The Role of Development Aid in fuelling Corruption and Undermining Governance in Ethiopia
July 5, 2013
Seid Hassan- Murray State University-USA
My own research as well as the research of other scholars show that the control of donor resources allowed the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), not only to consolidate political power that it seized in 1991, but also virtually penetrate the Ethiopian society at the grassroots level and expand its repressive and predatory tentacles.*
This paper also makes use of my ongoing studies regarding corruption in Ethiopia. The concluding part of the paper ties the corruptive practices of the TPLF/EPRDF when it was a liberation front (that is, the humanitarian aid-corruption nexus) with its current and similar activities (that is, the capture and misuse of development aid.) The paper exclusively focuses on the development aid -corruption nexus.
The paper uses theme-based cases (heavily donor-funded projects) in order to illustrate the captured nature of development aid and extent of corruption in…
View original post 789 more words
“ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል”
Source: www.goolgule.com
ዓለም ባንክ ርምጃ ለመውሰድ ጫፍ ደርሷል ኢህአዴግ ላይ ቀደም ሲል ሲቀርቡበት ከነበሩት ሪፖርቶች በተለየ ጥቅሞቹ ላይ ያነጣጠሩ አስደንጋጭ መረጃዎች እንደወጡበት ተሰማ። መረጃው የኢህአዴግን አንገት የማነቅ ያህል እንደሚቆጠርና ለተግባራዊነቱ የተንቀሳቀሱትን አካላት “የአስተዋይነት” ትግል ውጤት እንደሆነ ተጠቁሟል…
ኢህአዴግ በህዝብ ስም በብድርና በርዳታ የሚያገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለፖለቲካ ስራ እንደሚያውለውና ለአፈና ተቋማቱ ማጠናከሪያ እንደሚጠቀምበት የተከሰሰበት ሪፖርት መጠናቀቁን የገለጹት የጎልጉል ታማኝ ምንጮች ናቸው። ምንጮቹ እንዳሉት ሪፖርቱ የቀረበለት የዓለም ባንክ በቅርቡ መረጃውን ተቀብሎ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ኢህአዴግ ርምጃው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለማክሸፍ የተለመደውን ሩጫ መጀመሩ ተሰምቷል።
በኢህአዴግ ላይ የቀረበው ሪፖርት የመፍትሄ ሃሳብም ያካተተ እንደሆነ የተናገሩት የጎልጉል ምንጮች፣ የዓለም ባንክ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሪፖርቱን ሙሉ በሙሉ እንደሚቀበለውና ይፋ እንደሚያደርገው አስረድተዋል። የምርመራ ዘገባውን ስላጠናውና ስላቀረበው የኢንስፔክሽን ተቋምና የስራ ተሞክሮ በቂ ግንዛቤ ያላቸው እነዚህ ክፍሎች እንደሚሉት የዓለም ባንክ ቦርድ ይህ ተቋም ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ያቀረባቸውን ሪፖርቶች ላለመቀበል አንገራግሮ እንደማያውቅ ያስረዳሉ።
በሚመሩት ህዝብ ላይ ግፍ የሚፈጽሙ መንግስታትና በልማት ስም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚያካሂዱ አገራት የሚፈጸሙ…
View original post 1,048 more words
ሰበር ዜና አሁድ የሚደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ የቀበሌ ሰራተኞች በየቤቱ እየቀሰቀሱ መሆኑ ተገለፀ
Bisrat Woldemichael
አንድነት ፓርቲ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ የከተማው መስተዳደሮችና የፀጥታ ኃይሎች ፓርቲው ህጋዊ የማሳወቅ ስራውን መስራቱን ገልፀው ሰልፉን መከልከል እንደማይችሉ ካረጋገጡ በኋላ በከተማው ያሉ የቀበሌ ሰራተኞች መደበኛ ስራቸውን ጥለው በሰላማዊ ሰልፉ ዙሪያ በየቤቱ እየዞሩ ማስፈራራትና ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ማንም እንዳይገኝ፣ ሰልፉ ህገወጥ ነው በሚል ቅስቀሳ እየሰሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ ችያለሁ፡፡ ነዋሪው በበኩሉ የፓርቲው ጥያቄ የእኛም ጥያቄ ስለሆነ በሰልፉ ላይ እንገኛለን፣ ፓርቲው የሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ህገወጥ ከሆነ እነሱን (ፓርቲውንና ቅስቀሳ የሚሰሩትን ) ለምን አታግዷቸውም የሚል ጥያቄ ሲያነሱባቸው፤ ለቅስቀሳው የተሰማሩት የቀበሌ ሰራተኞች እምቢ ብለው የሚወጡ ካሉ እስራት ይጠብቃቸዋል፤ በሚደርስባቸው ችግር ኃላፊነቱን አንወስድም ሲሉ ማስፈራሪያና ዛቻ መፈፀማቸው ተጠቁሟል፡፡
የደቡብ ወሎ ዞን የአንድነት ፓርቲ ሰብሳቢ አቶ ብስራት አቢ ቅስቀሳ በማድረግና በራሪ ወረቀት ሲበትኑ መጀመሪያ የደሴ ከተማ 4ኛ ፖሊስ ጣቢያ ያለምንም ምክንያት አስሯቸው የጣቢያው አዘዦች ከሰዓታት በኋላ ሲለቋቸው 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ በድጋሚ ምክንያቱን ሳይገልፅላቸው ለአንድ ሰዓት አስሮ እንደለቀቃቸው ተናግረዋል፡፡ አቶ ብስራት አሁንም ድረስ መስተዳደሩ ከፈቀደ በኋላ በጎን ህገወጥ ስራ መስራቱ እንዳሳዘናቸውና ሰላማዊ ሰልፉ ህገወጥ ነው ካለም ደብዳቤ መፃፍና እንዲቀር ማድረግ ሲችሉ ከላይ ፈቅደው እታች ላሉት መመሪያ አላስተላለፉም፤ ይሁን እንጂ ሰላማዊ ሰልፉ ህጋዊና ሰላማዊ ስለሆነ እንቀጥልበታለን፣ ህገወጥ ናችሁ የሚል አካል ካለ ሰልፉን ለማድረግ የሚያስችል ህጋዊ ሰነድ የያዙ መሆናቸውን በመግለፅ አሁንም ቅስቀሳ ላይ እንደሆኑ ማረጋገጥ ችያለሁ፡፡ የከተማው ፅጥታ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ በላይ በበኩላቸው እኛ ሰልፉን ለማደናቀፍ ያሰርነው የለም፣ እኔ አሁን ከከተማ ውጭ ስለሆንኩ አረጋግጬ እነግርሃለው፤ የእውነት የታሰረ ካለም አንተም አረጋግጥ ቢሉኝም ዳግም ላገኛቸው አልቻልኩም፡፡
የከተማው ከንቲባ አቶ አለባቸው የሱፍን በጉዳዩ ዙሪያ ትናንት ሐምሌ 3 ቀን 2005ዓ.ም. ሳናግራቸው ምንም የሚፈጠር ችግር እንደሌለና ከፓርቲው አመራሮች ጋርም ለመመካከርና ለመወያየት ቀጠሮ ይዘናል፣ ፓርቲው ህጋዊ በሆነ መንገድ አሳውቆናል፣ መከልከልም ሆነ ማገድ አንችልም፤ ነገር ግን በፀጥታው ጉዳይ ለመነጋገር ነው ያሰብነው ሲሉ ነግረውኝ ነበር፡፡ ዛሬ በቀበሌ ሰራተኞችና በየቀጠናው ባሉ ፖሊሶች እየተደረገ ስላለው ምላሽ እንዲሰጡኝ ወደ ቢሮአቸው ባቀናም ከቢሮ ውጭ ስብሰባ ላይ መሆናቸው ስለተነገረኝ ከሰዓት በኋላ በተንቀሳቃሽ ስልካቸው ብደውልም ሊያነሱልኝ አልቻሉም፤ስለዚህ ምላሻቸውን ማካተት አልቻልኩም፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች መካከል የመጨረሻው ዙር ከአዲስ አበባ አቶ ግርማ ሰይፉ(ብቸኛው የተፎከካሪ ፓርቲ የፓርላማ አባል)፣ አቶ በላይ ፈቃዱን ጨምሮ ሌሎች አመራሮች ለእሁዱ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ሰላማዊ ሰልፉ ዛሬ ደሴ ከተማ ገብተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ከሼህ ኑሩ ይማም መገደል ጋር በተያያዘ በርካት ወጣቶች አሁንም እየታሰሩ መሆኑን 4ኛ ፖሊስ ጣቢያ የተመለከትኩ ሲሆን ይህ በሌሎችም ጣቢያዎች እየተከናወነ መሆኑም በከተማው ያነጋገርኳቸው ነዋሪዎች አረጋግጠውልኛል፡፡
አንድነት ፓርቲ በይፋ ህዝባዊ የተቃውሞ ንቅናቄ ጀመረ
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ ገዥው የፓርቲ ኢህአዴግን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን እየጣሰ ነው በሚል ዛሬ ሰኔ 13 ቀን 2005 ዓ.ም. ይፋዊ ህዝባዊ ንቅናቄ መጀመሩን አስታወቀ፡፡ ፓርቲው አዲስ አበባ ቀበና በሚገኘው ዋና ፅህፈት ቤቱ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቀው “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት”(Millions of Voices For Freedom) በሚል መሪ ቃል መጀመሩን አስታውቋል፡፡
የሚሊዮኖችን ድምፅ በመሰብሰብ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚጋጨውን የፀረ ሽብርተኝነት ህግ በመቃወም እንዲሰረዝ የተቃውሞ ስምምነት ፊርማ(ፒቲሽን) በማሰባሰብ ለእስር ተዳረጉ ፖለቲከኞች፣ ጋዜጠኞች እና የኃይማኖት ነፃነት ጠያቂዎች እንዲፈቱ እንጠይቃለን ብሏል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በሀገሪቱ በተለያየ ምክንያት ገጠርና ከተማ ያሉ ከአዲስ አበባና ሌሎች ከተማ ያሉ ዜጎች አለአግባብ ከሚኖሩበት ቀዬ ማፈናቀል በተለይም ዘርን መሰረት በማድረግ ከጉራፈራዳና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ያሉ ነዋሪዎች እና በልማት ስም ለውጭ ዜጎች መሬት እየተሰጠ እንደ ጋምቤላ ያሉ ዜጎቻችን መፈናቀላቸው ህገወጥ ተግባር ነው በሚል በማውገዝ የድርጊቱ ፈፃሚዎችን ለፍርድ ማቅረብ እንደተዘጋጀና ለዚህም እንቅስቃሴያችንን የሚደግፉ ኢትዮጵውያን ፊርማቸውን እንዲያኖሩ ጠይቋል፡፡
ፓርቲው ከላይ የተጠቀሱትን ተግባራዊ ለማድረግ የተለያዩ የሰላማዊ ትግል ስልቶችን የቀየሰ ሲሆን በዋነኝነትም በአዲስ አበባና በተለያዩ የክልል ከተሞች ህዝባዊ የአዳራሽ ስብሰባዎችን፣የአደባባይ ስብሰባዎችንና የተቃውሞ ሰላማዊ ሰለፍ ማድረግን እንደሚያካትት ተጠቅሷል፡፡ በተለይ በአዲስ አበባ 6 ህዝባዊ ስብሰባዎችን፣ በክልሎች ለመጀመሪያ ዙር ብቻ 10 ስብሰባዎች ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታውቋ፡፡
እንደ ፓርቲው ገለፃ ከሆነ የህዝባዊ ንቅናቄ ዓላማው፡-
1. የፀረ-ሽብር ህጉ የኢትዮጵያውያንን በርካታ መብቶች የሚገፍ በመሆኑና ከህገ መንግስቱ ጋር የሚፃረር በመሆኑ በሚሊዮኖች የሚቆጠር የተቃውሞ ድምፅ በማሰባሰብ በአስቸኳይ እዲሰረዝ ጥያቄ እናቀርባለን፡፡ የድጋፍ ፊርማ(ፒቲሽን) እናስፈርማለን ፡፡ ይህንንም በሰላማዊ ሰልፍ እንጠይቃለን፡፡ ከዛም የሚሊዮኖችን ድምፅ በመያዝ ወደ ክስ እንሄዳለን፡፡
2. በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለው በገጠርና በከተማ የዜጎች መፈናቀልና የመሬት ቅርምት እንዲቆምና መፍትሄ እንዲያገኝ እንጠይቃለን፡፡
3. የስራ አጥነትና የኑሮ ውድነት እንዲቀረፍ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ እርምጃዎች እንዲወሰዱ እንጠይቃለን፡፡
4. የንግዱ ማኀበረሰብ ውስጥ ፍትሃዊ ውድድር እንዲኖር ፣ ማጥላላትና ማዋከብ እንዲቆም፤ ገዥው ፓርቲ ህግ አውጭ እና ነጋዴ የሚሆንበት ስርዓት እንዲያበቃና የግሉ ሴክተር በልማት ውስጥ ከፍተኛ ሚና እንዲኖረው እንጠይቃለን፡፡ ለዚህ ትልቅ ሀገራዊ ንቅናቄ መሳካት ህዝቡ ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ መኀበራት፣ ሚዲያው፣ በውጭ የሚኖሩና ለሀገር ተቆርቋሪ የሆኑ ኢትዮጵያውያን፣ የሀገርን ጥቅም ለማስቀደም የሚፈልጉ የኢህአዴግ አባላት እንዲሳተፉ ሀገራዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን ሲል በመግለጫው አስታውቋል፡፡ በመግለጨው ዙሪያም ከጋዜጠኞች በርካታ ጥያቄዎች ቀርበው ከፓርቲው አመራሮች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጥፋተኛ መሆኑን አመነ
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ምንያህል ተሾመ ሰኔ 1 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቦትስዋና ብሄራዊ ቡድን ጋር በተደረገው ጨዋታ መሰለፉ ስህተት እንደሆነ አመነ፡፡ ፌዴሬሽኑ ብሄራዊ ቡድኑ ከደቡብ አፍሪካ አቻው ጋር ከመጫወቱ በፊት ችግር ስለመፈጠሩ ከፊፋ ደብዳቤ ደርሶት እንደነበርም ገልጿል፡፡

የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ለችግሩ ተጠያቂ ያላቸውን ግለሰቦች ዝርዝርም ይፋ አድርጓል፡፡ በዚህ መሰረት የብሄራዊ ቡድኑ ቡድን መሪ አቶ ብርሀኑ ከበደ ፣ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ፣ ረዳት አሰልጣኝ ስዩም ከበደ ፣ የቡድኑ ተጨዋች ምንያህል ተሾመ እና የፌዴሬሽኑ ፅህፈት ቤት ኃላፊዎች ጥፋተኛ ተብለዋል።
ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴው በጥፋተኞቹ ላይ በቅርቡ ተገቢውን ቅጣት በመውሰድ የቅጣት ውሳኔውን ለህዝብ ይፋ እንደሚያደርግ አስታውቋል፡፡
ፌዴሬሽኑ በተፈጠረው ችግር ከፍተኛ ሀዘን እንደተሰማው ገልፆ መላውን የኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርታ ጠይቋል፡፡
የቡድኑ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው በተፈጠረው ስህተት የተሰማቸውን ሀዘን ገልፀው ፥ ከማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ ጋር ለሚካሄደው ጨዋታ ከወዲሁ መዘጋጀት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ ይሁን እንጂ አሰልጣኝ ሰውነት ቢሻው ጨዋታውም አሸንፈን ወደ አለም ዋንጫ እንደምንሳተፍ እርግጠኛ ነኝ ብለዋል ፡፡
በፊፋ ህግ መሰረት ተገቢ ያልሆነ ተጨዋችን ማሰለፍ በጨዋታው የተገኘውን ነጥብ እና ተጨማሪ የገንዘብ ቅጣት እንደሚያስጥል ይታወቃል፡፡