የታላቁ ህዳሴ ግድብ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ተገደሉ
(ዳጉሚዲያ) በአባይ ወንዝ ላይ እየተሰራ የሚገኘው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ዋና ስራ አስኪያጅ ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ዛሬ ሐምሌ 19 ቀን 2010 ዓ ም ከጠዋቱ 2፡20 ሰዓት አካባቢ አዲስ አበባ በሚገኘው መስቀል አደባባይ በግል የቤት መኪናቸው ውስጥ በጥይት ተገድለው መገኘታቸውን የፌደራል ፖሊስ ዋና ኮሚሽን ዳይሬክተር ጄነራል ዘይኑ ጀማል ይፋ አድርገዋል። ይሁን እንጂ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስ ግድያው እንዴት እና በማን እንደተፈፀመ ያልታወቀ ሲሆን፤ የፌደራል እና የአዲስ አበባ ፖሊስ ምርመራ እያደረጉ መሆኑን ኮሚሽነሩ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።
ፎቶ፡ ኢንጂነር ስመኘው በቀለ በታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ስራ ላይ
እንደፖሊስ መረጃ ከሆነ ኢንጂነሩ ጠዋት አዲስ አበባ በሚገኘው ቢሯቸው ገብተው እንደነበር የገለፅ ሲሆን፤ ከጠዋቱ 2፡20 ሰዓት ላይ ግን መስቀል አደባባይ ከመደበኛው የተሽከርካሪ መንገድ ገባ ብሎ ወጣቶች ስፖርት ወደሚያዘወትሩበት ቅርብ ርቀት በኮድ 3 አ.አ (AA)29722 ቶዮታ ብርማ ቀለም መኪና ውስጥ በአሽከርካሪው ወንበር ላይ እንድተቀመጡ በቀኝ ጆሯቸው በስተኋላ በጥይት ተገድለው መገኘታውን አረጋግጧል። ይህ በእንዲህ እንዳለ በጥይት የተመቱበት ጆሯቸው አካባቢ ደም ሲፈሳቸው እንደነበር፤ እንዲሁም በቀኝ እጃቸው በኩል ኮልት ሽጉጥ መገኘቱን ፖሊስ አስታውቅዋል። ፖሊስም ለምርመራ ይረዱኛል ያላቸውን መረጃዎች ከሰበሰበ በኋላ ለተጨማሪ ምርመራ ከረፋዱ 5፡30 ሰዓት ላይ አስከሬናቸው ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል መወሰዱንም ጨምረው ገልፀዋል። ከግድያው ጋር በተያያዘ መረጃ ይኖራቸዋል በሚል በርካታ ተጠርጣሪዎች እና የአይን እማኞች ወደ ፌደራል ፖሊስ ምርመራ መወሰዳቸውም ታውቋል። የምርመራው ውጤት እንደተጠናቀቀ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግም ኮሚሽነሩ ገልፀዋል።
ፎቶ፡ የታላቁ ህዳሴ ግድብ ሲጠናቀቅ የሚኖረው ገፅታ በከፊል
ኢንጂነሩ ትናንት ሐምሌ 18 ቀን 2010 ዓ ም ከቢቢሲ የአማርኛ ፕሮግራም አጭር ቃለመጠይቅ ሰጥተው እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፤ ህይወታቸው እስካለፈ ድረስ በተለይም ከታህሥሥ 2 ቀን 2003 ዓ ም የታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት ዋና ስራ አስኪያጅ በመሆን እያገለገሉ እንደነበር ታውቋል።
አቶ አበበ ካሴ በእስር ቤት ስለደረሰበት ግፍ ተናገረ
ዳንኤል ተስፋዬ
~ “በግብረሰዶም ወንጀል ከተፈረደባቸው እና ከአህምሮ እመምተኞች ጋር ከአንድ አመት በላይ አንድ ላይ አንድታሰር ተደርጌያለሁ”
~ በደረሰብኝ ኢ-ሰባዊ ድርጊት ኩላሊቴ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶበታል። ሽንቴንም መቆጣጠር አልችልም…”
~”ከወልቃይት ማንነት ጋር በተያያዘ አሁንም በማረሚያ ቤት ሀላፊዎች ድብደባ እየፈፀሙብኝ ነው…”
በግንቦት 7 ስም ተከሶ 7 ዓመት ተፈርዶበት አዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ቃሊቲ የሚገኘው የአበበ ካሴ በእስር ቤት በደል እየተፈፀመበት እንደሚገኝ ገልፆአል።
ከ2006 ዓ.ም. ጀምሮ በእስር ላይ የሚገኘው አበበ ካሴ በቃሊቲ ማ /ቤት ከፍተኛ ስቃይና ድብደባ እንደደረሰበት ተናገረ። ከዝዋይ ማረሚያ ቤት ወደ ቃሊቲ ከተዛወረ ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ በፖለቲካ አመለካከቱ ምክንያት ሱፐር ገብረ ህይወት፣ ኦፌሰር መካሻ፣ ኦፌሰር ጥላሁን እና ሌሎችም የማረሚያ ቤቱ አመራሮች ከፍተኛ ድብደባ እንደፈፀሙበት ገልፆአል።
ስነ ልቦና እና አካላዊ ጉዳት እንዲደርስበት ግበረ ሰዶም ተከሰው ከተፈረደባቸው እና የአህምሮ ህመምተኞች ለብቻቸው ከሚተሰሩበት ማቆያ እንዳሰሩትም ተናግሯል። “ከወልቃይት ማንነት ጋር በተያያዘ እዚህ ሆነህ ወጣቶች እንዲደራጁ፣ እንዲያምፁ፣ በወልቃይት ጉዳይ ህዝብ አቋም እንዲይዝ መልህክት አስተላልፈሃል” በሚል ድብደባ ተፈፅሞብኛል ብሏል።
“እስር ቤት ውስጥ በደረሰበት ድብደባ ኩላሊቴ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብኛል። ሽንቴንም መቆጣጠር አልችልም” ብሏል። ይህን መረጃ ያጠናቀረው ዳንኤል ተስፋየ አበበ ከፍተኛ የሆነ የወገብ ህመም እና ድካም እንዳለበት መታዘብ ችሏል።
በሌላ ክስ 20 አመት ተፋርዶበት ከአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ፍርድ ቤት ቅጣቱ ተፈፃሚ እንዲሆን ትህዛዝ ለቃሊቲ ማረሚያ ቤት መሰጠቱን አበበ ገልጿል። አቶ አበበ ካሴ በማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ በደረሰበት ድብደባ እና ስቃይ 20 የእግሩ እና የእጁ ጥፍሮቹ ሙሉ በሙሉ መነቀላቸው፣ ብልቱ መኮላሸቱ፣ በኤሌክትሪክ ንዝረት በተፈፀመበት ግርፋት ለ11 ወራት ያህል አንድ ጎኑ ደንዝዞ እንደነበር በዚህም ምክንያት የእግሩ ጡንቻዎች መሸማቀቃቸው መግለፁ ይታወሳል።
ጋዜጠኛ እስክንድር እና ውብሸት ታዬ ከእስር ተለቀቁ
ላለፉት 6 ዓመት ከ6 ወራት በእስር ላይ የነበሩት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ዛሬ የካቲት 7 ቀን 2010 ዓ ም ከእስር ተለቀዋል።
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፥ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ እና ጦማሪ ዘለዓለም ወርቅአገኝሁ
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በመንግሥት በቀረበበት ክስ የ18 ዓመት እስርት ተፈርዶበት የነበረ ቢሆንም፤ ጋዜጠኛ እስክንድር የፔን አሜሪካ “Freedom to write Award” እና የዓለም አቀፍ የፕሬስ ተቋምን “World press freedom Hero” የሚሉ ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን ማግኘቱ ይታወሳል። ከእስር እንደተፈታም ህዝቡ ላደረገለት ድጋፍና አቀባብል አመስግኗል።
ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በቀረበበክ ክስ 14 ዓመት እስር ተፈርዶበት የነበረ ሲሆን፤ እ. አ. አ. የ213 ዓለም አቀፍ የአፍሪካ ንፃ ፕሬስ “African free press Award” አሽናፊ ሲሆን በእስር ቤት ሳለ ሁለት መፅሐፍትን ለንባብ ማብቃቱ ይታወቃል።
ባለፈው ደብርሃን ድረ ገፅ ጦማሪ ዘለዓለም ወርቅአገኘሁ ባለፈው ጥር 21 ቀን 2010 ዓ.ም. የተበየነበት እስር በአመክሮ በማጠናቀቅ ከእስር የተፈታ ሲሆን፤ ክሳቸው በአቃቤ ህግ ይግባኝ እየታየ የነበሩት የዞን 9 ጦማሪያን ክስም ዛሬ እንዲቋረጥ መደረጉ ታውቋል።
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፥ አቶ አንዱዓለም አራጌ፥ እና ሌሎችም …
ብስራት ወልደሚካኤል
ረቡዕ መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ. ም. በግምት ከቀኑ 10 ሰዓት አካባቢ ሰላማዊ ሰዎች ከመደበኛ ዕለታዊ እንቅስቃሴዎቻቸው እንደወንጀለኛ ታድነው የታሰሩበት ቀን ነው።
ፎቶ፡ ከማኅበራዊ ገፅ
ረቡዕ መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ. ም. በግምት ከቀኑ 10 ሰዓት አካባቢ ሰላማዊ ሰዎች ከመደበኛ ዕለታዊ እንቅስቃሴዎቻቸው እንደወንጀለኛ ታድነው የታሰሩበት ቀን ነው።
አንዱዓለም አራጌ በወቅቱ የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ እና ምክትል ሊቀመንበር ነበር። ሀገር ሊያቀና ሲኳትን የነበረው አንዱዓለም ሰላማዊ የመብት ትግልን ስራው አድርጎ መንቀሳቀስ የጀመረው ገና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪ ሳለ ነው።
መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ. ም. ሰቆቃ አላልቅ ወዳለበት ማዕከላዊ እና ቃሊቲ ወህኒ ቤት ከገፋቱ በፊት ጠዋቱ የመጀመሪያ ልጁን ሩህ አንዱዓለምን ለመጀመሪያ ጊዜ ትምህርት ቤት አድርሶት ወደ አንድነት ፓርቲ መደበኛ ስራው ገብቷል። በዕለቱም ከመቼው ጊዜ በላይ ደስ ብሎት ይታይ ነበር። ምክንያቱ ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ የአብራኩን ክፋይ ፥ልጁን እጁን በመያዝ ወደ ትምህርት ቤት የወሰደበት ቀን ነውና። ይሄንን ደስታውንም በወቅቱ እዛ ለነበርን ሰዎች ሁሉ ሲያጋራ አስታውሳለሁ። ደስ የሚል ደስታ፥ በፍቅር የተሞላ ፈገግታ፥ የምርም ደስስስስ ይል ነበር። ማታ ወደ ቤት ተመልሶ የልጁን የትምህርት ቤት የመጀመሪያ ቀን ውሎ ምን እንደሚመስል እና የተሰማውን ስሜት ለማጣራትም ያቺ የአንዲት ቀን ጉማጅ እንደረዘመችበት አስታውሳለሁ።
ግን ምን ዋጋ አለው? የዛሬን አያድርገውና ፤በዕለቱ በግምት ከቀኑ 8 ሰዓት አካባቢ ከአውራምባ ታየምስ ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል (ከዳዊት ከበደ እንደተደወለለት እንደነገረኝ ትዝ ይለኛ) ስልክ ተደወለለት። ስልኩንም አነሳ። ከዛም በዛሚ ኤፍ ኤም ሬዲዮ አንዱዓለምን፥ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣና ይዛ በወጣችው ሐሳቦች ዙሪያ በዛሚ ኤፌ ኤም ሬዲዮ “የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ” በሚለው የዕለቱ የቀትር መርሃ ግብር ነገር እየተቦካ እንደሆነ እና እንዲያደምጥ ተነገረው።
በወቅቱ ቢሮው ውስጥ መደበኛ ሬዲዮ አገልግሎት ስለሌለና በስልኩም አገልግሎቱን ማግኘት ስላልቻለ ቢሮው ከሚገኝበት ፎቅ በመውረድ የሰማውን ነገር ነገረኝ። ያቺ ደካማ ስልኬ ሬዲዮ እንደምትሰራ ጠየቀኝ። እኔም በስልኬ መሰል አገልግሎት አልባነት እየሳቅሁ የስራ ባልደረባዬ የነበረውን ጋዜጠኛ ብዙአየሁን ጠየቅኩት። የእሱም ስልክ እንደኔው የሬዲዮ አገልግሎት አልነበረውም። ከዛም የጋዜጣው ፀሐፊዎች የነበሩትን የሺን እና ብርቱካንን ጠየቅን እና ከአንዳቸው አገኘን። በመጨረሻም ከማን እንደሆነ ለጊዜው ባላስታውስም በተገኘው ስልክ በነ ሚሚ ስብሃቱ (ዛሚ ኤፍ ኤሜ ሬዲዮ) “የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ” በሚለው የዕለቱ መርሃ ግብር ላይ ስለ አንዱዓለም አራጌ፥ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና “ፍኖተ ነፃነት” ጋዜጣ የማክሰኞው መስከረም 2 ቀን 2004 ዓ. ም. ዕትም ይዘት ላይ ጭምር በነ ሚሚ ስብሃቱ፥ መሰረት አታላይ ፥ ፀጋልዑል መኮንን? እና ሁለት ሌላ ባልደረቦቻቸው በአደባባይ ሲቦጭቁ፥ ሲዘረጥጡና ሲወነጅሉ ሰማናቸው።
ሁላችንም በተደረገው የስም ማጥፋት እጅግ አዘንን፥ ተናደድን። ምክንያቱም እነ ሚሚ ምንም ያህል ለህወሓት/ኢህአዴግ ወግነው ጥብቅና የሚቆሙ፤ ኽረ እንደውም ከጳጳሱ ቄሱ ቢሆኑ እንኳ እንደዚህ በአደባባይ የሌለና ያልተፈፀመ እንዲሁም ያልተባለን ነገር ሽብር እንደተነዛና እንደተፈጠረ ተደርጎ መቅረቡ በጣም ያም ነበር። በርግጥ አሁንም ያው ናቸው። ውንጀላቸው በ “ፍኖተ ነፃነት” ጋዜጣ ላይ የወጡ ይዘቶችን፤ በተለይም የአንዱዓለም ቃለ መጠይቅ እና የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የአረቡን አብዮት በተመለከተ በአንድነት ፓርቲ በተደረገለት ግብዣ ያቀረበውን ትንታኔና ውይይት በተመለከት ነበር።
በነገራችን ላይ በአገዛዙ እና በአገዛዙ ወዳጆች በግል ሚዲያ ስም ድጋፍ እንደ ተቋቋመና እስካሁንም ሙሉ በጀቱ እንደሚሸፈንለት የሚነገረው የነ “ሚሚ ስብሃቱና ባለቤቷ ዘሪሁን ተሾመ” ዛሚ ኤፍ ኤም ሬዲዮ፤ “የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ” የሚለው የእሁድና ረቡዕ የሚዘጋጅ መርሃ ግብር አለ። ይህ ኤፍ ኤም ጣቢያ የህወሓትን ጥቅም ይጎዳሉ ተብለው የሚታሰቡ ጋዜጠኞች፥ ህዝባዊ ቅቡልነትና ከፍተኛ ድጋፍ አላቸው የሚባሉ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች፥ አንዳንዴም የህወሓትን ክፉ ስራና ድርጊት ይገዳደራሉ ተብለው የሚታሰቡ በስሩ ያሉ አንዳንድ የኢህአዴግ መሪዎችም ጭምር ለህወሓት የበቀል እስርና እርድ የሚታጩበት ልዩ የቁጩ መርሃ ግብር ነው።
በዕለቱ ረቡዕ መስከረም 3 ቀን 2004 ዓ. ም. የነ ሚሚ ስብሃቱ ዛሚ ኤፍ ኤም ከህወሓት ደህንነት ጋር ቀጥታ ግንኙነት ብቻ ሳይሆን ተልዕኮም ተሰጥቷቸው እንደሚሰሩ ለመጀመሪያ ጊዜ ያረጋገጥኩትም ያኔ ነው። እውነት ለመናገር ልክ የነሱ ውንጀላ ከተጠናቀቀ በኋላ እጅግ በጣም ተሰማኝ፥ ተናደድኩ። ብቻ እንዴት እንደምገልፀው አላውቅም። ምክንያቱም የጋዜጠኝነት ሙያ ለእንዲህ ዓይነት ርካሽ ተግባር ሊውል እንደሚችል በፍፁም ገምቼ አላውቅም ነበርና።
የነ ሚሚ ውንጀላ ከተጠናቀቀ በኋላ በግምት ከ 30 ደቂቃ በኋላ የአንድነት ፓርቲ ኤዲቶሪያል ቦርድ ኃላፊ እና በፓርቲው የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ የበላይ ተጠሪ የነበረው አቶ በላይ ፈቃዱ ይመጣል። አቶ በላይም ሁላችንንም ሰላም ብሎን ስለጋዜጣዋ ዕትም ግርድፍ አስተያየት ( ማበረታቻና እርምት) ሰጥቶ ከአንዱዓለም ጋር ወደ ቢሮ ይገባሉ። ከተወሰኑ ደቂቃዎች በኋላም አንዱዓለምና በላይ ተያይዘው በበላይ መኪና እዛው ቀበና ባለው የአንድነት ዋናው ቢሮ አካባቢ ወደሚገኝ ካፌ ሻይ ቡና ለማለት ይሄዳሉ።
በወቅቱ ሁላችንም በሁኔታው ስለተናደድን ጥሩ ስሜት ላይ ባለመሆናችን የዕለቱን የከሰዓት በኋላ የኤዲቶሪያል ቦርድ ውይይት በይደር ለበነጋታው ሐሙስ አስተላልፈን ነበር። ስለሆነም ስለ ሚሚ ስብሃቱና በወቅቱ ስለወነጀሉ “ጋዜጠኞች” እንዲሁም ስለ ዛሚ የኋላ መረጃ ለመቃረም (በግሌ) ልምድ ወዳላቸውና ወደ ማውቃቸው ሰዎች አመራሁ። ይሁን እንጂ እኔ በወፍ በረር ከማውቀው የተለየ መረጃ አላገኘሁም። ከዛም ስለ ዛሚ ኤፍ ኤም ከኢንተርኔትና ብሮድካስት ባለስልጣን ድረ ገፅ የተሻለ መረጃ ባገኝ ብሞክርም ከማውቀው የተለየና ሚነግረኝን አጣሁ። ከዛም ስልኩ ቀደም ሲል ቢኖረኝም ለመጀመሪያ ጊዜ ደውዬ ላስቸግረው ወደ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ጋር ደወልኩ። ስልኩ ይጠራል አያነሳም። ያው ስራ ላይ ሆኖ ይሆናል በሚል ትንሽ ቆይቼ ደወልኩ፤ ስልኩ ይጠራል አይነሳም። በመጨረሻም ነገ እደውልለታለሁ ብዬ ወደ መኖሪያ ቤቴ አመራሁ።
ከዛም ለቀጣዩ ማክሰኞ ህትመት የሚሆን አዳዲስ መረጃ ከተገኘ በሚል ወደ ተወሰኑ የክፍለ ሀገር የመረጃ ምንጮች ጋር በመደወል ትንሽ ካወጋን በኋላ ሁለቱ በኢንተርኔት የመረጃ ሳጥኔ ውስጥ አዲስ መልዕክት እንደተውልኝ በምንግባባበት ቋንቋ ነገሩኝ። እኔም አመሻሹ ላይ ከቤቴ ሰፈር ካለ የኢንተርኔት ካፌ ደንበኛዬ ጋ እያመራሁ ሳለ አንድ ስልክ ከወንድሜ ተደወለ። አነሳሁ። የት ነህ? አለኝ። እዚሁ ሰፈር ነኝ አልኩት። ከዛም፤ ሰማህ? አለኝ። ምኑን? አልኩት። እነ እስክንድርና አንዱዓለም ታሰሩ፥ ዜናው በኢቴቪ ተለቋል አለኝ። አትቀልድ! ከአንድ ሰዓት በፊት ከአንዱዓለም ጋር ነበርኩ፤ ምንድነው ምታወራው? አልኩት። በቃ አትራቅ ብሎ ስልኩን ዘጋው። ውሽቱን መሰለኝ። ርግጥ ነው ማንም ቢሆን ሊያምን የሚችል አይመስለኝም።
ጋዜጠኛ እስክንድርን በተለይ በ1997 ዓ. ም. ቀውጢ ወቅት የክፍለ ሀገር ኮሌጅ ተማሪና ተመራቂ ብሆንም ሐዋሳ ለግሉ ፕሬስ ንባብና ገበያ እንግዳ አልነበረችም። ያኔ እስክንድርን በስራው አውቀዋለሁ። በዕድሜ ከኛ ላቅ ያሉ የምንግባባቸው አንዳንድ ሰዎች ደግሞ በደንብ በአካል የሚያውቁት ያህል አድናቂዎቹ እንደነበሩ አስታውሳለሁ። የመታሰራቸውን ዜና ያረዳኝ ወንድሜ ደግሞ በተመሳሳይ ዓመት አዲስ አበባ ተማሪና ተመራቂ ብቻ ሳይሆን ያን የጦዘ የተስፋ ፖለቲካና ሚዲያ ከተወሰነ ኩርኩም ጋር ስለቀመሰ ከእኔ በተሻለ እስክንድርን ያውቀዋል። ሲያደንቀውም ሰምቻለሁ። ነገር ግን በአካል የሚተዋወቁ አይመስለኝም። አንዱዓለምን በፖለትካው ተሳትፎው በሚዲያ ያውቀዋል እንጂ በአካል አያውቀውም።
ጋዜጠኛ እስክንድር ምኒልክ፥ አስኳል እና ሳተናው የሚባሉ ጋዜጦችን ለንባብ በማብቃት፥ በጋዜጠኝነት ስራውም ብዙ ዋጋ የከፈለ ሰው ነው። በኢትዮጵያ ፕሬስ ታሪክ በአንድ አገዛዝ ብቻ ተደጋጋሚ በደሎች ከደረሰባችውና ብዙ ዋጋ ከከፈሉ የሀገራችን ጋዜጠኞች ቀዳሚውን ስፍራ ይይዛል። በዛ ላይ ትሁት፥ ሰው አክባሪና ጠንቃቃ ነው። አሳዳጆቹንና አሳሪዎቹን እንኳ ጠንቅቆ ያውቃል፤ ግን ቦታ አይሰጣቸውም። ስለሀገራችን ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና ከእኛ ታሪክና የመንግሥት ምስረታ እጅግ የሚራራቅ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ያላቸው ግን በተሻለ ሁኔታ ቀድመውን ከሄዱ የሌላው ዓለም ሀገሮች ጋር ያለንን ልዩነት ሲያወራ በቁጭት ነው። የጥሩ ስብዕና እና አርዓያ ባለቤት ነው፤እስክንድር።
አንዱዓለም አራጌ፤ ከጥላቻ፥ የበቀልክና ክፋት ፖለቲካ ማርከሻ እና ለእኛ ትውልድ መሪ ቢሆኑ ብዬ ከምመኛቸውና ከማውቃችው እጅግ ጥቂት ግለሰቦች አንዱዓለም አራጌ ዋነኛው ነው። መልካምነቱን፥ ቅንነቱን፥ ለሰዎች ያለውን አክብሮትና ፍቅር፥ ታታሪነቱን፥ብቃቱን፥ ለሀገርና ለወገን ያለውን ፍቅር እና መልካም ስብዕናውን በቅርብ አውቃለሁ። ህልሙን እና ፍላጎቱንም አይደብቅም። ሲብዛም ግልፅ ነው።
በጣም የሚገርመው አንዱዓለም በብዙ ነገር መልካም አርዓያ ነው። አንዱዓለም ከማንበብ በስተቀር ከማንኛውም ጎጂ ደባል ሱስ ነፃ ነው። በዚህ ሁሉ እደመማለሁ። ውሸትና ማስመሰል ደግሞ አይታይበትም። ሲበዛ የዋህ ነው። በየዋህነቱና በቅንነቱም በግፍ ከመታሰሩ በተጨማሪ በሌሎች ክፉዎች ወጥመድ ውስጥ ሁሉ ገብቶ እንደነበር አስታውሳለሁ (ይሄንን ከለውጥ በኋላ ጊዜ ሲደርስ እነግራችኋለው)። ይሄንንም ለምቀርባቸው ብቻ ሳይሆን እንደው በሀገራችን ፖለቲካ ዙሪያ ወሬ ከገረብን እና በመሪዎች ጉዳይ ሲወራ አንዱዓለምን በመልካም ምሳሌነት አነሳዋለሁ። ዛሬም ቢሆን እንዲሁ። ያንን ወንድሜ ያቃል። ስለዚህ ወንድሜ እንዴት ሰላማዊና መልካም አርዓያ የሆኑ ሰዎችን በተመለከተ መጥፎ የውሸት መርዶ ይነግረኛል? የሚል ጥርጣሬ አሳደረብኝ። እንዲህ ዓይነት ቀልድ ደግሞ ደስ አይልም፤ ያው ቀልድ ስለመሰለኝ።
ከዛ ወዲያው ወደ አንዱዓለም ጋር ስልክ ደወልኩ፤ ስልኩ ይጠራል ግን አይነሳም። በተደጋጋሚ ደወልኩ አይነሳም። እስክንድርም ጋር ደወልኩ አይነሳም። ዛሬ የምን ነጃሳ ቀን ነው እያልኩ ጥሩ ባልሆነ ስሜት ወደ ደንበኛዬ ኢንተርኔት ካፌ ደረስኩ። እሱም ዜናውን ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ተለቆ ሰምቶ ኖሯል ተናዷል፥ በጣም ተከፍቷል። እነኝህ ጅቦች አሰሯቸው አይደል? አለኝ፤ ገና ከመግባቴ። አሁንም ኢንተርኔት ከፍቼ እስካይ አላመንኩም። ብቻ የንዴት ስሜቴ እየናረ ሄደ። ወንበር ሳብኩና በተረበሸ ስሜት ጥግ ወዳለችው ኮምፒዩተር መነካካት ጀመርኩ። ስድስት ኪሎ ያለ አንድ የቅርብ ወዳጄ የእስሩን የመርዶ ዜና ከቁጭት ጋር አጋርቶ አየሁ። ደነገጥኩ። ማመን አልቻልኩም። ከዛ ገለልተኛ የሚዲያ ወግ ከሚናፍቀው ኢቴቪ የተጋራውን ዜና ሰማሁ። በጣም ስሜታዊ ነበርኩ፤ነኝም። የንዴትና ቁጭት ለቅሶ ፈንቅሎ ወጣ። ቀደም ሲል የክፍለ ሀገር መረጃዎችን ለማየትና ለመገረብ ከቤት ብወጣም በሰዓቱ እነኛን መረጃዎች ማየት አልፈለኩም። ጭራሽ ሌላ በርካታ መልዕክቶች እንደተላኩ የመረጃ ሳጥኔ ያሳየኛል። እኔ ግን በዛ ስሜት ውስጥ ሌላ መረጃ ማየትም ሆነ ማጋራት አልፈለኩም። በምን ስሜት? ከዛም በርካታ የስልክ ጥሪዎች መጡ ማንሳት አስጠላኝ።
የኢንተርኔት ካፌው ባለቤት ረዳት ሆና ምትሰራው ልጅ ስሜታችን ግራ ቢገባት በተሸማቀቀ የፍርሃት ስሜት ታየናለች። ባለቤቱም በሁኔታው ስለተናደደ ያለወትሮው ከአምስት ደቂቃ በኋላ ቤቱን ስለሚዘጋ ሌሎች መደበኛ ደንበኞቹ ቶሎ ጨርሰው እንዲወጡ ትብብር ይጠይቃቸዋል። ሰራተኛዋንም ነገ በስራ ሰዓቷ እንድትመጣና በወቅቱ ወደ ቤቷ መሄድ እንደምትችል ይነግራታል። እኔና እሱ ብቻ ቀረን፤ በንዴትና ቁጭት ስሜት ውስጥ …. ። ትንሽ ካወራን በኋላ ኢንተርኔት ካፌውን ዘግተን ሁለታችንም ወደየቤታችን ሄድን። ቤት ስገባም በምሽት ድጋሚ ዜናውንና ድራማውን አየሁ። ህልም ሁሉ መሰለኝ። ምክንያቱም ለእንዲህ ዓይነት የጭካኔ ድራማ ምልከታ ገና እንግዳ ነበርኩና።
ለካ የዛን ዕለት እነ ሚሚ ስብሃቱ “በጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ” መርሃ ግብራቸው ሲነግሩን የነበረው በህወሓት ደህንነት የታቀደና ያለቀ የእስር መርዶ ነበር፤ ወይ አለማወቅ!?
በዕለቱ እስክንድር ልጁ ናፍቆትን በራሱ መኪና ሰላም ባይኖርም፤ እንደወትሮው ሀገር አማን ብሎ ልጁን ከትምህርት ቤት ወደ መኖሪያ ቤቱ ይዞት እየመጣ ሳለ በበርካታ ፖሊሶች፥ የደህንነት ባልደረቦችና የህወሓት ካሜራማኖች ተደርድረው መንገድ ላይ ያውም አደባባይ ላይ እንደወንጀለኛ አስቁመው የያዙት። ምን ይሄ ብቻ፤ በህፃን ልጁ ፊት እጆቹን በካቴና አስረው ነው ያንገላቱት። በወቅቱ በስፍራው የነበሩ እንደነገሩኝ ከሆነ በህወሓት የወንጀል ድራማ ልጁ ናፍቆት ተደናግጦ አምርሮ ሲያልቅስ እንደታዘቡ በሀዘን አጫውተውኛል። ተመልከቱ! በሚያድግ ህፃን ልጅ ፊት እንደዛ ያለ ነውር ነው የፈፀሙት።
ያኔ የህፃን ኖላዊ እና ሩህ አባት አንዱዓለም አራጌ እና የህፃን ናፍቆት አባት ጋዜጠኛ እስክንድር በግፍ ታሰሩ። ባልዋሉብት፥ በሚጠሉትና በሚታገሉት መንግሥታዊ ሽብር ጭራሽ ተወነጀሉበት። ከዚያም የግንቦት 7 አባል ናችሁ ተብለው ፤ ጋዜጠኛ እስክንድር ላይ 18 ዓመት፥ አቶ አንዱዓለም አራጌ ላይ ደግሞ ዕድሜ ልክ ፈረዱባቸው።
በነገራችን ላይ በተመሳሳይ ክስ በዛው ቀን እዛው አዲስ አበባ ከእስክንድርና አንዱዓለም በተጨማሪ ከአንድነት ፓርቲ መምህር ናትናኤል መኮንን እና አሳምነው ብርሃኑ፤ ከመኢዴፓ አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ) እና አቶ ዘመኑ ሞላ ታስረው ነበር። ከክፍለ ሀገር ደግሞ የአንድነት ፓርቲ አመራር የነበሩት ሻምበል የሺዋስ ይሁንዓለም፥ አቶ ዮሐንስ ተረፈ፥ እና አቶ ሻማ ነበሩበት። ይሁን እንጂ አቶ አሳምነው ብርሃኑ፥ ዘመኑ ሞላ እና አቶ ሻማ (የቤተ እስራኤል ማኅበረሰብ አባል እንደሆነ እና ወደ እስራኤል ለመሄድ ጉዞ ዝግጅት ላይ እያለ የታሰረ) አብረዋቸው በታሰሩት ላይ በግድ እንዲመሰክሩ ተደርገው ተለቀዋል።
የአንድነቱ መምህር ናትናኤል መኮንን አቶ አንዱዓለም አራጌ ላይ በሐሰት ” የግንቦት 7 አመራር ነው፥ ተዕልኮ ሰጥቶች ሀገር ልናሸብርን ተነጋግረን ወስነናል በል” ተብሎ ልክ እንደ አቶ አሳምነው ብርሃኑ መስክሮ እንዲወጣ ተደጋጋሚ ማስፈራሪያ፥ ድብደባና ዛቻ ደርሶበታል። ይሄንንም በተደጋጋሚ ፍርድ ቤት ችሎት ላይ ቢያመለክትም ሲመለሰ ከበፊት በከፋ መልኩ ተደብድቧል፥ ለ21 ቀናትም ራቁቱን ውጭ ላይ ቀዝቃዛ ውሃ እየተደፋበት ተገርፏል፥ ብዙ ስቃይ ደርሶበታል። ግን እንዳሉት በሐሰት ለመመስከር ፈቃደኛ ሳይሆን በመቅረቱ 25 ዓመት እስር ፈርደውበት እዛው ወህኒ ቤት ይገኛል። መምህር ናትናኤል ደግሞ ከስራ ወደቤቱ በአምበሳ የከተማ አውቶቡስ ውስጥ ከስራ ወደቤቱ ሲያመራ ነው በፖሊሶች መኪና ከበባ ተሳፋሪው በሙሉ ታግቶ ተይዞ የታሰረው።
አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ የአሁኑ እስርና ስቃይ ብቻ ሳይሆን ከዚህ በፊት ልክ እንደሌሎቹ ብዙ ስቃይ እንደደረሰበት ፍርድ ቤት ተናግሯል። ስለሱ ማውቅ የሚፈልጉ የበለጠ የኤርምያስ ለገሰ “የመለስ ትሩፋቶችና ባለቤት አልባ ከተማ” የሚለው መፅሐፍ ላይ የተወሰነ ነገር ያገኛሉ። ሌላው ክንፈሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ) በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በሚያስብል ድፍረት ንጉስን በመፈንቅለ መንግሥት ለመጣል ሙከራ አድርገው የከሸፈባችውና አርዓያ የነበሩት የወንድማማቾቹ የነ ጀነራል መንግሥቱ ነዋይ እና አቶ ግርማሜ ነዋይ የቅርብ የሥጋ ዘመድም ነው።
በሙያው የሶስት ዓለም አቀፍ የፕሬስ ሽልማቶች ባለቤት የሆነው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ከዚህ በፊት 7 ጊዜ ታስሮና ቶርቸር ተደርጎ የተለቀቀ ሲሆን፤ አሁን 7ኛ ዓመቱን እስር ላይ እያሳለፈ ያለው ለ8ኛ ጊዜ ከታሰረ በኋላ ነው። አቶ አንዱዓለም አራጌ ደግሞ በ1997 ዓ ም በነበረው ምርጫ ግርግር ከወቅቱ የቅንጅት አመራሮች ጋር ታስሮ በተመሳሳይ ዕድሜ ልክ ፈርደውበት ነበር። ከሁለት ዓመት በኋላም ከሌሎች የቅንጅት አመራሮችና ጋዜጠኞች ጋር ከተለቀቀ በኋላ ነው ድጋሚ የታሰረው።
አሳዛኙ ነገር፤ ” መንግሥት” በቅርቡ በሀገሪቱ ህዝብና በዓለም አቀፍ ምኅበረሰብና ተቋማት በደረሰበት ጫና የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞችን እንደሚፈታ ቃል ገብቶ ነበር። ይህንንም ተከትሎ ባለፈው አንጋፍውን የኦፌኮ/መድረክ ፓርቲ አመራር ዶ/ር መረራ ጉዲናን ጨምሮ በርካታ ዜጎችን ከእስር መልቀቁ ይታወቃል።
ሰሞኑን ደግሞ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና አንዱዓለም አራጌን ጨምሮ የቀሩ በርካታ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች በቅርቡ እንደሚፈቱ ይፋ አድርጓል። መንግሥት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፥ አቶ አንዱዓለም አራጌ፥ አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ ባልተቀበሉት፥ በተከሰሱአበትና በተፈረደባችው ክስ ” የግንቦት 7 አባልና አመራር ነበርኩ፥ በፈፀምኩት የሽብር ተግባር ተፀፅቻለሁ፥ መንግሥትንና ህዝቡን ይቅርታ እጠይቃለሁ” ብላችሁ ፈርሙና ውጡ ማለቱ ተሰምቷል። ይሁን እንጂ የመንግሥት የወንጀል ይቅርታ ጥያቄው በነ እስክንድር ተቀባይነትን ሊያገኝ አልቻለም።
በእስር ያሉ የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎችም በተመሳሳይ ጥያቄ ” በፈፀምነው የሽብር ተግባር ተፀፅተናል፥ መንግሥትና ህዝቡን ይቅርታ እንጠይቃለን” ብላችሁ ፈርሙና ውጡ የሚለው የመንግሥት ተማፅኖ ተቀባይነት አላገኘም። ይፈታሉ ከተባሉ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች በተጨማሪ እነ አቶ በቀለ ገርባ እና አቶ ኦልባና ሌሊሳን ጨምሮ በርካታ ሰዎች አሁንም እስር ላይ እንደሆኑ ይታወቃል።
በርግጥ አንድ እውነት አለ። መንግሥት በደረሰበት ጫና እንጂ ለእስረኞ አዝኖ ወይም እስረኞችን በግፍ ስላሰቃያቸው ተፀፅቶና ርህራሄ ተሰምቶት አይደለም የለቀቃቸውና ሊለቃቸው የፈለገው። አሁን ያለው የሀገር ውስጥ የፖለቲካ ድባብ፥ የህዝቡ ዛሬም ያልተቋጨ ትግልና የዓለም አቀፉ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ጫና በርትቶበት እንጂ። ስለዚህ መንግሥት ጊዜ ያለፈበትን የፖለቲካ መቆመሪያ ቅድመ ሁኔታ ትቶ ሁሉንም በሚባል ደረጃ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች የመለቀቁ ጉዳይ ቀጥይ እንደሚሆን ይገመታል። ከለው ተለዋዋጭ የሀገሪቱ የፖለቲካ ትኩሳት አኳያ ከህሊና እስረኞች መለቀቅ በኋላስ የሚለውን የሀገሪቱ የፖለቲካ ሁኔታ በተመለከተ ያው ጊዜ ይፈተዋል ከማለት ውጭ መተንበይ አስችጋሪ ነው።
President’s office requests list of convicted, charged political party leaders
By Tamiru Tsige
Photo: The governor EPRDF Chairmen’s
The Office of the President requested the Federal Prisons Administration and the Federal Attorney General respectively to provide it with a list of political party members and leaders who are eligible for pardon as well as political party leaders and members currently on trial, The Reporter learnt.
According to sources close to the matter, the President’s Office is due to receive the lists within two days.
It is to be remembered that, in a joint briefing they gave to the Ethiopian Broadcasting Corporation (EBC) and Ethiopian News Agency (ENA) yesterday, the leadership of the four member parties of the EPRDF announced that opposition party members and leaders will be released and that charges against those undergoing trial will be withdrawn.
The infamous detention and investigation center also known as “Maekelawi” was also said to be closed and converted to a modern museum.
Source: Reporter