ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖት ተፈታ
በየመን ሁቲ አማጽያን እጅ ለእስር ተዳርጎ የነበረው ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖት ከእስር ተፈትቶ ከቤተሰቡ ጋር ተቀላቅሏል። ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖት የታሰረበት ምክንያት ይደግፈው በነበረ አንድ ስደተኛ ኢትዮጵያዊ ጥቆማ ሲሆን ” በስደተኛው ስም እርዳታ ይሰበስባል ፣ ስለየመን የተለያዩ መረጃዎችም ወደ ውጭ ያቀብላል ” የሚል ክስ ተመስርቶበት ነበር ።
ጉዳዩን ያጣራው ፖሊስ በቀረበው ክስ ዙሪያ ጭብጥ መረጃ ማስረጃ በማጣቱ ግሩም በነጻ ተለቋል ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የከሳሽ ምስክር ሆነው የቀረቡት አብዛኛው ምስክሮች ” እውነትን በጥቅም አንለውጥም ” በሚል ከሳሽን በመክዳት ወደ ህሊናቸው መመላሳቸው ታውቋል ።
