Category Archives: Politics

በአዲስ አበባ የተጠራው ሰልፍ በፖሊስ ድብደባ እና እስር ተጠናቀቀ

ሰማያዊ ፓርቲ የሳውዲዓረቢያ መንግስት ከባለፈው ሳምንት ጀምሮ በኢትዮጵያውያን ላይ እየፈፀመ ያለውን ግድያ፣ እስር እና እንግልት ለመቃወም ዛሬ አርብ ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም. አዲስ አበባ ወሎ ሰፈር በሚገኘው የሰውዲ ኤምባሲ ሊደረግ የነበረው የተቃውሞ ሰልፍ በፌደራል እና በአዲስ አበባ ፖሊስ ድብደባ እና እስር ተጠናቀቀ፡፡ ሰለፍ 4 ኪሎ ግንፍሌ ከሚገኘው የሰማያዊ ፓርቲ ጽህፈት ቤት ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ሲጀምር በበፖሊስ እገታ ተፈፅሞ ነበር፡፡ በመቀጠልም አራት ኪሎ ቅድስት ስላሴ ኮሌጅ ፊትለፊት ደግሞ በርካታ የፌደራል ፖሊሶች ዳግም እገታ ፈፀሙ፡፡

በመጨረሻም በእገታው ያልተበገረው የአዲስ አበባ ነዋሪ ወሎ ሰፈር በሚገኘው የሳውዲዓረቢያ ኤምባሲ አካባቢ ቢያመራም በ3 ፒክአፕ መኪና የመጡ የፈደራል ፖሊሶች የተገኘውን ህዝብ በያዙት ዱላ፣ በእጅ እና በእግር ድብደባ ጀመሩ፡፡ ከረፋዱ 5፡30 ሰዓት ላይ እዛውም የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች አቶ ይልቃል ጌትነት፣ አቶ ስለሺ ፈይሳ፣ አቶ ጌታነህ ባልቻ ፣ አቶ ወረታው ዋሴ፣ አቶ ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ አቶ ዮናታን ተስፋዬ እና አቶ ሀብታሙ ደመቀ በፖሊስ ታስረው ተወሰዱ፡፡ በዚሁ ሰዓት ደራሲ አቶ አስራት አብርሃምም መታሰሩ ታውቋል፡፡

በሰልፉ ላይ ከተገኙ ነዋሪዎችም ቁጥራቸው ከ500 የማያንሱ ሰዎች ታፍሰው ላንቻ ፖሊስ ጣቢያ እና ጃንሜዳ ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸውን የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ከበደ ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ ከቀኑ 10፡50 ሰዓት አካባቢ ከታሰሩት መካከል የተወሰኑትን መፍታት መጀመሩን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ይሁን እንጂ ይህ እስከተዘገበበት ሰዓት ድረስ ከተፈፀመባቸው ድብደባ በተጨማሪ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችን ጨምሮ በርካታ ሰዎች አሁንም እስር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል፡፡

 በዚህ ጉዳይ ላይ የመንግስት ቃል አቀባይ የሆኑት አቶ ሽመለስ ከማል እና የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ አቶ አባተ ስጦታውን ለማናገር ብንሞክርም ስልካቸውን ባለማንሳታቸው አልተሳካም፡፡ በፖሊስ ድብደባ ተፈፅሞባቸው ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው በተለይ ከላንቻ አካባቢ ካለው ከፖሊስ ጣቢያ በሚኒባስ እየተወሰዱ መሆናቸውን የዓይን እማኞች የገለፁ ሲሆን፤ ወሎ ሰፈር በሚገኘው ሳውዲዓረቢያ ኤምባሲ አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎችም ተባባሪ ናችሁ በሚል አሁንም እየተለቀሙ እየታሰሩ መሆኑን ምንጮቻችንን አስታውቀዋል፡፡

ይህ ሁሉ ድርጊት ያበሳጫቸው የሰልፉ ታዳሚዎች እና ታዛቢዎች መንግስት ይሄንን ስፍ እራሱ ማስተባበር የሚጠበቅበትን ዜጎች በራሳቸው ፈቃድና ተነሳሽነት ድርጊቱን በመቃም መውጣታቸው ሊበረታታ ሲገባ መከልከሉ ኢህአዴግ ኢትዮጵያውያን በሳውዲዓረቢያ መንግስት እና ፖሊስ እደረሰባቸው ያለውን ግድያ፣ እስር እና ስቃይ እንደሚደግፈው በግልፅ ያረጋገጠበት ነው ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡ የፊታችን እሁድ ህዳር 8 ቀን 2006 ዓ.ም. አንድነት ከሌሎች የመድረክ አባል ፓርቲዎች ጋር ተመሳሳይ ሰልፍ በዚሁ በአዲስ አበባ ወሎ ሰፈር በሚገኘው የሳውዲዓረቢያ ኤምባሲ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ መጥራታቸውም ታውቋል፡፡

ሰበር ሰሚ ችሎት የነ አቶ በቀለ ገርባን ይግባኝን እንደማያይ አስታወቀ -እነ አንዱዓለም አራጌም የፊታችን ሰኞ ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርቡ ይጠበቃል

የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት የኦፌኮ-መድረክ ምክትል ሊቀመንበር እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ ላይ እና የኦፌኮ ሌላው አመመራር ወጣት ኦልባና ሌሊሳ የጠየቁትን ይግባኝ ዛሬ ጥቅምት 21 ቀን 2006 ዓ.ም. በዋለው ችሎት የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ የህግ ስህተት የለውም በሚል ሰበር ሰሚ ችሎቱ ይግባኙን ውድቅ አድርጎታል፡፡ አቶ በቀለ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ወንጀል ችሎት በፌደራሉ አቃቤ ህግ በተከሰሱበት የሽብር ወንጀል 8 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደባቸው ሲሆን ፤ ይህን በመቃወምፈደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ጠይቀው ነበር፡፡

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱም በከፍተኛው ፍርድ ቤት የተወሰነውን የ8 ዓመት እስራት ወደ 3 ዓመት ከ7 ወር ዝቅ ማድረጉይታወቃል፡፡ አቶ ኦልባና ሌሊሳም በከፍተኛው ፍርድ ቤት 13 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደባቸውን በይግባኝ ጠቅላይፍርድ ቤቱ ወደ 11 ዝቅ እንዲል አድርጓል፡፡ ይሁን እንጂ እነ አቶ በቀለ ገርባ የተከሰስነው በሐሰት የፈጠራወንጀል እንጂ ምንም የፈፀምነው ወንጀል ስለሌለ፤ አቃቤ ህግም በከሰሰን ወንጀል ያቀረበው ማስረጃ እርስ በርሱየሚጣረስ በመሆኑ ሰበር ሰሚ ችሎቱ በነፃ ሊያሰናብተን ይገባል ሲሉ ይግባኝ ቢሉም ፤ሰበር ሰሚ ችሎቱ በዛሬውጥቅምት 21 ቀን 2006 ዓ.ም. ውሎው የይግባኝ ጥያቄያቸውን ውድቅ አድርጎታል፡፡

በተያያዘ ዜና የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር እና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አንዱዓለም አራጌ ፣ሌላው የፓርቲው ምክር ቤት አባል አቶ ናትናኤል መኮንን፣ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ፣ አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ እናሌሎች የአንድነት ፓርቲ አመራርና አባላት በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እና ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተወሰነባቸውንየጥፋተኝነት ውሳኔ በመቃወም ለሰበር ሰሚ ችሎት ይግባኝ ብለዋል፡፡ በዚሁ መሰረት የፊታችን ሰኞ ጥቅምት 25 ቀን 2006 ዓ.ም. ከቀኑ 8 ሰዓት 6 ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ቀነ ቀጠሮ መሰጠቱንጠበቃው አቶ አበበ ጉታ አስታውቀዋል፡፡

ይህም ለነ አቶ አንዱዓለም ቀጠሮ የመጀመሪያው የሰበር ሰሚ ችሎት ቀነ ቀጠሮ መሆኑ ታውቋል፡፡ አቶ አንዱዓለምአራጌ በከፍተኛው እና በጠቅላይ ፍርድ ቤት ዕድሜ ልከል ፅኑ እስራት ሲፈረድበት ጋዜጠና እስክንድ ነጋ ደግሞ 18 ፅኑ እስራት ፍርድ በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ መፅናቱ ሲታወቅ የሌሎችም እንዲሁ መሆኑም አይዘነጋም፡፡

ፖሊስ በቦምብ ፍንዳታ ህይወታቸው ያለፈው ሶማሊያውያን አሸባሪዎች ናቸው ሲል መናገሩ ተጠቆመ

ጥቅምት3 ቀን 2006 .. በአዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሩዋንዳ ማዞሪያና ቦሌ ሚካኤል መግቢያ አካባቢ በቦንብ ፍንዳታ ህይወታቸው ያለፈው ሁለት ሶማሊያውያን ሽብርተኞች መሆናቸውን ማረጋገጡን፤ የፌደራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል ማስታወቁን ሪፖርተር በጥቅምት 6 ቀን 2006 .. እትሙ ዘግቧል ፡፡ የአንድግለሰብሰርቪስቤትተከራይተውከነበሩትሶማሊያውያንመካከልአንደኛው20 ቀናትበላይየቆየሲሆን፤ሌላኛውፍንዳታውከመድረሱበፊትከሁለትሰዓታትበፊትየደረሰመሆኑንግብረኃይሉማረጋገጡንአስረድቷል፡

ሽብርተኛ የተባሉት ሶማሊያውያን ካፈነዱት ቦምብ በተጨማሪ መጠናቸው ያልተገለፁ ቦምቦችና አንድ ሽጉጥ ከሁለት ካርታ ጥይት ጋር መገኘቱን፣ የፈንጅ ማቀጣጠያና የአደጋ መከላከያ ጃኬቶች ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ማሊያና ቀበቶዎች መገኘታቸውም ተጠቁሟል፡፡ እንደሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ከሶማሊያውያኑ ጋር ቀጥታ ግንኙነት አላቸው የተባሉ 3 ተጠርጣሪዎችና የቤቱ አከራይ በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑንም ግብረ ኃይሉ አስታውቋል፡፡

የአደጋውን መንስኤና አጠቃላይ ስለነበረው ሁኔታ ፖሊስ መረጃ እያሰባሰበ በመሆኑ ዝርዝር መረጃ ለመስጠት እንደማይችሉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ይህደጎ ስዩም ለሪፖርተር የገለፁ ቢሆንም፤ የፌደራል ፖሊስ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል ግለሰቦቹ ሽብርተኛ መሆናቸውን ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የውስጥ አዋቂ ምንጮች እንደጠቆሙት ከሆነ የፍንዳታው ቅንብር ኢህአዴግ ቀደም ሲል ልክ ጨዋታው ሲያልቅ በተለይ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ካሸነፈ ስታዲየም አካባቢ በማፈንዳት የድርጊቱ ፈፃሚዎች የትጥቅ ትግል እያደረጉ ያሉ ተቃዋሚዎች እና የኃይማኖት አክራሪዎች ናቸው ለማለት አቅዶት የነበረውን ሆን ብሎ ግቡ ሳይሳካ ሲቀር በበሌላ ቦታ ማፈንዳቱን የከዚህ ቀደም የኢህአዴግን ድርጊት እያመሳከሩ ያስታወሱ አልታጡም ፡፡

በተለይም በፍንዳታው ዓለም አቀፉ ማኀበረሰብ የታሰሩ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ላይ መንግስት የወሰደውን እርምጃ እንዲደግፉና እንዲፈጡ የሚጠይቀውን ጫና በመግታት እውቅና ለማግኘት ታቅዶ እንደነበር ከኢህአዴግ ውስጥ እየወጡ ያሉ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡

ምንጭ፡- ቃሌ የውይይት መድረክ

 

 

 

የመጅሊስ እና የዑለማዎች ምክር ቤት የይፍረሱ ክስ ለሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርብ ተገለፀ

የኢትዮጵያ እስልምና እና የዑለማዎች ምክር ቤት ይፍረሱ በሚል የቀረበው አቤቱታ ውድቅ ከተደረገ በኋላ ፤ በድጋሚ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚቀርብ ኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ጥቅምት 6 ቀን 2006 ዓ.ም. ባወጣው እትሙ አስነብቧል፡፡

muslimsየታሰሩት የኢትዮጵያ ሙስሊም ችግሮች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ጠበቃ ተማም አባ ቡልጉ እንደተናገሩት፤ የተጀመረው ክስ ለመስከረም 27 ቀን 2006 ዓ.ም. ድጋሚ ያስቀርባል አያስቀርብም የሚለውን ለማየት እንደነበር ተናግረው ፤ ጉዳዩ ተብራርቶ በመቅረቡ ለማክሰኞ ጥቅምት 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ሰበር ሰሚ ችሎት እንደሚሰየም ጋዜጣው ቢዘግብም የማክሰኞ ችሎት ውሎውን በመለከተ ግን ያለው ነገር የለም፡፡

እንደጋዜጣው ዘገባ ከሆነ ፤ ዑለማዎች ምክር ቤት በራሱ በእስልምና ጠቅላይ ጉባዔዎች ስር ያለ በመሆኑ እና የነዚህ የበላይ ደግሞ መጅሊሱ በመሆኑ ዑለማዎች ምክር ቤት የማስመረጥ መብት የለውም የሚለው የክሱ አንዱ ጭብጥ መሆኑን ጠበቃ ተማም መናገራቸው ተዘግቧል፡፡ እንደጠበቃ ተማም ገለፃ፤ ዑለማዎች ምክር ቤት ምርጫ ያካሄደው የራሱ የሆነ ህጋዊ ሰውነት ሳይኖረው ነው፡፡ ምርጫውን የማካሄድ ስልጣን የዑለማዎች ምክር ቤት ሊሆን አይችልም፡፡

“ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ መሞታቸው ተነግሮናል” አቶ ስብሃት ነጋ

በኢትዮ – ኤርትራ ጦርነት ወቅት ያበሩት የነበረው የጦር አውሮፕላን ተከስክሶና ቆስለው በሻዕብያ እጅ ለሁለተኛ ጊዜ የወደቁት ጀግናው ኢትዮጵያዊ ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ በኤርትራ እስር ቤቶች በስቃይ ቆይተዋል፡፡

colonel bezabehጦርነቱ አብቅቶ ሁለቱ አገሮች የጦር ምርኮኞቻቸውን ሲቀያየሩ የኢትዮጵያ መንግስት በኮሎኔሉ ጉዳይ ገፍቶ መሄድ ባለመቻሉ በዛብህ ወደ አገራቸው ሳይመለሱ በኤርትራ እስር ቤት መቅረታቸውን የመንግስት ተቃዋሚዎች ይናገራሉ፡፡
የኮሎኔሉ ቤተሰቦች ደህንነታቸውን ይሰሙ የነበሩት ከአለም አቀፍ ቀይ መስቀል ሰራተኞች የነበረ ቢሆንም ግንኙነቱ መቋረጡን ለአብራሪው ቤተሰቦች ቅርበት ያላቸውና የኮሎኔሉ ወንድም ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ለላይፍ መጽሔት ሰጥተውት በነበረ ቃለ ምልልስ መናገራቸው ይታወሳል፡፡

የኮሎኔሉ ቤተሰቦች በተለያዮ ጊዜያት ወደ መንግስት አቤት በማለት አብራሪውን በዲፕሎማሲ ጥረት ከእስር እንዲያስፈቱ ሲወተውቱ ቢቆዮም መኖር አለመኖራቸውን እንኳን የሚያረጋግጥላቸው እስከማጣት መድረሳቸው ጉዳዮን ለፈጣሪ ከመስጠት የዘለለ አማራጭ እንዳይኖራቸው አድርጓል፡:

የኢትዮጵያ የሰላምና ልማት ኢንስቲትዮትን የሚመሩት የቀድሞው የህወሃት ነባር ታጋይ አቶ ስብሃት ነጋ አሜሪካን አገር ጎራ ባሉበት አጋጣሚ ከገዛ ፓልቶክ ሩም ተሳታፊ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ‹‹ኮሎኔል በዛብህ ጴጥሮስ መሞታቸው ተነግሮናል፡፡አሁን እየጠየቅን የምንገኘው ከሞቱም ሬሳቸውን እንዲያሳዮንና የአሟሟታቸውን ምክንያት እንዲነግሩን ነው፡፡››በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡የፓልቶኩ አቅራቢም በኮሎኔሉ ሞት የተሰማትን ሀዘን በፓልቶኩ ስም ገልጻለች፡:

የስብሃትን ንግግር ተከትሎ የኮሎኔሉ ቤተሰቦች በስብሃት የተነገረውን ከዚህ ቀደም መስማታቸውን ለማረጋገጥ ሞክረናል፡፡ የኮሎኔሉ ቤተሰቦች በዛብህ ሞተዋል ተብለው በይፋ አለመረዳታቸውን ባደረግነው የማጣራት ሙከራ ለማወቅ ችለናል፡፡ ስብሃት ነጋ በኤርትራ 27 የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን የጦር ምርኮኞች እንደሚገኙ በቃለ ምልልሳቸው አስታውቀዋል፡፡

ምንጭ፡- ዘ-ሐበሻ ድህረ ገፅ