Category Archives: News

በደብረማርቆስ ማረሚያ ቤት 5 ሰዎች ህይወታቸው አለፈ

በደብረ ማርቆስ ማረሚያ ቤት  በደረሰ ቃጠሎ  በእስር ላይ የሚገኙ 5 ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ በርካቶች መቁሰላቸው ተገለፀ፡፡ በተለይ ከስፍራው  ምንጮቸችን እንደገለፁት ከሆነ ቃጠሎው የተከሰተው ታህሣሥ 12 ቀን 2005ዓ.ም.  ከሌሊቱ 5 ሰዓት እንደሆነ እና እስረኞቹ ላይ ጉዳት ሊደርስ የቻለው  በእስር ላይ የሚገኙ ሰዎች ያሉት ክፍል ሲቃጠል በላያቸው ላይ ተዘግቶ የነበረውን በር የሚከፍትላቸው አጥተው እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

አዲስ ሚዲያም  የቃጠሎውን መንስኤ እና ቃጠሎው ባጠቃላይ ያደረሰውን ጉዳት በተመለከተ የደብረማርቆስ ማረሚያ ቤት አስተዳደርና የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በጉዳዩ ዙሪያ  ምላሽ እንዲሰጡን ተደጋጋሚ ጥረት ቢደርግም አልተሳካም፡፡

በኮብልስቶን ስራ በተፈጠረ የእርስ በርስ ግጭት 8 ሰዎች መሞታቸው ተገለፀ

በአዲስ አበባ በሚገኘው ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ስሙ ቦሌ ለሚ በሚባል አካባቢ ማክሰኞ መጋቢት 3 ቀን 2005ዓ.ም. ኮብልስቶን በሚሰሩ ሰዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት 8 ሰዎች መሞታቸውንና በርካታ ሰዎች መቁሰላቸው ተጠቁሟል፡፡ ከአካባቢው ምንጮቻችን የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ የግጭቱ መንስኤ የሞባይል መጥፋት እንደሆነ እና በዚህም ኮብልስቶን ትሰራ የነበረች የአንዲትን ሴት ጡት ሌላው ሰራተኛ በመቁረጡ ህይወቷ ማለፉን ተከትሎ በዛው ዕለት ፀቡን ለማረጋጋት የሞከረ ፖሊስም በኮብልስቶን ተመቶ ወዲያው ህይወቱ ማለፉን ጠቁመዋል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ጉዳዩ ወደ ዘረኝነት ስሜት ተለውጦ ግጭቱ እስከ ሐሙስ መጋቢት 5 ቀን መዝለቁንና ህይወቷ ያለፈው ወጣት የአካባቢው ኦሮሚያ ተወላጅ በመሆኗ ጉዳዩ ወደ ማኀበረሰቡ በመድረሱ በርካታ የአካባቢው ሰዎች ከአያት ኮንዶሚኒየም እስከ ቦሌ ለሚ ድረስ ከበባ በማድረግ በሰራተኞች መካከል የኢህአዴግ አደራጅና ሰላይ ናቸው የተባሉ 6 ሰዎችን በመግደልና በርካታ ሰዎችን በማቁሰላቸው በአካባቢው ከ 3 ተሸከርካሪ ያላነሱ የፌደራል ፖሊሶች ግጭቱን ለማረጋጋት  ቢገኙም እንዳልቻሉና በርካቶችንም ወስደው እንዳሰሩ የዓይን እማኞች ገልፀዋል፡፡ ይሁን እንጂ እስከ አሁን ከፖሊስ ወገን የተሰጠ ማረጋገጫ የለም፡፡  የዝግጅት ክፍሉ ጉዳዩ በቀጥታ ይመለከተዋል ወደተባለው  ቦሌ ክፍለ ከተማ  ፖሊስ መረጃ ክፍል ስለጉዳዩ ለማረጋገጥ ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካም፡፡

ዘገባው ወደህዝብ እንዲደርስ እስከተደረገበት መጋቢት 7 ቀን 2005ዓ.ም. ድረስ ቀደም ሲል በርካታ ሰዎች የኮብልስቶን ስራ ይሰሩበት የነበረው አያት ጨፌ እና ቦሌ ለሚ የሚባል አካባቢ ማንም ሰው እንዳይገባ የተደረገ ሲሆን ከሰራተኞች ጋር እዛው በሚገኝ ቀበሌ ለጊዜው ማንነታቸው ያልታወቁ የመንግስት ባለስልጣናት እያወያዩ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡ ችግሩ እስኪፈታም  በአካባቢው እስከ ሰኞ መጋቢት 10 ቀን 2005ዓ.ም. ድረስ ስራ እንደለሌም ምንጮቻችን ከስፍራው ጠቁመዋል፡፡ ስማቸውን መግለፅ ያልፈለጉ በስፍራው የኮብልስቶን ስራ ላይ ተሰማርተው የነበሩና አሁን በውስጡ የቆየና እየተስፋፋ የመጣው የዘረኝነት ስሜት አስፈሪ ደረጃ ላይ የደረሰ በመሆኑ፤ ቀደም ሲልም ችግሩ እንዲቀረፍ ቢገለፅም ከማባባስ ውጭ መፍትሄ የሚሰጥ የመንግስት አካል ባለመኖሩ ዳግም ወደስራው እንደማይመለሱ በመግለፅ “ይህ ዜጎችን በዘረኝነት ከፋፍሎ የማጫረስ የአቶ መለስ ዕራይ ተጠናክሮ መቀጠሉን ያሳያል ሲሉ በስፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች ገልፀዋል፡፡

በኢትዮጵያ የንግድ ስራ ችግር ገጠመው

 

በኢትዮጵያ ከፍተኛ የንግድ መቀዛቀዝ እየታየ መሆኑ ተጠቆመ፡፡ በተለይ በውጭ ምንዛሪ እጥረት ምክንያትና የገዥው ኢህአዴግ የአየተከተለ ያለው የንግድ ስርዓት አድሎነት የተሞላበት ከመሆኑም በተጨማሪ ለስርዓቱ ከቀረቡት ጥቂት ነጋዴዎች እና ንብረትነቱ የህወሃት/ ኢህአዴግ እንደሆነ የሚነገርለት ኤፈርት ኩባንያ ውጭ ያሉ ነጋዴዎች ከአቅማቸው በላይ ግብር እየተጫነባቸው በመሆኑ  የንግድ ስራቸውን ወደ ሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች እያዛወሩ መሆኑን ስማቸውን መግለፅ ያልፈለጉ ኢትዮጵያውያን የኩባንያ ባለቤቶች አስታወቁ፡፡

እንደባለሃብቶቹ ገለፃ ከሆነ በአሁን ሰዓት ምንም ዓይነት የባንክ ብድር እንዳናገኝ አበዳሪ ባንኮች ለእኛ የሚያበድሩ ከሆነ ከሚያበድሩን ገንዘብ ላይ 27 በመቶ ለአባይ ግድብ እንዲያውሉ ጥብቅ መመሪያ በመተላለፉ ባንኮቹ ለማበደር ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ በዚህም ምክንያት በንግድ ስርዓቱ ላይ ከፍተኛ ችግር በመፈጠሩ በሀገሪቱ ላይ የዕቃ አቅርቦት ችግር እየተከሰተ መሆኑንም  ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ ከውጭ ዕቃ ለማምጣት የውጭ ምንዛሪ የሚፈልግ ነጋዴ ከመደበኛው የአሜሪካን ዶላር ምንዛሪ ውጭ በአንድ ዶላር እስከ 25 ሳንቲም ተጨማሪ ክፍያ በህገወጥ መንገድ ለባንክ አስተዳደሮች እንዲሰጡ እየተገደዱ መሆኑን በማስታወስ እንደ ለስላሳ መጠጦች ኢንዱስትሪ ያሉትም ከውጭ ምንዛሪው እጥረት በተጨማሪ የስኳር አቅርቦት ችግር በመከሰቱ የምርት እጥረት መኖሩም ተጠቁሟል፡፡

ከላይ ተፈጠረ የተባለውን የንግድ ችግር በተመለከተ የንግድ ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አማከለ ይማም በበኩላቸው “የተባለው ችግር አልተፈጠረም፣ ይህን በሚመለከት ጥያቄያችሁን በፅሑፍ ማቅረብ አለባችሁ” ከሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ የተፈጠረውን የውጭ ምንዛሪ እጥረት በተመለከተ ደግሞ የብሔራዊ ባንክ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደረጀ እንግዳው  የውጭ ምንዛሪ እጥረትን በተመለከተ የባንኩ ገዥ እና ምክትላቸው ለኢቴቪ ከሰጡት ውጭ ሌላ ምላሽ እንደሌላቸው  ለፍኖተ ነፃነት ገልፀዋል፡፡

ከደመወዛቸው ላይ በግድ ለአባይ ግድብ መቆረጡን ሰራተኞች ተቃወሙ

 

 በደቡብ ክልል ወላይታ ዞን የሚሰሩ የመንግስት ሰራተኞች ከዚህ በፊት ለአንድ ዓመት አቅማችን ሳይፈቅድ ከወር ደመወዛችን ላይ ሲቀቆረጥ ነበር፤ አሁን ግን ካለብን የኑሮ ውድነት የተነሳ አቅማችን አይፈቅድም ስለዚህ ያለፈቃዳችን ሊቆረጥብን አይገባም ሲሉ በርካታ የመንግስት ሰራተኞች ፒቲሽን ተፈራርመው ማስገባታቸው የደረሰን መረጃ አየመንግስት  ሰራተኞች በግድ ለአባይ ግድብ ከደመወዛቸው ላይ እንዳይቆረጥብን ሲሉ ፒቲሽን መልክቷል፡፡

ሰራተኞቹ በቁጥር ወደ 36 የሚደርሱ በዞኑ በተለያየ የመንግስት መስሪያ ቤት የሚሰሩ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን እስካሁን የተሰጣቸው ምላሽ ግን የለም፡፡ እንደሰራተኞቹ ገለፃ ከሆነ “በአሁን ወቅት በሀገሪቱ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ተከስቶ እያለ ያለፈቃዳችን ለአንድ ዓመት ያህል ተቆርጧዋል፤ አሁን ግን አንችልም፡፡ ስለዚህ አሁንም በኢህአዴግ ካድሬዎች አማካኝነት ያለፈቃዳችን ከደመወዛችን ላይ እንዳይቆረጥ እስከመጨረሻው እንታገላለን” ሲሉ አስታውቀዋል፡፡

በተለይ በዞኑ አረካ ወረዳ ያሉ የግብርና ሰራተኞች ድርጊቱን ተቃውመው አቤቱታ ለወረዳው አስተዳደርና ግብርና ፅ/ቤት ቢያቀርቡም አቤቱታቸውን ውድቅ እንዳደረጉባቸው በመግለፅ በጋራ የተስማሙ ሰራተኞች እስከ ፍርድ ቤት ድረስ በመሄድ ክስ እንደሚመሰርቱ አስታውቀዋል፡፡ ስለጉዳዩ ለማጣራት የዝግጅት ክፍሉ ወደወረዳው ዋና አስተዳደር አቶ ደመቀ ደጀኔ ተደጋጋሚ ጥረት ቢደረግም አልተሳካም፡፡፡

ይሁን እንጂ በድጋሚ ወደወረዳው ግብርና ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ ጴጥሮስን ስለጉዳዩ ጠይቀናቸው “ተቆረጠ የተባለው ደመወዝ ሰራተኞቹ በተስማሙት መሰረት ነው፤ በርግጥ በታህሣስ 2005 ዓ.ም. ሊቀረጥ ሲል ወቅቱ በዓል ስለነበረ እንዳይቆረጥብን ስላሉ ቅሬታቸውን የተቀበልን ቢሆንም ኋላ ከጥር 2005 ዓ.ም. ጀምሮ 2ኛ ዙር እንዲቆረጥ በተስማሙት መሰረት መቆረጥ ተጀምሯል፡፡ በዚህም ዙሪያ አንዳንድ ግለሰቦች ከወር ደመወዛቸው ላይ እንዳይቆረጥ ቅሬታ ያቀረቡ ቢሆንም ከተጀመረ በኋላ ማስተናገድ እንደማንችል ተነጋግረን ተግባብተናል” ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ አረካ ወረዳ በደቡብ ክል ወላይታ ዞን ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የተወለዱበትና ምርጫ የተወዳደሩበት ስፍራ መሆኑ ይታወቃል፡፡

Opposition Political Parties Showing Reservation to the Ethiopian National Transitional Council (ENTC)

By Betre Yacob.

Ethiopian National Transitional Council (ENTC)Opposition political parties in Ethiopia are said to have been showing reservation to the Ethiopian National Transitional Council (ENTC), which has been working to overthrow the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) tyrannical regime that has been abusing, oppressing and exploiting its own people.

One ENTC leadership told this writer in an interview that although opposition political parties working in Ethiopia expressed their support to the Council (ENTC) — most of them have so far shown reservation to work together.

“When we formed ENTC, we had anticipated the joining of the other political groups under this umbrella. Hence the structure of the organization was designed in a bi-cameral way where organizations will have one wing with their voices and votes, and the public will be on the other end. To that effect, written invitations were sent to all the organized groups that are struggling for change in Ethiopia. Unfortunately, this did not work out as the opposition parties had some reservations even though they expressed support to the council”, he said.

The leadership, who said that the opposition political parties needed time to feel comfortable to rally behind the idea and join this new organization, said that —recognizing the problem —the general assembly of the council had passed a resolution in July 2012— to mobilize the public and, in the mean time, work closely with the other political parties and civic organizations.

“Accordingly, we are working together with other political parties in defining the roadmap and target around the alternative that ENTC believes yields success. Along with several other political parties and civic organizations, we have formed the “Joint Coordinating Committee of Ethiopian Democratic Forces” to help strengthen the cooperation. This committee is comprised of subcommittees and task forces which help develop the working relationships between the organizations”, he said.

The leadership also said that studying the past history of Ethiopian politics and assessing current political situations in Ethiopia, ENTC believed that along with the struggle for freedom— it was not too early to start thinking and planning of what was beyond.

“We believe that creation of an all-inclusive transitional government will help us have a framework and readiness that is required if the regime falls. In addition to that, having this institution beforehand will force the disparate political groups to work under one umbrella strengthening the struggle, hence two birds with one stone. Currently ENTC is calling for the formation of such an institution”, he explained.

Different political analysts argue that the Ethiopian National Transitional Council (ENTC) has been the first ever and wise development in the Ethiopian opposition politics. They are optimistic that the council will strengthen the Ethiopian struggle for freedom by bringing opposition political parties —which have been so fragmented.

The Ethiopian National Transitional Council (ENTC) was officially established in Dallas, USA on July 3, 2012, by Ethiopians from all over the world. It has been given the objective to overthrow the EPRDF regime and facilitate a peaceful transition of power to opposition political parties through participatory, fair, and democratic election.

Since its establishment, the council have done so many successful activities. For instance, it has managed to organize and mobilize Ethiopians that were part of the silent majority at the grassroots level in different local councils / chapters from all over the world including some in Africa. In addition, it has been doing meaningful works to influence western governments, which are the backbone of the tyrant regime in Ethiopia, to stand for the demand of the Ethiopian people.