በኦሮሚያ ክልል በተካሄዱ ተቃውሞዎች 67 ሰዎች ተገደሉ
ግጭቱ ከክልሉ አቅም በላይ በመሆኑ የመከላከያ ሠራዊት ተሰማርቷል
የኦኤምኤን ቴሌቪዥን ጣቢያ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጃዋር መሐመድ የተመደበለት ጥበቃ እንዲነሳ በመባሉ በተቀሰቀሰ ውዝግብ፣ በኦሮሚያ ክልል በተካሄዱ ተቃውሞዎች የሞቱ ሰዎች ቁጥር 67 መድረሱ ተረጋገጠ፡፡ በአንዳንድ አካባቢዎች ሃይማኖታዊና ብሔር ተኮር ጥቃቶች ተፈጽመዋል፡፡
የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ዓርብ ጥቅምት 14 ቀን እንዳስታወቀው በክልሉ በተቀሰቀሱ ተቃውሞዎች 67 ሰዎች ተገድለዋል፡፡ ከተገደሉት ውስጥ 13 ያህሉ በጥይት፣ ቀሪዎቹ ደግሞ በተፈጸመባቸው ጥቃት ሕይወታቸው ማለፉን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል፡፡ ከተገደሉት መካከል አምስቱ የፖሊስ ባልደረቦች እንደሆኑ ኮሚሽኑ አስታውቋል፡፡
የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ይህንን ቢልም ጉዳት በደረሰባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ ሰዎች የተገደሉት ሰዎች ቁጥር ሊጨምር ይችላል እያሉ ነው፡፡ በአንዳንድ ሥፍራዎች የተፈጸሙት ጥቃቶች ሃይማኖታዊና ብሔር ተኮር በመሆናቸው ሳቢያ በርካቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው ተናግረዋል፡፡
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመንግሥታቸው የበጀት ዓመቱ ዕቅዶችና በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራርያ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) የውጭ ዜግነት ያላቸው የሚዲያ ባለቤቶች ጥላቻና ግጭትን ከሚቀሰቅሱ ሥራዎች ካልተቆጠቡ፣ መንግሥት ዕርምጃ እንደሚወስድ ማክሰኞ ጥቅምት 11 ቀን 2012 ዓ.ም. ማስታወቃቸው ይታወሳል፡፡
የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማስጠንቀቂያ በጥቅሉ የተነገረ ቢሆንም ጃዋር የውጭ ዜግነት ያለው ትውልደ ኢትዮጵያዊ የፖለቲካ አክቲቪስትና የሚዲያ ባለቤት መሆኑ፣ ራሱን ጨምሮ በርካቶች የጠቅላይ ሚኒስትሩ ማስጠንቀቂያ በዋናነት እሱን የሚመለከት አድርገው ተገንዝበውት ነበር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህንን ማስጠንቀቂያ ባስተላለፉበት ዕለት አመሻሽይ ላይ ወደ ሩሲያ ተጉዘዋል፡፡ ነገር ግን በዚያው ዕለት ዕኩለ ሌሊት ለጃዋር ደኅንነት ጥበቃ እንዲያደርጉ በመንግሥት የተመደቡ ጥበቃዎች፣ በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ አካባቢ ከሚገኘው መኖሪያ ቤት ሥራቸውን አቋርጠው እንዲወጡ ታዘዋል በመባሉ ምክንያት አለመግባባት ተፈጥሯል፡፡
የጥበቃ አገልግሎቱ ተገቢ ባልሆነ ሰዓትና እሱ ሳያውቅ እንዲነሳ ትዕዛዝ ተላልፏል በመባሉ በጃዋር ላይ ሥጋት መፍጠሩንና ለዚህም ተጨባጭ ምክንያት ከመንግሥት ኃላፊዎች ማግኘት አለመቻሉን በመግለጽ፣ ከ1.7 ሚሊዮን በላይ ተከታዮችን ባፈራበት የማኅበራዊ ትስስር ገጽ ላይ በዚያው ሌሊት ይፋ እንዲያደርግ እንዳስገደደው ራሱ ተናግሯል፡፡
ይህንንም ተከትሎ ከጃዋር መኖሪያ ቅርብ ከሆኑ አካባቢዎች ደጋፊዎቹ ሌሊቱን ተጉዘው በሥፍራው የደረሱ ሲሆን፣ እሱ ይፋ ያደረገው መረጃም ስሜትና ጥርጣሬን እየቀላቀለ ሌሊቱን ሲሰራጭ አድሮ ‹‹ቄሮ›› በሚባል መጠሪያ የሚታወቁ ወጣቶች በማግሥቱ በበርካታ የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ለተቃውሞ እንዲወጡ፣ ተቃውሟቸውንም መንገድ በመዝጋትና እንቅስቃሴዎችን በማስተጓጎል እንዲገልጹ አድርጓቸዋል፡፡ ተቃውሞውም እየተስፋፋ በርካታ ሥፍራዎችን አዳርሷል፡፡
ጃዋር የተመደቡለት የጥበቃ ሰዎች በዕኩለ ሌሊት እንዲነሱና ጥበቃው እንዲቋረጥ መንግሥት አድርጓል ያለውን ድርጊት ‹‹የግድያ ሙከራ›› እንደሆነ፣ ሌሎች ፖለቲካዊ ምክንያቶችንም በማያያዝ በማግሥቱ ጠዋት በራሱ ሚዲያ (ኦኤምኤን) እና በሌሎች ሚዲያዎች እንዲገለጽ አድርጓል፡፡
በመሆኑም ረቡዕ ጥቅምት 12 ቀን 2012 ዓ.ም. ማለዳ በአዲስ አበባ ዙሪያ ባሉ የኦሮሚያ ከተሞች የተጀመረው ተቃውሞ፣ በበርካታ የኦሮሚያ ከተሞችም ተስፋፍቶ ቀጥሏል፡፡ ተቃውሞው መንገድ ከመዝጋትና የተባለውን ድርጊት ከማውገዝ አልፎ በመሄድ ገጽታውን በመቀየር ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማኅበራዊ መሠረታቸው በሆነው የኦሮሞ ሕዝብ ላይ ክህደት እንደፈጸሙ፣ እንዲሁም የኦሮሞ ሕዝብ ትግል ጥያቄዎች እንዳይመለሱ አድርገዋል የሚሉ ውግዘቶች ተስታጋብቶባቸዋል፡፡ በቅርቡ ያሳተሙት ‹‹መደመር›› የተሰኘው መጽሐፋቸውና ባነሮች እንዲቃጠሉ ተደርገዋል፡፡ የተቃውሞ ሠልፎቹ በተካሄዱባቸው አንዳንድ አካባዎች ለአብነትም በተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ የሌላ ብሔር ተወላጆችና የጃዋር ደጋፊዎች በመጋጨታቸው፣ የበርካታ ሰዎች ሕይወት እንዲቀጠፍ ምክንያት ሆኗል፡፡
የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነር እንደሻው ጣሰው በጃዋር ላይ ምንም ዓይነት የግድያ ሙከራ አለመቃጣቱን፣ ግለሰቡም በሥራው ላይ እንደሚገኝ ረቡዕ ቀትር ላይ በመግለጽ ለማረጋጋት ጥረት አድርገው ነበር፡፡
ለጃዋርም ሆነ ከውጭ ለገቡ ተፅዕኖ ፈጣሪ ፖለቲከኞች መንግሥት መድቦ የነበረውን የጥበቃ አገልግሎት በአገሪቱ በተፈጠረው አንፃራዊ ሰላም ምክንያት በማቋረጥ ላይ እንደነበር የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽነሩ ተናግረዋል፡፡ ረቡዕ ጠዋት የተጀመረው ተቃውሞ ከቀትር በኋላም እየተስፋፋ በርካታ የኦሮሚያ ከተሞችን በግጭት ሲንጥ ውሏል፡፡
ተቃውሞዎቹ በአንዳንድ አካባቢዎች ሃይማኖታዊና የብሔር ግጭት መልክ በመያዛቸው፣ ከቁጥጥር ውጭ መሆናቸውንና የፀጥታ አስከባሪዎችም ክስተቱን ለመቆጣጠር ኃይል ወደ መጠቀም እንዲገቡ ማስገደዱን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በዚህም ምክንያት ረቡዕ ዕለት በአምቦ ሦስት ሰዎች፣ በምሥራቅ ሐረርጌ አንድ መገደላቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚሁ ቀን በአዳማ ከተማ በሚገኝ አንድ ዱቄት ፋብሪካ ላይ ጥቃት ለማድረስ ሙከራ አድርገዋል በተባሉ ተቃዋሚዎች ላይ የፋብሪካው የጥበቃ ሠራተኛ ተኩስ በመክፈት ሁለት ሠልፈኞችን በመግደላቸው ምክንያት ተቃውሞው ማየሉን፣ በዚህም ሳቢያ የፋብሪካው የጥበቃ ሠራተኛ በሠልፈኞቹ ሲገደሉ፣ በፋብሪካው ቅጥር ግቢ የነበሩ 15 ተሽከርካሪዎች መውደማቸውም ታውቋል፡፡ በተመሳሳይ በድሬዳዋ ከተማ አራት ሰዎች መገደላቸውንም የተገኘው መረጃ ያመለክታል፡፡ በድሬዳዋና በሐረር ከተሞች በነጋታው በተፈጸሙ ጥቃቶች በርካቶች እንደተገደሉ የዓይን እማኞች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ጥቃቶቹም በጣም አስፈሪ እንደነበሩ አክለዋል፡፡
የኦሮሚያ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ረቡዕ አመሻሽ ላይ በሰጡት መግለጫ፣ የክልሉ ሕዝብ እንዲረጋጋ ጥሪ በማቅረብ የጃዋር ጥበቃዎችን ለማንሳት የተሄደበት መንገድ አግባብነት እንደሌለው ተናግረዋል፡፡
አክለውም ተቃውሞው ሌላ መልክ እንዲይዝ በማድረግ ክልሉን ለመረበሽ ዓላማ ያላቸው ኃይሎች መኖራቸውን በመግለጽ፣ የክልሉ መንግሥት በእነዚህ ላይ አስፈላጊውን ዕርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቀዋል፡፡
ይሁን እንጂ ተቃውሞውንና ግጭቱን በማግሥቱም መቆጣጠር አልተቻለም፡፡ በማግሥቱ ሐሙስ ግጭቶቹ ተጠናክረው የቀጠሉ ሲሆን፣ በተለይም በመጀመርያው ቀን የነበረውን ተቃውሞ ለማስተጓጎል ሞክረዋል የተባሉ የማኅበረሰብ ክፍሎችን ማንነት በመለየት ጥቃት ወደ መሰንዘር እንደተገባ ታውቋል፡፡
የዓይን እማኞች በምዕራብ ኦሮሚያ ወለቴ በተባለ አካባቢ የመጀመርያ ቀን ተቃውሞውን የማስተጓጎል ሙከራ አድርገዋል የተባሉ የሌላ ብሔረሰብ ተወላጆችን በየመኖሪያቸው በመግባት ጥቃት መሰንዘሩን ተናግረዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በአንድ ያላለቀ ሕንፃ ላይ በጋራ ከሚኖሩ ሰዎች መካከል ሴቶቹን በመለየት፣ ወንዶቹን ከመኖሪያቻው በማውጣት ጥቃት ያደረሱባቸው መሆኑንና ጥቃት ከደረሰባቸው መካከልም ስድስት የሚሆኑት መገደላቸውን የዓይን እማኞች አስረድተዋል፡፡ በአምቦም እንደዚሁ ሰዎች ሞተዋል፡፡
በምሥራቅ ሐረርጌም ተመሳሳይ ጥቃት ሊደርስባቸው የነበሩ አንድ ግለሰብ በጦር መሥሪያ ራሳቸውን ለመከላከል ባደረጉት ሙከራ ጥቃት ሊያደርሱባቸው ከመጡት መካከል ሁለት ሰዎች መግደላቸውን፣ ይህንንም ተከትሎ ግለሰቡ ከሥፍራው ቢያመልጡም በባለቤታቸው ላይ በተፈጸመ ግድያ እንዲሁም በሌሎች ሁለት ሰዎች ላይ በተፈጸመ ጥቃት በድምሩ አምስት የአካባቢው ነዋሪዎች መገደላቸውን የአካባቢው ሰዎች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ ዶዶላ አካባቢ ለተቃውሞ የወጡ ወጣቶች ብሔርና ሃይማኖት ለይተው በማጥቃት ድርጊት ውስጥ በመግባታቸው አራት ሰዎች እንደተገደሉ ተሰምቷል፡፡
በሁለቱ ቀናት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን ሪፖርተር ግጭቶቹ ከተቀሰቀሱባቸው አካባቢዎች ነዋሪዎች ያሰባሰበው መረጃ ያመለክታል፡፡ የሟቾችን ቁጥር በተመለከተ የተለያዩ አኃዞች እየተሰሙ ቢሆንም፣ ከገለልተኛ አካላት ትክክለኛውን ቁጥር ማረጋገጥ አልተቻለም፡፡ ሐሙስ ከቀትር በኋላ ጃዋር ከተለያዩ የኦሮሞ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር በመሆን በሰጠው መግለጫ፣ በተካሄዱት ተቃውሞዎች በቂ መልዕክት መተላለፉን በመግለጽ ተከታዮቹም ሆኑ ሌሎች የኦሮሞ ማኅበረሰቦች ተቃውሟቸውን በመግታት እንዲረጋጉ በኦኤምኤን ማሳሰቢያ ሰጥቷል፡፡ በተለይ ዶዶላ አካባቢ የከፋ ጥቃት ሲፈጸም እንደነበር ታውቋል፡፡ የተገደሉ ሰዎችን አስከሬን ለመቅበር የተቸገሩ ሰዎች ለመንግሥት አካላት የድረሱልን ጥሪ ሲያሰሙ ነበር፡፡ ቤቶቻቸው የተቃጠሉባቸው ሰዎችም እንዲሁ ድረሱልን ሲሉ ነበር፡፡
ይህንን ተከትሎ መለስተኛ መረጋጋት ዓርብ ዕለት ቢስተዋልም ውጥረቱ እንዳየለ ነበር፡፡ ዓርብ ዕለት የመከላከያ ሠራዊቱ በሰጠው መግለጫ የክልሉ መንግሥት ግጭቱን ለመቆጣጠር ከአቅም በላይ እንደሆነበት በመግለጽ፣ የፌደራል መንግሥትን ድጋፍ በመጠየቁ መንግሥት ሠራዊቱ ችግር በተፈጠረባቸው አካባቢዎች እንዲሰማራ መወሰኑን አመልክቷል፡፡
የመከላከያ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነትና ኢንዶክትሪኔሽን ዳይሬክተር ሜጀር ጄነራል መሐመድ ተሰማ በሰጡት መግለጫ፣ ሠራዊቱ ወደ ክልሉ በመግባት ግጭቱን እንዲቆጣጠር ከመንግሥት በተሰጠው መመርያ መሰማራቱን አረጋግጠዋል፡፡
በዚህም መሠረት አዳማ፣ ቢሾፍቱ፣ ድሬዳዋ፣ ባሌ፣ ዶዶላ፣ አሰላ፣ ኮፈሌ፣ አምቦ፣ ሻሸመኔ፣ ሞጆና በሐረር ሠራዊቱ ከተሰማራባቸው መካከል መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡
በተፈጠረው ግጭት ለጠፋው የሰው ሕይወትና የንብረት ውድመት ተጠያቂ ስለሆኑ አካላት ግን፣ ለኅትመት እስከ ገባንበት ቅዳሜ እኩለ ቀን ድረስ በመንግሥት በኩል የተባለ ነገር የለም፡፡ ብዙዎች ግን የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ መንግሥትን ዕርምጃ እየጠበቁ ነበር፡፡
Source: ሪፓርተር
Censorship and Hate Speech in Ethiopia
By Bisrat Woldemichael
Freedom of speech does not mean hate speech to use for insulting or attacking anyone. Hate speech is any kind of communication in speech, writing or behaviour, that denigrates or insults a person or a group on the basis of who they are, in other words, based on their religion, ethnicity, nationality, race or another identity factor. Hate speech may suggest that the person or group—it is usually groups—is inferior and that they should be excluded or discriminated against on this basis including, for example, by limiting their access to resources, education, employment or political positions.[10]
The hate speech has a contribution to creating conflicts between individuals, the societies, the movement, between the states. The objectives of hate speeches are to attack, insult, marginalize or expose innocent individuals and civilian for personal egoistic interest than the public. The haters are negative thinkers those who are searching or finding the dark point from the bright sky. Once the free mind colonized by hate speech, it is difficult to manage easily because it has already corrupted the haters’ fellow mind. Perhaps they could not find anything for their hate purpose, then they create a false flag for conflicts to attack the exposed target individuals or social groups. Moreover, all incitement to discrimination, hostility or violence is hate speech, not all hate speech constitutes incitement.[11]
It has contributions to social crises, conflicts, genocide, and political instability. For example between 1941 to 1945 the Germany Nazi party of Hitler’s irresponsible hate speech abused his fellow leaders, soldiers and Nazi party members, the 17 million targeted people, including 6 million European Jewish were killed.[12] In Rwanda, 1994, the irresponsible leaders and journalists promulgated hate speech through media, such as Kangura newspaper, the Radio Rwanda, Echo des 1000 Collines, and The station Radio-Télévision Libre des Milles Collines (RTLM) promoted hate speech in Rwanda.[13] In addition, some of songwriters and singers; Simon Bikindi, Nanga Abahutu and Bene Sebahinzi contributed to inflammatory fuel for such horrible genocide.[14] As a result, they created conflicts between ethnics’ groups, mainly Hutu and Tutsi, then more than 800 thousand civilians killed, and 2 million people displaced within a short period of time. Similarly, hate speech affected Kenyan, Bosnia and Guatemala societies.
In Ethiopia, since the 1960’s revolution, hate speeches are highly grew up by irresponsible political activists, radical groups and their leaders entire the country. The haters gave negative attitudes and bad images for a specific social group, with lots of pseudo-stories to use for mobilizing their supporters for political interest. In addition, the haters gave code name for specific ethnic groups and religion followers. Their members and supporters accepted as a truth, then published and broadcasting hate speeches repeatedly. Finally, in May 1991 those political groups took the government office, but they continue their hate speech as an ordinary word until April 2018. The ruling party, EPRDF and its coalition members and affiliated groups’ constituents are not free from hate speeches. In addition to promoting hate speech to discriminating, insulting some specific social groups who are categorized by political elites and activists. Some of the opposition groups did the same thing to react to the ruling party attitude. All these imprudent political traditions have been expanded entire the country.
The New prime minister, Abiy Ahmed boldly changed this negative attitude of state-sponsored hate speech and criminalizing targeted social groups and political organizations. This is a good opportunity for all actors those who want to exercise their democratic rights to involve in a genuine political activity. Unlikely, some of the activists and political leaders manoeuvre hate speech as a tactic for their selfishness demand. Gradually, hate speeches are dramatically increased both in mainstream and social media. As a result, many civilians, including children and women have been killed, more than 2 million people internally displaced.[15] Therefore, hate speeches have a contribution to creating social conflicts, which are orchestrated by activists, and the local leaders. Of course, some of the ruling party leaders and the radical groups are committed for local displacement and ethnic cleansing.
Today, social media are very important to disseminate information, knowledge and make social life. The proper use of social media platform is important to help to exercise freedom of speech and citizen journalism. On the other hand, some people misuse the platform for insulting or harassing individuals or some social groups. Yet, hate speech promoters and sponsors are not accountable for such public damages. Hate speech is using an instrument for dictators and idealess activists to mobilise their supporters, then leads to taking immediate reactions to limit freedom of speech. In Ethiopia, hate speeches highly spreading by mainstream media and social media as well. Ethnic-based private owned and regional state media promoting hate speech against of pro-Ethiopian unity groups commonly insulting, attacking and discriminating with the words, “homeless, settlers, …”
In social media, the ruling party had experiences to organize the activists in the name of “Social media soldiers” under fake name those who were promoted hate speech, and to share distorted information for diverting and controlling social media. Similarly, some of the diaspora based ethno-nationalist activists and haters have the same experiences to react the ruling party and the other counterpart. Currently, the country is under political reform, however, both of them are continuing in the same way to create a false flag, promoting hate speech and social grievance. It has an impact on freedom of expressions and press freedom as well. Unless to manage the hate speeches, the country reform will be faced by social crises and political instability. Otherwise, the hate speech determines the fate of freedom of expression and press freedom sustainability in general.
[1]The World Bank Group (2017) Ethiopia, [Online], accessed April 25, 2019, available at https://data.worldbank.org/country/ethiopia.
[2]CSA (2017) Population projections [Online], accessed April 25, 2019.
[3]World Justice project (2019) Global rule of Law Index, 1025 Vermont Avenue, NW, Suite 1200, Washington, DC 20005 USA, available at https://worldjusticeproject.org/sites/default/files/documents/WJP_Ruleo… Website_reduced.pdf.
[4]UN (2015) Universal declaration of human rights, United Nations.
[5]Federal Negarit Gazeta (1995), Federal Democratic Republic of Ethiopia: Constitution ‘proclamation’ no. 1/1995, Berehannena Selam Printing Enterprise, Addis Ababa.
[6]Federal Negarit Gazeta (2009), Anti-terrorism proclamation no.652/2009, Berhannena Selam Printing Enterprise, Addis Ababa.
[7]Sullivan M. K. (2010) Two concepts of freedom of speech, Vol. 124:143, Harvard Law Review.
[8]Dorter K. (1976) Socrates on Life, Death and Suicide, Laval théologique et philosophique, vol. 32, no. 1, p. 23-41.
[9]Amnesty International (2019), Ethiopia: Stop harassing Eskinder Nega for his opinions, [Online], accessed June 18, available at https://www.amnesty.org/en/latest/news/2019/06/ethiopia-stop-harassing-….
[10]Reporters without Border (2019) New era for Ethiopia’s journalists, [Online], accessed April 20, 2019, available at https://rsf.org/en/news/new-era-ethiopias-journalists.
[11]UN (2017) Plan of action for religious leaders and actors to prevent incitement to violence that could lead to atrocity crimes, Genocide prevention document.
[12]Flaim F.R. and Furman H. (2008) The Hitler legacy: A dilemma of hate speech hate crime in a post-holocaust world, (ed.), Trenton, New Jersey, 08625, USA.
[13]Scheffler A. and Pelley M.L. (2015) The Inherent Dangerof Hate Speech Legislation: A Case Study from Rwanda and Kenya on the Failure of a Preventative Measure, fesmedia Africa, Friedrich-Ebert-Stiftung, Namibia.
[14]United States Holocaust museum memorial (None), Hate speech and group-targeted violence, the role of speech in violent conflicts, Washington DC, USA, [Online], accessed April 24, 2019, available at http://www.genocidewatch.org/images/OutsideResearch_Hate_Speech_and_Gro….
[15]Human rights watch (2019) World Report, Ethiopia reports: events of 2018, [Online], accessed April 25, 2019, available at https://www.hrw.org/world-report/2019/country-chapters/ethiopia.
Source: https://www.penopp.org/articles/censorship-and-hate-speech-ethiopia
በከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ላይ ሰኔ 15 የተፈጸመው ግድያ ዓቃቤ ሕግንና ተጠርጣሪዎችን እያወዛገበ ነው
ታምሩ ጽጌ
‹‹ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተቋሙን የማይመጥን ውሳኔ ሰጥቷል››
ተጠርጣሪዎች
‹‹የተወሰኑ ተጠርጣሪዎች በህቡዕ ተደራጅተው ጦርነት ይመሩ ነበር››
ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ
በአማራ ክልል ከፍተኛ አመራሮች፣ በመከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹምና በጓደኛቸው ላይ ሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በተቀራራቢ ሰዓታት ውስጥ የተፈጸመው ግድያ፣ ዓቃቤ ሕግንና ከግድያው ጋር በተያያዘ ተጠርጥረው የታሰሩ ተጠርጣሪዎችን ማወዛገቡ ቀጥሏል፡፡
ግድያው በተፈጸመ ማግሥት ከሰኔ 16 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በቁጥጥር ሥር ውለው በተለያዩ ጊዜያት ፍርድ ቤት ሲቀርቡ፣ የተጠረጠሩት ከግድያው ጋር በተያያዘና የሽብርተኝነት ሕግን አዋጅ ቁጥር 652/2001 በመተላለፍ በሽብር ተግባር ወንጀል ተጠርጥረው መሆኑን የሚናገሩት ቁጥራቸው ከ30 በላይ የሚሆኑት ተጠርጣሪዎች፣ ግድያውን በሚመለከት የፌዴራልም ሆነ የክልል መንግሥት አመራሮች የተናገሩትና ያሰራቸው የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ቢሮ የሚናገረው የተለያየ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ የሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. ከፍተኛ አመራሮች ግድያን በማቀነባበርና በመሳተፍ ተጠርጥረው፣ በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው በፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ ተጠይቆባቸው ቢፈቀድም፣ ፖሊስ በተሰጠው ጊዜ ምንም ዓይነት ማስረጃ ሊያቀርብባቸው ባለመቻሉ፣ ፍርድ ቤቱ ሰፊ ትንታኔ በመስጠት በዋስ እንዲለቀቁ ውሳኔ ሰጥቶ እንደነበር ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት አስረድተዋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው አማካይነት ነሐሴ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. ባቀረቡት ክርክር እንዳስረዱት፣ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ያቀረቡት የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዝርዝር ትንታኔ በመስጠት ለደንበኞቻቸው የጠበቀላቸውን ሕገ መንግሥታዊ የዋስትና መብት፣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ያላግባብ ስለነፈጋቸው ነው፡፡ የከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ሕገ መንግሥታዊ የሆነውን የዋስትና መብት የነፈጋቸው፣ ተቋሙን በማይመጥንና የዳኝነትን ብቃት ግምት ውስጥ ሊያስገባ በሚችል ሁኔታ መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ይኼውም አንድ የፀረ ሽብር ተግባር ወንጀል ፈጽሟል ተብሎ የተጠረጠረ ዜጋ በፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 20 (3) ድንጋጌ መሠረት ምርመራ ሊፈቀድበት የሚችለው 28 ቀናት ሆኖ ተደንግጎ እያለ፣ በከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት በደንበኞቻቸው ላይ የተሰጠው የምርመራ ጊዜ 42 ቀናት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ይኼ ደግሞ የሕጉን ድንጋጌ ከመጣሱም በላይ፣ ምንም ዓይነት ማስረጃ ያልቀረበባቸው ተጠርጣሪዎችን ከሕግ አግባብ ውጪ እንዲታሰሩ ማድረግ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ዓቃቤ ሕግ፣ የፖሊስ አባል፣ የአብን አመራሮችና አባላት፣ የተቋማት ሠራተኞችና ሌሎችም ሲሆኑ፣ በመዝገብ ቁጥሮች 181966፣ 181965፣ 182124፣ 182129 እና በመዝገብ ቁጥር 182150 ተካተው በአምስት መዝገቦች ከ30 በላይ ተጠርጣሪዎች የከፍተኛው ፍርድ ቤት ውሳኔን በመቃወም በሰባት ጠበቆች ተወክለው ሰፊ ክርክር አድርገዋል፡፡
የፌዴራል መንግሥትና የአማራ ክልል የመንግሥት አመራሮች በአማራ ክልል አመራሮች ላይ የተፈጸመው ግድያ ‹‹የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ነው›› እያሉ በይፋ ከዕለቱ ጀምሮ በመገናኛ ብዙኃን ጭምር ገልጸው እያለ፣ ደንበኞቻቸውን በሽብር ተግባር ወንጀል መጠርጠር እርስ በርሱ የሚጣረስና ሕዝብንም እምነት የሚያሳጣ መሆኑን ጠበቆቹ ገልጸዋል፡፡
ፖሊስ ደንበኞቻቸውን በሽብር ተግባር ወንጀል ጠርጥሯቸዋል ቢባል እንኳን፣ በተፈቀደለት የ28 ቀናት ጊዜ ውስጥ ማን በማን ላይና ምን ዓይነት ወንጀል እንደፈጸመ በመለየት በዝርዝርና በተናጠል ለፍርድ ቤት ማቅረብ እንዳለበት በሕጉ ተደንግጎ ቢገኝም፣ 28 ቀናት ቆይቶ ፍርድ ቤት ሲቀርብ ምንም ዓይነት የምርመራ ውጤት አለማቅረቡን አስረድተዋል፡፡
የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤትም የፖሊስ ምርመራ መዝገቦችን አስቀርቦ ከመረመረ በኋላ፣ ምንም ዓይነት ለሽብር ተግባር ወንጀል የጥርጣሬ መነሻ ነገር ባለማግኘቱ፣ ተጠርጣሪዎቹ ከ2,000 ብር እስከ 5,000 ብር በሚደርስ ዋስትና ከእስር እንዲፈቱ ውሳኔ መስጠቱንም ገልጸዋል፡፡ ፖሊስ ‹‹በሽብር ተግባር ወንጀል ጠርጥሬያቸዋለሁ›› በማለት ላሰራቸው የአብን አባላት ያቀረበላቸው ጥያቄ፣ ‹‹ማንን ነው የምትረዱት? ማነው ያሰማራችሁ?›› የሚሉና ‹‹ጠርጥሬያችኋለሁ›› ካለበት መነሻ ሐሳብ ጋር የማይገናኝ መሆኑንም ጠበቆቹ ጠቁመዋል፡፡ ‹‹የአዲኃን ሥልጠና ወስዳችኋል፣ ከእነ ዘመነ ካሴ ጋር ግንኙነት አላችሁ›› የሚሉ የግለሰቦች ወይም የተወሰነ ቡድን ፍላጎትን የሚያንፀባርቁ ጥያቄዎች እንጂ፣ ከሰኔ 15 ቀን የከፍተኛ አመራሮች ግድያ ጋር የሚያያዝ ምንም ዓይነት ምርመራ እንዳልተካሄደባቸውም አስረድተዋል፡፡
አንዳንዶቹ በተለይ ዓቃቤ ሕግ አቶ የወግሰው በቀለና የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ባልደረባና የልደታ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምርያ መርማሪ ዋና ሳጅን ሞገስ በቀለ፣ የባልደራስ ምክር ቤት አባል መሆናቸውን ደርሰንበታልና መረጃ ያቀብላሉ›› ከሚል ምርመራ በስተቀር፣ የሽብር ወንጀል ተሳትፏቸው ምን እንደሆነ ያቀረበው የጥርጣሬ መነሻ ማስረጃ እንደሌለም ገልጸዋል፡፡
‹‹የከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት ዋስትና የከለከላቸው አቋም ይዞ ነው፤›› የሚሉት የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች፣ ይኼንንም ሊያስብላቸው የቻለው በዋስ እንዲወጡ በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት እያንዳንዳቸው የ5,000 ብር ዋስትና ማቅረብ እንዳለባቸው ውሳኔ የተሰጠላቸው፣ አቶ የወግሰው በቀለና ዋና ሳጅን ሞገስ በቀለ፣ ዋስትናቸው ወደ 200,000 ብር ማሳደጉ ማሳያ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ዋስትና ከተፈቀደላቸው ሳምንት ቢሞላቸውም፣ አቅማቸውን ያላገናዘበ ዋስትና በመሆኑ ከእስር ሊለቀቁ እንዳልቻሉም አክለዋል፡፡ ሌላው ጠበቆቹ ያቀረቡት ክርክር ሕጉ ግልጽ ሆኖ ሳለ፣ ለምን ተለጥጦና ለተጠርጣሪ በማይጠቅም ሁኔታ እንደሚተረጎም እንዳልገባቸው ጠቁመው፣ ከሰኔ 15 ቀን የእነ ጄኔራል ሰዓረ መኮንን ግድያ ጋር በተያያዘ፣ ‹‹የገዳዩ ሚስት ናት›› የተባለችና ከግድው ጋር ምንም ግንኙነት የሌላት ሴትም ታስራ እንደምትገኝ ገልጸዋል፡፡ ዳኞቹ የሚሠሩት ለህሊናቸውና ለሕግ ተገዥ ሆነው ቢሆንም፣ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በአግባቡ የሰጠውን ውሳኔ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ያገደበትና ከሕጉ ውጪ የሥራ ቀናትን ብቻ በመቁጠር በአጠቃላይ 42 ቀናት የፈቀደበት ሒደት፣ ከሕግ አግባብ ውጪ መሆኑንም አስረድተዋል፡፡ ፖሊስ ራሱ ጠይቆ የነበረው 28 ቀናት እንደሚበቃው ገልጾ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱ 42 ቀናት መፍቀዱ ለምንና በየትኛው የሕግ አግባብ እንደሆነ ግልጽ አለመሆኑንም አክለዋል፡፡ አዴፓ ‹‹እርስ በርሳችን ተጠፋፋን›› እያለ ከ30 በላይ ንፁኃን ዜጎችን ማሰር፣ ተገቢ አለመሆኑንም ገልጸዋል፡፡ መፈንቅለ መንግሥት መሆኑ የተገለጸበትን ድርጊት የሽብር ተግባር ወንጀል በማለት ዜጎችን ያላግባብ ማሰር ሆን ተብሎ ሰብዓዊ መብታቸውን ላለማክበር የተደረገ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ጠበቆችን ጭምር በነፃነት እንዳይከራከሩና እንዳይናገሩ ጫና በማድረግ፣ በክርክሩ ወቅት ያነሷቸውን መከራከሪያ ሐሳቦች እንኳን እንዳልመዘገበላቸውም አስረድተዋል፡፡ በአጠቃላይ ደንበኞቻቸው ታስረው የሚገኙበት ጉዳይ እንኳን በሽብር ተግባር ወንጀል፣ በተራ ወንጀል እንኳን ሊያስጠረጥር እንደማይችል የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች በክርክራቸው አስረድተዋል፡፡
ከሰኔ 15 ቀን ከፍተኛ የመንግሥት አመራሮች ግድያ ጋር በተያያዘ በሽብር ተግባር ወንጀል ተጠርጥረዋል ስለተባሉትና ይግባኝ ስለጠየቁት ተጠርጣሪዎች፣ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቀርቦ ምላሽ የሰጠው (የተከራከረው) የፌዴራል ፖሊስ ወንጀል መርማሪ ሳይሆን ዓቃቤ ሕግ ነው፡፡ በዕለቱ የቀረቡት ሁለት ዓቃቢያነ ሕግ እንዳስረዱት፣ እያንዳንዳቸው ተጠርጣሪዎች ከሰኔ 15 ቀን 2011 ዓ.ም. በፊት ሲደራጁ ቆይተው፣ በተለያዩ አቅጣጫዎች በመንቀሳቀስ ግድያው እንዲፈጸም አድርገዋል፡፡ ይኼ ሁኔታ በተፈጸመበትና ፖሊስ ስለሁኔታው በማጣራት ላይ እያለ፣ የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተጠርጣሪዎቹ በዋስ እንዲወጡ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡
ፍርድ ቤቱ ድርጊቱን ‹‹ተራ የፖለቲካ ሽኩቻ ነው›› በማለት የዳኛውን ገለልተኛነት የሚያጠራጥር መሆኑንም አክለዋል፡፡ ዓቃቢያነ ሕጉ እንዳብራሩት የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የምርመራ መዝገቡን ወስዶ ለሳምንት ማቆየቱና አልመልስም በማለቱ፣ እጃቸው ላይ በነበረ ሰነድ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ይግባኝ ብለው፣ የተጠርጣሪዎቹ የዋስትና መብት እንዲታገድ ማድረጋቸውን አስረድተዋል፡፡ በተለይ አራት ተጠርጣሪዎች በኅቡዕ ጦር እየመሩ እንደነበርና መረጃ ሲለዋወጡበት የነበረን ማስረጃ ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት ጠይቀው በመጠባበቅ ላይ እያሉ፣ ዋስትና መፍቀድ ተገቢ አለመሆኑንም ዓቃቢያነ ሕጉ ተናግረዋል፡፡
በግለሰብ እጅ ሊገባ የማይችል የጦር ሜዳ መነጽር መገኘቱንም ገልጸዋል፡፡ በአዲስ አበባ በወታደራዊ አመራሮች ላይ ግድያ ሲፈጸም የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቋረጥ ግዳጅ የተሰጣቸው፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሠራተኞች መያዛቸውንም ገልጸዋል፡፡ የጦር መሣሪያ መግዛቱንና 6,000 ጥይቶች ቢኖሩትም ከጎንደር እንዴት እንደሚያሳልፈው ምክክር ሲያደረግ የነበረ ተጠርጣሪና ሌሎችም፣ በኅቡዕ ተደራጅተው በእነማን ላይ ዕርምጃ እንደሚወስዱ ሥልጠና ጭምር የወሰዱ ተጠርጣሪዎች መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡ ይኼ ሁሉ ባለበት ገና በምርመራ ላይ እንደሆኑ እየገለጹ የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዋስትና መፍቀዱ ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡ በአጠቃላይ ከሰኔ 15 ከፍተኛ አመራሮች ግድያ ጋር በተያያዘ የሽብር ተግባር ስለመፈጸሙ ከተለያዩ የመንግሥት ተቋማት ጋር እየሠሩ እያለ፣ የወንጀል ተግባሩን በመቀየር ዋስትና መስጠቱም ተገቢ አለመሆኑን ዓቃቢያነ ሕጉ ደጋግመው አስረድተዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ በመሀል፣ ‹‹በመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት በእያንዳንዱ ተጠርጣሪ ላይ ለወንጀል ጥርጣሬ መነሻ የሚሆን የምርመራ ውጤት አቅርባችሁ ነበር?›› የሚል ጥያቄ ለዓቃቢያነ ሕጉ አቅርቦላቸው፣ ማን ከማን ጋር ግንኙነት እንደነበረው በቂ መጠርጠሪያ ማቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡ ቀሪ መረጃና ማስረጃ በመሰብሰብ ላይ እንደሆኑም ማስረዳታቸውን ከኢትዮ ቴሌኮም፣ ከባንክ፣ የባልደራስ ምክር ቤትን እንደ ሽፋን በመጠቀም ወንጀል መፈጸማቸውን ለማሳየት ከብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት መረጃ መጠየቃቸውን ቢገልጹም፣ ፍርድ ቤቱ እንዳልተቀበላቸው አስረድተዋል፡፡
ከፍተኛው ፍርድ ቤት ግን ያቀረቡትን የይግባኝ አቤቱታ በሚገባ ከተመለከተ በኋላ፣ ዋስትናውን እንደሻረውም አክለዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ በመቀጠል፣ ‹‹እናንተ (ዓቃቢያነ ሕጉ ወይም ፖሊስ) 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ ጠይቃችሁ ከፍተኛው ፍርድ ቤት እንዴት ከዚያ በላይ ሊፈቅድ ቻለ?›› በማለት ሲጠይቃቸው፣ ችሎቱ የበዓል ቀናትን ትቶ የሥራ ቀናትን ብቻ በመቁጠር መስጠቱን ጠቁመው ስህተት ከሆነ ሊታረም እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ በመቀጠል፣ ‹‹ከሰኔ 16 ቀን 2011 ዓ.ም. ጀምሮ በምርመራ ላይ ከሆናችሁ እንዴት እስካሁን አልጨረሳችሁም? አሁንስ በምን ላይ ናችሁ?›› የሚል ጥያቄ አቅርቦላቸው፣ ተጠርጣሪዎቹ ሲዘጋጁ የከረሙት ከጥቅምት ወር 2011 ዓ.ም. ጀምሮ መሆኑን፣ በቤንሻንጉል ጉምዝ ዋና ከተማ በአሶሳና በአዲስ አበባ የተፈጸመውን ሁሉ ማጣራት ስላለባቸው፣ እየሠሩና የጠየቁት ለመረጃ እስከሚመጣላቸው እየጠበቁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የተጠርጣሪዎቹ ጠበቆች በተሰጣቸው ድጋሚ የመከራከሪያ ዕድል እንዳስረዱት፣ ዓቃቤያነ ሕጉ የምርመራ መዝገቡ በመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት ስምንት ቀናት በዳኛ ዕግድ መቆየቱን ለችሎቱ መግለጻቸው፣ ከአንድ ከፍተኛ የሕግ ተቋም የማይጠበቅ ምላሽ ከመሆኑም ባለፈ ግምት ውስጥ የሚከት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ ፖሊስ የራሱን ዋና የምርመራ መዝገብ ይዞ ለፍርድ ቤት የሚያቀርበው ደግሞ ግልባጩን (ኮፒ) መሆኑን ጠቁመው፣ መዝገቡ ዳኛው ዘንድ ስምንት ቀናት መቆየቱንና ‹‹አልሰጥም አሉኝ›› የሚል ሰበብ ማቅረብ ተገቢ አለመሆኑን ገልጸዋል፡፡
ሌላው ዓቃቢያነ ሕጉ የምርመራ መዝገቡ አካል ያልሆነን ጉዳይ ‹‹አሶሳ ከተማ የተፈጸመን ድርጊትም እየመረመርኩ ነው›› ማለቱ የማይገናኝ ነገር ለማገናኝት መሞከር መሆኑንም አክለዋል፡፡ የጦር ሜዳ መነጽር ይዘው ተገኝተዋል በማለት ዓቃቢያነ ሕጉ ተጠርጣሪዎቹን ለመወንጀል ያደረገው ጥረት፣ ‹‹መነጽር አይደለም ታንክ ይዘው ቢገኙ ሽብር ነው ማለት ነው?›› በማለት ጠይቀው፣ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን አስቀርቦ እንዲያይላቸው ጠይቀዋል፡፡ ተገኘ የተባለው የጦር ሜዳ መነጽር የዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያና ከመምህር ቤት የተገኘ መሆኑንም አክለዋል፡፡ በኅቡዕ ተደራጅተው ጦር ሲመሩ ነበር የተባሉት ደንበኞቻቸው ጫማ የሚጠርጉ ሊስትሮዎች፣ የቤት ሠራተኞችና የፖለቲካ ድርጅት አባላት መሆናቸውንም አክለዋል፡፡
ግድያው ሰኔ 15 ቀን ተፈጽሞ ደንበኞቻቸው ሰኔ 16 ቀን መያዛቸው የሚገርም እንደሆነ የገለጹት ጠበቆቹ፣ ይኼ የሚያሳየው እነሱን ለመያዝ ዝርዝር ተይዞና ቀደም ብሎ ዝግጅት መኖሩ የሚያረጋግጥ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የሽብር ተግባር ወንጀል አያስቀጣም ሳይሆን፣ በአዋጅ ቁጥር 652/2011 አንቀጽ (19) መሠረት ሊያስጠረጥራቸው የሚችል ማስረጃ እንዳልተገኘባቸው ወይም ፖሊስ በተሰጠው የ28 ቀናት የምርመራ ጊዜ ሊያቀርብ እንዳልቻለ መግለጹ እንደሆነ አስረድተዋል፡፡ ዓቃቢያነ ሕጉ ተጠርጣሪዎቹ የጦር ሥልጠና ሲያደርጉ እንደነበር መግለጻቸው ስህተት መሆኑን ጠበቆቹ ጠቁመው፣ መንግሥት ራሱ በጀት መድቦ ሲያሠለጥናቸው የነበሩ መሆናቸውን አክለዋል፡፡ በአጠቃላይ ፖሊስ እንኳን ማስረጃ ሊያቀርብባቸው ቀርቶ ቃላቸውን እንኳን እንዳልተቀበላቸውም ጠቁመዋል፡፡
ተጠርጣሪው ዓቃቤ ሕግ አቶ የወግሰው በቀለ ለሥር ፍርድ ቤቶች ከታሰረ 50 ቀናት እንደሞላው ሲያስረዳ፣ ፍርድ ቤቱ ለምን ምርመራ እንዳልጨረሰ ፖሊስን ሲጠይቀው፣ የባልደራስ ምክር ቤት አባል መሆኑን ስለደረሰበት እያጣራ መሆኑን እንደገለጸም አስታውሰዋል፡፡
የግራ ቀኙን ክርክር የሰማው የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ሰሚ ችሎት መርምሮ ውሳኔ ለመስጠት ለነሐሴ 22 ቀን 2011 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
Ethiopian Reporter
በኢትዮጵያ የለውጥ ተስፋ እና ስጋቶች
ብስራት ወልደሚካኤል
afrosonb@gmail.com
ጥንታዊ እና ቀዳሚ ከነበሩ ሀገሮች መካከል አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ በተለይ በቅርቡ ከአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) በዓለ ሲመት ከተደረገበት መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ.ም. አካባቢ የተስፋ አድማሶች ጎልተው ይታዩ ነበር። ዛሬም በርካታ ፈተናዎች ተደቅነውባታል። ህዝቡም ዛሬም ቅን መሪና የዴሞክራሲ ሥርዓትን ይናፍቃል። ምንም እንኳ የተፈጥሮ ሃብትን የተቸረች ቢሆንም፤ ዛሬም ድረስ ለዜጎቿ ንፁህ የመጠጥ ውሃ አቅርቦት፥ የምግብ ዋስትና አለመረጋገጥ፥ የመብራት አቅርቦት እና አገልግሎት መጓል፥ ጥራቱን የጠበቀ በቂ የትምህርት እና የጤና ሽፋን በበቂ ሁኔታ አለመዳረስ ተጠቃሽ ችግሮች ናቸው።
በሀገሪቱ ስር የሰደደ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እና የመልካም አስተዳደር ዕጦት ሌላው የዜጎች ትልቁ ፈተና ነው። በተለይ ከሀገሪቱ ኢኮኖሚ ጋር ያልተመጣጠነ የህዝብ ብዛት፥ የወጣቶች ሥራ አጥነት፥ የህግ የበላይነት አለመረጋገጥ እንዳለ ሆኖ፤ ልቅ የሆነው የሙስና ሰንሰለት ሀገሪቱ ከውጭ በዕርዳታ፥ ብድርና ንግድ ከምታገኘው ዓመታዊ የውጭ ምንዛሪ ይልቅ በተደራጀ ፖለቲካዊ መዋቅር ተደግፎ ከሀገር የሚሸሸው የዶላር መጠን እና አድሏዊነት የተፀናወተው ሥርዓት አልባው የንግድ ሥርዓት የዜጎችን ሰላምና ህይወት ሲፈታተን ቆይቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ (ፎቶ፡ ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት የተወሰደ)
በርግጥ በኮሎኔል መግሥቱ ኃይለማርያም ይመራ ከነበረው የኢሕዴሪ መንግሥታዊ ሥርዓት መገርሰስ በኋላ ግንቦት 1983 ዓ.ም. በምዕራባዊያን እና አረብ ሀገራት ድጋፍ ወደ ሥልጣን የመጣው የቀድሞው የጫካ አማጺ የትግራይ ነፃ አውጭ ድርጅት (ህወሓት) ኢህአዴግ በሚል ካባ በአምሳሉ ከፈጠራቸው የፖለቲካ ድርጅት (ብአዴን/አዴፓ፥ ኦህዴድ/ኦዴፓ እና ደኢህዴግ/ደኢህዴን) ድርጅቶች ጋር ኢህአዴግ በሚል ግንባር ወደ ሥልጣን ሲመጣ ብዙ ተስፋ ተጥሎበት ነበር። ይሁን እንጂ በነበረበት ያለፉት 27 ዓመታት የማዕከላዊ መንግሥት ሥልጣን ቆይታው ለሀገሪቱም ሆነ ለዜጎችም በበርካታ ጉዳዮች እጅግ ፈተና የበዛበት የግፍ አገዛዝ ነበር። በአገዛዙም በርካታ ዜጎች በግፍ ታስረዋል፥ ተገድለዋል፥ ከሀገር ተሰደዋል። የሰብዓዊና የዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰትም ከሀገር አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ መነጋገሪያ እንደነበር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ነው። በርካታ ሰነዶችና ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ የህዝቡን ብቻ ሳይሆን ብሔራዊ የሀገሪቱን ጥቅም በማሳጣትም በሀገሪቱ ታሪክ ከነበሩ አገዛዞች በተለየ በጥቁር መዝገብ እንዲሰፍር ተደርጓል።
ከሶስት ዓመታት ተከታታይ ህዝባዊ አመፅ በኋላ መጋቢት 24 ቀን 2010 ዓ ም የሀገሪቱ 15ኛው ጠቅላይ ሚኒስትር በመሆን ወደ ሥልጣን የመጡት አብይ አህመድ (ዶ/ር) በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ፊት ቃለ መሐላ በመፈፀም ከወትሮ የኢህአዴግ አሰልቺ የቃላት ጋጋት እጅጉን የራቀና በዜጎች የተወደደላቸውን ንግግር በተሰማበት ወቅት ሀገሪቱ በብሩህ ተስፋ ተሞልታ ነበር። በተለይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተከታታይ በወሰዷቸው መልካም ርምጃዎች፤ በተለይም የታሰሩ የነፃው ፕሬስ ጋዜጠኞችን እና ጦማሪዎችን ጨምሮ የፖለቲካ እስረኞችን መፍታት፥ መንግሥት በዜጎች ላይ ለፈፀመው ጥፋት በይፋ ይቅርታ መጠየቅ፥ ብረት ያነሱ ተቀናቃኝ አማጺያንን ጨምሮ በውጭ ያሉ ተቀናቃኝ የፖለቲካ ኃይሎች በሰላም ወደ ሀገር ገብተው ሰላማዊ የፖለቲካ እንቅስቃሴ እንዲያካሂዱ ጥሪና ድጋፍ ማድረግ ተጠቃሽ በጎ ርምጃዎች ናቸው።
ለረጅም ጊዜ “ሞት አልባ” ጦርነት የነበረው የኢትዮጵፃ እና የኤርትራ መፋጠጥ በሰላም እንዲቋጭ ማድረጋቸው እና ብሔራዊ አንድነትና መግባባትን በአደባባይ ከማቀንቀን አልፈው ለተግባራዊነት መንቀሳቀሳቸው ከህዝቡ ባልተለመደ መልኩ በርካታ ድጋፍና አጋርነት አስገኝቶላቸዋል። እንዲሁም ለበርካታ ዓመታት ህዝቡ ያለገዥው ህወሓት/ኢህአዴግ ፍላጎት ውጭ ናቸው የተባሉና ታግተው የነበረው የሳተላይትና የመረጃ መረብ ሚዲያዎች ክፍት እንዲሆኑና ለህቡም አማራጭ ሆነው እንዲያገለግሉ መፍቀዳቸው፤ በተለይ ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ እና የፕሬስ ነፃነት አቀንቃኞችና ተሟጋቾች ሳይቀር ይበል የሚያሰኙ በርካታ ውዳሴዎችን እንዲያገኙ አስችሏቸዋል።
በሀገር ውስጥ በተለያዩ ከተሞች ጉብኝትና ምክክር ከማድረጋቸው በተጨማሪ በውጭ ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር ያደረጉት ምክክርና መቀራረብም ያልተለመደና የተወደሰ አዲስ የለውጥ ክስተት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። በህዝባዊ አመፅ ተዳክሞ የነበረውን እና የተራቆተውን የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ለማሻሻሉ እየወሰዱ ያሉት በጎ ርምጃም ከሚወደስላቸው ተግባራት መካከል አንዱ ነው። በተጨማሪም ላለፉት 27 ዓመታት በፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት ለሁለት ተከፍሎ የነበረው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ወደ አንድነት እንዲመጡ የተደረገው ድጋፍና አስተዋፅዖ ፤ እንዲሁም በተመሳሳይ መልኩ የኢትዮጵያ ሙስሊም መጅልስ ተቋም ላይ በተደረ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት የነበረው መለያየት ወደ አንድነት እንዲመጣ መደረጉ በበጎ የሚወሱ ተግባራት ናቸው። እነኚህ በጎ ተግባራት የህዝቡን አንድነትና ህብረት ከማጠናቀር በተጨማር በሀገሪቱ ሰላም፥ ዕድገትና ብልፅግና ላይ ዜጎች ብሩህ ተስፋን እንዲሰንቁ አስችሏቸዋል።
ነገር-ግን ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያ ሁሉ የነበረው ተስፋና ድጋፍ ግን ከአንድ ዓመታ በላይ መዝለቅ የቻለ አይመስልም። ለአንድ ዓመት ያህል የመብት ተሟጋቾችና ጋዜጠኞች ሳይታሰሩ የመቆየታቸው በጎ ተስፋ አሁን አሁን ስጋት እየታየበት ይገኛል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ የለውጥ መሪውና ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይወክሉታል በሚባለው ኦሮሚያ ክልልን ጨምሮ በርካታ ዜጎች የደህንነት ዋስትና ማጣት እየተለመደ መጥቷል። በአማራ ክልል፥ በደቡብ እና ቤኒሻንጉል ክልልም የተለያዩ አካባቢዎች ተመሳሳይ የፀጥታና ደህንነት ስጋቶች ይስተዋላሉ።
በጠቅላይ ሚኒስትሩ ላይ ከሚነሱ ነቀፌታዎች መካከል ይሰሩልኛል ብለው የነበረውን ህግ ወደ ጎን በመተው የራሳቸውን ሰው ከህግ አግባብ ውጭ የሾሟቸው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አካላት ሹመት፥ የሥራ ስምሪት እና የተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ሥልጣን እና ሹመት ከብቃትና አካታችነት ይልቅ ከዚህ ቀደም ይወገዝና ተቃውሞ ይቀርብበት የነበረውን የሟቹ አቶ መለስ ዜናዊ እና የድርጅታቸው ህወሓት አገዛዝን ተመሳሳይ መንገድ እየተከተሉ ነው በሚል በርካታ ደጋፊዎቻቸው ሳይቀር ነቀፌታ ማቅረባቸውን ቀጥለዋል። ይህ በእንዲህ እንዳለ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ሥልጣን ከመምጣታቸው በፊት በዋናነት ሶማሊና ኦሮሚያ ክልል አካባቢ ወደ አንድ ሚሊዮን ዜጎች ከመደበኛ መኖሪያቸው የተፈናቀሉ ቢሆንም፤ በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር የአንድ ዓመት አስተዳደር ጊዜ ውስጥ ግን ወደ ሁለት ሚሊዮን ዜጎች በኃይል ተፈናቅለዋል፥ በርካቶችም በርስ በርስ ግጭት ተገድለዋል፥ ቆስለዋል።
አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ወደ ሥልጣን ከመጡ በኋላ ብቻ የአዲስ አበባ ወጣቶችን ከአንዴም ሁለት ጊዜ ያለምንም ህጋዊ መሰረትና ምክንያት በጅምላ ሰብስቦ ማሰርና ማንገላታት በቀዳሚነት ይደግፏችው የነበሩ ወጣቶች አዲሱን አስተዳደር በጥርጣሬ እንዲያዩት ምክንያት ሆኗል። በተለያዩ መንግሥታዊ አስተዳድር ጉዳዮች እና አገልግሎት አሰጣጥ ላይም ሁሉንም በእኩል ከማየት ይልቅ ፖለቲካዊ ወገንተኝነትን የተላበሰ አድሏዊነት እየተንፀባረቀ ነው በሚልም የነበረውን ተስፋ በሂደት ወደ ስጋት እየተለወጠ መጥቷል። በተለይም በኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ አቅራቢያ ቡራዩ፥ ለገዳዲና ለገጣፎ ከተሞች፥ ምዕራብ ወለጋ፥ ቄለም ወለጋ፥ ሆሮ ጉድሩ ወለጋ፥ ምሥራቅ ወለጋ፥ ምዕራብ እና ምሥራቅ ጉጂ ዞን፤ በአማራ ክልል፥ ሰሜን ጎንደርና ምዕራብ ጎንደር፤ በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን፥ ጉጂ ዞን፥ ቡርጂ ጌዲዮ፥ አማሮ፥ ከፋ ዞን እና ደራሼ አካባቢን መጥቀስ ይቻላል። ይህ ዘገባ በሚጠናከርበት ጊዜም መንግሥት ባመነው መረጃ እንኳ ወደ ሶስት ሚሊዮን ዜጎች ከመደበኛ ኑሯቸውና ቀዬያቸው ተፈናቅለዋል። በርግጥ የተወሰኑት ወደ ቀድሞ መኖሪያቸው እንዲመለሱ ጥረት እየተደረ መሆኑ እንዳለ ሆኖ፤ አሁንም ድረስ ዜጎች ተረጋግተው የመኖር ተስፋቸው ላይ ስጋትን ጭሯል።
በኦሮሚያ ክልል ለሰላማዊ ትግል በሚል ስምምነት ወደ ሀገር ውስጥ ጥሪ ተደርጎለት ከኤርትራ አስመራ ወደ ሀገር የገባውና በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው ሸኔ የሚባለውና የኦነግ ክንፍ
በአራቱም የወለጋ ዞኖች በሚገኙ የተለያዩ 19 ያህል የንግድ ባንኮች ዘረፋ መፈፀሙ ቢገለፅም በጉዳዩ ዙሪያ ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ አዲስ አበባ የሚገኙት የድርጅቱ መሪም ሆኑ ሌሎች የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ዝምታን መምረጣቸው የህግ የበላይነት መላላትና የዜጎች ደህንነት ከዕለት ወደ ዕለት አደጋ ውስጥ መውደቁ ሌላኛው የጠቅላይ ሚኒስትሩ ድክመት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። የሀገሪቱ ፀጥታና ደህንነት ጉዳይ ከወዲሁ ትኩረት ካልተሰጠው፥ ተጠያቂነትና የህግ የበላይነት በሁሉም ዜጎች ላይ በእኩል የማይሰራ ከሆነ ወደ አላስፈላጊ ረብሻና ሥርዓት አልበኝነት እንዳያመራ ስጋት አለ። የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ከመጠበቅ አኳያ በመንግሥት በኩል እየተወሰደ ያለው የእርምትም ይሁን የጥንቃቄ ርምጃ እጅጉን ደካማ ነው።
ሐሳብን ከመግለፅና ከፕሬስ ነፃነት ጋር በተያያዘ ያለው ተስፋ በቅርቡ በአንዳንድ ጋዜጠኞችና ጦማሪዎች ላይ ስጋቶች እንደ አዲስ ተደቅኖባቸዋል። በተለይ የካቲት 23 ቀን 2011 ዓ.ም. በአዲስ አበባ አቅራቢያ ባሉ የኦሮሚያ ክልል ለገዳዲና ለገጣፎ ከተሞች በመንግሥት አስተዳድር በግልፅ ውሳኔና ርምጃ የተፈናቀሉ ዜጎችን አስመልክቶ ለዘገባ የተጓዙ የ”መረጃ ቲቪ” ዘጋቢ ጋዜጠኛ ፋሲል አረጋይ እና የፎቶ ጋዜጠኛው ሀብታሙ ኦዳ በከተማው ፖሊስ ጣቢያ ፊትለፊት የአካል ጥቃት ተፈፅሞባቸዋል። ጋዜጠኛ ፋሲልም በደረሰበት ጥቃት አዲስ አበባ ዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል የህክምና ርዳታ ተደርጎለታል። በቅርቡም የአሃዱ ቴቪ ጣቢያ ከሰንዳፋ ከተማ ጋር በተያያዝ በተላለፍ ዘገባ ጋር በሚል ግንቦት 16 ቀን 2011ዓ.ም. ጋዜጠኛ ታምራት አበራ ከሚሰራበት አሃዱ ቴልቪዥን እና ሬዲዮ ጣቢያ በኦሮሚያ ፖሊስ ተወስዶ መታሰሩና፤ በዕለቱ የታሰረውን ጋዜጠኛ ሊጎበኘው የሄደው የኢትዮ-ኦንላየን ሚዲያ ጋዜጠኛ ጌጥዬ ያለው መታሰሩ በነፃው ፕሬስ ጫና ጅማሮ ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። እንደ ምንጮች ከሆነ በአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ አስተዳደር እየተፈፀሙ ያሉ ብልሹና አድሏዊ አሰራሮችን የሚያጋልጡ የኢንተርኔት መረጃ አምደኛ ጋዜጠኞች፥ ጦማሪዎችና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች የጦማሮቻቸው እና የግል የይለፍ ቃል በኢትዮጵያ የመረጃ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ (INSA) ብርበራና የይለፍ ቃል ነጠቃ እየተሞከረ እንደሆነ ይነገራል። እነኚህ ሁሉ የነበሩ የለውጥ ብሩ ተስፋዎች ላይ የስጋት ደመና ጋርደዋል።
ሌላው ከዚህ ቀደም በህወሓት/ኢህአዴግ የመንግሥት አስተዳደር ወቅት የአመራር አካልና የወጣት አደረጃጀት አባላት የነበሩና ተከታዮቻቸው በአዲሱ የአብይ አህመድ ኦዴፓ/ኢህአዴግ አመራር ላይ የተለያየ ጫና ለመፍጠር ሲጥሩ ይስተዋላል። ለአብነትም የቀድሞ የኦህዴድ/ኦዴፓ የታችኛው አንዳንድ አመራር አካላት፥ የህወሃት አመራሮች፥ የቀድሞ ብአዴን/አዴፓ እና የደኢህዴን አመራሮች በየአካባቢያቸው ከሚያደርጉት እንቅስቃሴ በተጨማሪ በማኀበራዊ ሚዲያ ሳይቀር አንዳንዶቹ ከአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር መምጣት በኋላ ከኢህአዴግ አካል የነበሩት አዳዲስ የፖለቲካ ድርጅት በመፍጠር ጭምር የሚያደርጉት እንቅስቃሴ በአንዳንድ አካባቢዎች ጥርጣሬ፥ ግጭትና ስጋት መፍጠራቸው አልቀረም። በአንፃሩ ከኦነግ ታጣቂ በስተቅር አብዛኛው ከውጭ የመጡትም ሆነ በሀገር ውስጥ ያሉ የገዥው ኢህአዴግ ተቀናቃኝ የፖለቲካ ድርጅቶች ከአዲሱ አስተዳደር ጋር የተሻለ መከባበርና መቀራረብ ይታይባቸዋል። ይሄ ለሰላምና መረጋጋቱ ተስፋ ሰጭ ቢሆንም፤ በአንዳንድ ሚዲያ ላይ የሚታዩ የጋዜጠኝነት የሙያ ስነ ምግባር ጋር የሚቃረኑ የሚዲያ አጠቃቀም ክፍተቶች፥ ተጠያቂነትና ኃላፊነትን ተላብሶ እንዲሰራ ሊረዳ የሚችል ነፃና ገለልተኛ የጋዜጠኞች የሙያ ማኀበር አለመኖርም እንደ አንድ ስጋት የሚታይ ነው።
በተለያ በማኀበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ረገድ በርካታ የማኀበራዊ የግል ገፆች ትክክለኛ ባልሆነ ስም፥ አንዳንዱ ደግሞ በህይወት ባለም ሆነ በሌለ ስመ ጥር ግለሰቦች ስም ገፅ በመክፈት የሚሰራጩ ሐሰተኛ መረጃ ስርጭት እና የጥላቻ ንግግሮች ሌላው የለውጡ ፈተና ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። በተለይ ሐሰተኛ መረጃና የጥላቻ ንግግርን የሚያሰራጩ ግለሰቦች እየተበራከተ ከሄደ መንግሥና አስተዳደር ላይ ብቻ ሳይሆን የዜጎች ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትና የፕሬስ ነፃነት ላይ አሉታዊ ጫና ያሳድራል። ምናልባትም ችግሩ ተባብሱ በዜጎች መካከል ግጭት እና ቅራኔ መፍጠር ሲባባስ መንግሥት የራሱን አስተዳደራዊ ርምጃ እንዲወስድ ሊጋብዝ ይችላል። ይሄ ደግሞ በሌላ በኩል በዜጎች ሐሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትና የፕሬስ ነፃነት ላይ የራሱ የሆነ አሉታዊ ሚና ይኖረዋል። ስለዚህ ብሩህ ተስፋን ሰንቆ የነበረው ለውጥ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመንግሥትና በአንዳንዴ ዜጎች መካከል ጥርጣሬና ስጋትን እየታየ ይገኛል።