችን ማሰለፍ በጨዋታው የተገኘውን ነጥብ እና ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት እንደሚያስጥል ይታወቃል፡፡
የሎሬት አፈወርቅ ተክሌ ንብረት እያወዛገበ ነው
1ሚ. ብር አበድሬአቸዋለሁ የሚል ድርጅት ክስ ሊመሰርት ነው የአዋሣው ቤታቸው ተሸጦ ስም መዛወሩ እያነጋገረ ነው
እጅግ የተከበሩ የአለም ሎሬት አርቲስት አፈወርቅ ተክሌ ንብረት እያወዛገበ ነው፡፡ አርቲስቱ በሕይወት ሳሉ አንድ ሚሊዮን ብር አበድሬአቸዋለሁ የሚል ድርጅት ለክስ ወደ ፍርድ ቤት ማምራቱን ምንጮች ገልፀዋል፡፡ ሎሬት አፈወርቅ በህይወት ሳሉ የስዕል ሥራዎቻቸውን፣ ቪላ አልፋንና ሙሉ ንብረታቸውን ለመንግስት ማውረሳቸውን ተከትሎ፣ መንግስት ንብረቱን ለመረከብ እንቅስቃሴ ጀምሮ እንደነበር ይታወቃል፡፡ የእኚሁን ታላቅ አርቲስት ንብረት ለማጣራትና ለመመዝገብም ከፍርድ ቤት፣ ከታዋቂ ሰዎችና ከሙያ ባልደረቦች የተውጣጣ ኮሚቴ ተቋቁሞ ምዝገባና ቆጠራ ቢጀመርም ፍፃሜ ሣያገኝ ተቋርጧል፡፡ ሎሬት አፈወርቅ ተክሌ በህይወት ሣሉ የአክሲዮን ባለ መብት ለመሆን አንድ ሚሊዮን ብር ወስደዋል በሚል የአርቲስቱን ስዕሎች ይሸጥ በነበረ አንድ የማስታወቂያ ድርጅት ክስ ሊመሰረት መሆኑን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
ጉዳዩ በፍርድ ቤት እልባት እንዲያገኝ ለኮልፌ ምድብ ችሎት ተመርቶ እየታየ መሆኑን የጠቆሙት ምንጮች፤ ለጊዜው የንብረት ምዝገባና ቆጠራው መቋረጡን ገልፀዋል፡፡ በአዋሣ ከተማ የሚገኘውና በሎሬት አፈወርቅ ተክሌ ስም የተመዘገበው ቤት በቀድሞ ባለቤታቸው አማካኝነት መሸጡን የጠቆሙት ምንጮች፤ የቤቱ ስም የተዛወረበት አሠራር ሕጋዊነት አነጋጋሪ እየሆነ መምጣቱን ጠቁመዋል፡፡ በሎሬት አፈወርቅ ተክሌ ስም በለንደንና በስኮትላንድ ባንኮች ያለ ገንዘብ እንዲመለስ ጥረት እየተደረገ ሲሆን በተለያዩ አገራት ያሉ ስዕሎችና ንብረቶችን ለማስመለስም እየተሞከረ ነው ተብሏል፡፡ የአርቲስቱ ንብረት ካለባቸው አገራት መካከልም ንብረቱንና ገንዘባቸውን ለመመለስ ፈቃደኛ የሆኑና በመመለስ ሂደት ላይ የሚገኙ እንዳሉ ተጠቁሟል፡፡
የሎሬት አፈወርቅ ተክሌ ቪላ አልፋ፤ በኮሚቴዎቹ ሲከፈት በሺዎች የሚቆጠር ፓውንድ በካዝናቸው ውስጥ መገኘቱንና ይህም በንብረት ዝርዝር ላይ ተመዝግቦ መያዙን ምንጮች ገልፀዋል፡፡ በፍርድ ቤት ጉዳይ የተቋረጠው የሎሬት አፈወርቅ ንብረት ቆጠራና ርክክብ መዘግየት በንብረቱ ላይ አደጋ ሊያስከትል እንደሚችል የጠቆሙት ምንጮች፤ እጅግ ውድ ዋጋ ያላቸው
ስዕሎቻቸውና የአርቲስቱ የመኖሪያ ቤትና የስዕል ስቱዲዮ የሆነው ቪላ አልፋም የመበላሸት አደጋ አንዣቦበታል ብለዋል፡፡ የሎሬት አፈወርቅ ተክሌ የቀብር ሥፍራ ምንም አይነት የማስታወሻ ሐውልት ሣይሰራበት መቅረቱን የጠቀሱት ምንጮች፤ ከጥቂት ጊዜ በኋላ የቀብራቸው ሥፍራ ሊጠፋ ይችላል የሚል ሥጋት መፈጠሩን ገልፀዋል፡፡
Written by መታሰቢያ ካሣዬ- http://www.addisadmassnews.com/
ከኮለኔል መንግስቱ እና ከአቶ መለስ ለኢትዮጵያ ሕፃናት አባት በመሆን ፋውንዴሽን ሊመሰረትለት የሚገባው ማነው?
”ጎዳና ቤቴ’
ሰኔ 25/2012 እአአቆጣጠር በቢቢሲ ድህረ ገፅ ላይ በወጣ አንድ ዘገባ መሰረት ኢትዮጵያ በአመት 5ሺህ በላይ ሕፃናት በማደጎነት ወደ አሜሪካ ብቻ እንደሚሄዱ እና አሜሪካ ከዓለም ላይ በማደጎነት ከምትወስደው ሕፃናት ኢትዮጵያውያን ሕፃናት ከ አምስቱ አንዱ እንደሆኑይገልፃል።(http://www.bbc.co.uk/news/world-africa-18506474)
ከኮለኔል መንግስቱ እና ከአቶ መለስ ለኢትዮጵያ ሕፃናት አባት በመሆን ፋውንዴሽን ሊመሰረትለት የሚገባው ማነው?
ቅዳሜ ጧት
” አቡነጎርጎርዮስ የዝዋይ ገዳም መስራች አንድቀን የመንፈስ ልጆቻቸውን እያስተማሩ ኮለኔል መንግስቱ ከአዋሳ ሲመጡ ጎራ ይላሉ።ወደ ገዳሙ ውስጥ ሳይገቡ ገና አጥሩን ሲመለከቱ በረጅሙ ታጥሮ ይመለከቱ እና ‘ይሄ መነኩሴ ይህን ይህል ቦታ አጥሮ አገሩ ታድያ ምን ተረፈ’ ይሉ እና አንዱን ወታደር አቡነ ጎርጎርዮስን እንዲጠራቸው ይልኩታል። አቡነ ጎርጎርዮስ መልክቱ እንደደረሳቸው ‘አሁን ትምህርት ላይ ነኝ ደግሞስ ፈላጊ ይመጣል እንጂ ተፈላጊ እንዴት ይሄዳል?’ ብለህ ንገረው ብለው መልሰው ይልካሉ።ኮለኔል መንግስቱ እንዲህ አይነት ድፍረት በመስማታቸው ምንም ሳይሉ ወደ አዲስ አበባ ይመለሳሉ። በቀጣዩ ቀናት አቡነ ጎርጎርዮስ ኮለኔል መንግስቱን ቅሬታቸውን ለመንገር ይመጣሉ።ቅሬታቸው ሌላ ነበር።እንደገቡ አቡነ ጎርጎርዮስ በቁጣ ”ለመሆኑ ሕፃናት አምባ የምታሳድጋቸው ልጆች አምላካቸውን ካላወቁ አውሬ እንደሚሆኑ ታውቃለህ?” ይሉታል ይደነግጣል። ”ምን ይደረግ?” ይላቸዋል።”ለእኔ ፍቀድልኝ እኔ የማደርገውን አውቃለሁ ” ይሉታል። ከድጋፍ ደብዳቤ ጋር ይልካቸዋል።
ምንጭ ፡- ከጉዳያችን ብሎግ የተወሰደ
ኸረ ዛሬም በአጃቢዎች እየተጠበቁ ነው !
ብስራት ወልደሚካኤል
afrosonb@gmail.com
አቶ መለስ ዜናዊ በህይወት እያሉ የጥበቃ አጃቢዎችን ብዛት ላየ የምር የሚሞቱ አይመስልም ነበር፡፡ ግን የማይሞት የለ እንዲሉ አቶ መለስ ስንቱን ኢትዮጵያዊ በግፍ ጨካኝ አመራራቸው ሲያስጨንቁ 21 ዓመታትን ካሳለፉ በኋላ ነሐሴ 14 ቀን 2004 ዓ.ም. መሞታቸው በአምላኪዎቻቸው ይፋ ሆነ፡፡ ይሁን እንጂ አምላኪዎቻቸው ነሐሴ ሞቱ ቢሉንም እሳቸው የሞቱት ሐምሌ 3 ቀን 2004 ዓ.ም. ኢትዮጵያዊያንን ካስጨነቁ በኋላ በቤልጂየም ብራሰልስ ሴይንት ሉክ ሆስፒታል በሞትና በህይወት መካከል ከተጨነቁ በኋላ ፓርቲያቸው ይቆዩልን ቢሉም ሳይሰናበቷቸው በጨበጣ ያለፈቃዳቸው የላይኛው ጥሪ በልጦ ላይመለሱ ሄደዋል፡፡ ያኔ ግን ትዝ ይላችኋል? ነሐሴ 15 ቀን 2004ዓ.ም. አቶ በረከት ስምዖን የአቶ መለስን መሞት በጠዋቱ ሲያረዱን “ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ባጋጠማቸው ኢንፌክሽን ትናንት ሐምሌ 14 ቀን 2004ዓ.ም.ከምሽቱ 4 ሰዓት ህይወታቸው አልፏል” አሉ፡፡ ግን አቶ በረከት የሰውየውን መሞት ለማርዳት የፈጠኑ አልመሰሏችሁም? በድናጋጤ እንዳንሞት እንኳ አላዘኑልንም፤ ያው ኢህአዴግ በተፈጥሮው “ግልፅ, ዴሞክራትና ዘመናዊ አስተዳደርም” አይደል? ለዛ ነው ቶሎ የነገሩን ፤ቢዘገየም ብራቮ! አቶ በረከት ብያለሁ፡፡
የአምባገነኑን ጨካኝ ለኢህአዴግዎች ቅዱስ የሆኑት መሪ ሞታቸውን ዓለም ይወቅልን፣ ነፍሳትም ያንቡ፣ ህዝቡም ይሰናበታቸው፣.…ተብሎ እምባ ማይታክታት ሀገር ህዝቡ ከነጭፍሮቻቸው በፈፀሙት የግፍ አገዛዛቸው 21 ዓመታትን ማልቀሱ ሳያንሰው ሞታቸው ከተነገረ ጀምሮ 13 ቀናት ምድሯን በጥቁር ልብስ ገበያ ካደሩ በኋላ ምክንያቱ ሳይታወቅ አስከሬኑ ለህዝብ ሳይታይ ባማረው የውጭ ሳጥን ነሐሴ 27 ቀን 2005ዓ.ም ግብዓተ መሬታቸው አዲስ አበባ በሚገኘው መንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ግቢ ተፈፅሟል፤ ወዳጆቻቸው እንዳሉን ከሆነ፡፡ ምክንያቱም ደጉ ለሀገሪቱ ህዝብ አላስ…የሆኑት አምባገነን መሪያችንን አስከሬን እንደነ ክቡር አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ፣ የዓለም ሎሬት አፈወርቅ ተክሌና አቡነ ጳውሎስ አስከሬኑ ለህዝብ አልታየማ! ባለማየታችንም ቢሆን ቅር አይለንም፣ አንኮነንም…”ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው” አይደል የሚለው ቃሉ? ደግሞስ እንኳን የእሳቸውን መሞት ቀርቶ የሀገራችንን ዕድገትስ በነገሩን ብቻ ያልኖርንበትን ሳናይ 11 በመቶ አድገናል ሲሉን እያመንን አይደል?….፤ታዲያ እሳቸው ከኢትዮጵያ በምን ያንሳሉ?…ምክንያቱም በህይወት እያሉ እራሳቸውን ብቻ ተቋምም፣ሀገርም ፣ህዝብ አርገው ይቆጠሩ ነበርና፡፡
አሁን ግን ግብዓተ መሬታቸው የተፈፀመበት ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን በወጣቶች ስፖርትና መዝናኛ(ወወክማ) አቅጣጫ ባለው መካነ መቃብራቸው ቦታ ግዙፍ የማያልቁ ትላልቅ ሻማዎች እየበሩ(እሳቸው ግን ተፍተዋል) በሁለት የጦር መሳሪያ በታጠቁ መከላከያ ሰራዊት ዘወትር ይጠበቃል፡፡ እንዴት ነው ነገሩ? ሰውዬው ሞተውም ይፈራሉ እንዴ? ወይ አምባገነን ለካ ሞቶም አያርፍ…..!
ሌላው ያስገረመኝ ጉዳይ ቤተክርስቲያን ሊሳለምና ፀሎቱን ሊያደርስ የሚሄድ ምዕመን ድንገት ዓይኑን አዲስ ወደ ሆነበት መካነ መቃብር አቅጣጫ መልከት ቢያደርግ አስከሬኑ ያረፈበት አጠገብ በተጠንቀቅ የተቀመጡት የመከላከያ ሰራዊቶቹ ግልምጫና ፍጥጫ ምን እሚሉት ነው? ደግሞስ ለሙት የሚደረገው ጥበቃ እና እኒያ ግዙፍ አራቱ ሻማዎች በጀት ከማን ይሆን የሚሸፈነው? መቼም ጉድ እማይሰማ የለ! ከሀገሪቱ በጀት ነው እንዳይባል፣ አያደርጉትም አይባልማ! እንዲህ ከሆነማ በቁማቸው ሀገሪቷንና ህዝቡን የጋጡት የኢህአዴግ ቱባ ቱባ ባለስልጣናት ሲሞቱ እንዲህ የሀገር በጀት የሚባክን ከሆነ ምን ቀረን…?
ግድ የለም ጎበዝ!…ከእንግዲህ ሞተውም በዛ ክፉ መንፈሳቸው ሀገር ማተራመስና ማራቆት ስለማያቆሙ አትሙቱብን፣ በቁማችሁ ጋጡና ጨርሱን ብለን እንፀልይላቸው ይሆን ወይስ…..? ኦ…ኦ…የረሳሁት ትዝ አለኝ!…ግን መከላከያ ሰራዊቱ የሞተ አስከሬን እንዲጠብቁ የተደረጉት የአቶ መለስ አምላኪ ኢህአዴጋዊያን አውጠተው የሙዚየሙን ስራ ያስተጓጉላሉ ተብሎስ ይሆን? የሀገሪቱ ካዝና ይመስል ምናልባት ሼም ስለማያውቁ ሊሆን ይችላል፤ አለበለዚያ ሰውዬው በምድር ለሰሩት ግፍ ወደላይኛው ቅጣት እንዳይሄዱ/እንዳያርጉ ታስቦስ ይሆን? ኸረ መላ በሉን ጎበዝ! ሞተውና ተቀብረውም ስፍራው በመከላከያ ጦር መጠበቁ ለምን ይሆን?


