Tag Archives: Journalist Woubshet Taye

ጋዜጠኛ እስክንድር እና ውብሸት ታዬ ከእስር ተለቀቁ

ላለፉት 6 ዓመት ከ6 ወራት በእስር ላይ የነበሩት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ዛሬ የካቲት 7 ቀን 2010 ዓ ም ከእስር ተለቀዋል።

Journalist Eskinder, Woubshet and Zelalem
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፥ ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ እና ጦማሪ ዘለዓለም ወርቅአገኝሁ

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በመንግሥት በቀረበበት ክስ የ18 ዓመት እስርት ተፈርዶበት የነበረ ቢሆንም፤ ጋዜጠኛ እስክንድር የፔን አሜሪካ “Freedom to write Award” እና የዓለም አቀፍ የፕሬስ ተቋምን “World press freedom Hero” የሚሉ ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን ማግኘቱ ይታወሳል። ከእስር እንደተፈታም ህዝቡ ላደረገለት ድጋፍና አቀባብል አመስግኗል።

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በቀረበበክ ክስ 14 ዓመት እስር ተፈርዶበት የነበረ ሲሆን፤ እ. አ. አ. የ213 ዓለም አቀፍ የአፍሪካ ንፃ ፕሬስ “African free press Award” አሽናፊ ሲሆን በእስር ቤት ሳለ ሁለት መፅሐፍትን ለንባብ ማብቃቱ ይታወቃል።

ባለፈው ደብርሃን ድረ ገፅ ጦማሪ ዘለዓለም ወርቅአገኘሁ ባለፈው ጥር 21 ቀን 2010 ዓ.ም. የተበየነበት እስር በአመክሮ በማጠናቀቅ ከእስር የተፈታ ሲሆን፤ ክሳቸው በአቃቤ ህግ ይግባኝ እየታየ የነበሩት የዞን 9 ጦማሪያን ክስም ዛሬ እንዲቋረጥ መደረጉ ታውቋል።

%d bloggers like this: