Teddy Afro chosen for World Cup 2014 Official Singer for Africa
In the grand tradition of music for the 2014 FIFA World Cup, the most Ethiopian young popular singer Tewodros Kassahun (Teddy Afro ) has been chosen to represent the world’s most popular sports competition. Teddy Afro’s Song will be featured as the official song for the 2014 World Cup for Africa.
According to the source Teddy afro was selected by Coca Cola to represent Africa for the 2014 FIFA World Cup song. It seems like Teddy Afro took Ethiopia to world cup already.
Teddy Afro’s finished Song and Video Clip that was shot in Kenya will be available world wide very soon.
ነፍስህን በገነት ያኑራት
ብስራት ወ/ሚካኤል
ብዙ ተስፋ ጥለን በህይወት ልናይህ
የጀመርከው አልቆ በለዛ አንደበትህ
ልናደምጠው ነበር አዲሱን ስራህን
ተስፋ ሆኖ ባይቀር ምኞት ቢሰምርልን
ይሁና…ምን ይደረጋል ከቁጭት በቀር
የሚወዱትን ማጣት እየጓጉ ማረር
በቃ እውን ሆነ ማለት ነው?
ዳግም ከድምፁ ውጭ በመድረክ ላናየው
ኦ…አንተ ሞት ለካ እንዲህ ጨካኝ ነህ
ተወዳጁ ኢዮቤን እንዲህ ትለያለህ
አሁን ምን ይባላል…አጣንህ በህይወት
በቃ ኢዮቤዬ… ነፍስህን ፈጣሪ በገነት ያኑራት
(ለድምፃዊ ኢዮብ መኮንን ነሐሴ 13 ቀን 2005 ዓ.ም.)
ወጣቱ ወዴት እየተመራ ነው?
ብስራት ወ/ሚካኤል
ልማት ትርጓሜው እጅግ ሰፊ ቢሆንም ጥቅል ሐሳቡ ግን ለሰው ልጆችም ሆነ የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ በማኀበረሰቡ ዘንድ ይሁንታን ያስገኘ ለኑሮ ተስማሚ ሁኔታን በመፍጠር ውጤታማ የሆነ ተጨባጭ እውነታን ያዘለ ክንውን ነው፡፡ ይህም ሰብዓዊና ቁሳዊ ይባላል፡፡ ይህን በተመለከተ በተለይ ሰብዓዊ ልማት የሚባለው ቁሳዊ የሚባለውን ልማት ሊያመጣ የሚችል የሰው ልጆች የባህሪ አስተሳሰብ አዎንታዊ ለውጥ ነው፡፡ ይህ ለውጥ የማኀበረሰቡን በጎ አሴቶችን አጠናክሮ በመቀጠል አሉታዊ የሚባሉትን በማረምና አዳዲስ አዎንታዊ ለውጦችን ከልማዳዊ አኗኗር ጋር በማስማማት በስልጣኔ ቀላልና ምቹ ሁኔታን መፍጠር ነው፡፡ ያኔ ቁሳዊ ልማቱን በሚፈለገው ደረጃ ማምጣት ይቻላል፡፡ የዚህ ልማት ውጤታማ ተግባርና የስልጣኔ ዝመና ሽግግር ትልቁን ሚና የሚጫወተው ወጣቱ ሲሆን ለዚህም አበረታች የሞራል ስንቅ ያስፈልጋል፡፡
በተለይ በኢትዮጵያ ከሀገሪቱ አብላጫው የህዝብ ቁጥር ልቆ የሚታየው ወጣቱ ነው፡፡ የዛን ያህል ደግሞ ከምርታማነት ይልቅ ጥገኛ እንዲሆን የተፈረደበት ይመስላል፡፡ በተለይ በአሁን ወቅት በኢትዮጵያ የራሱን ዕድል በራሱ መወሰን ተስኖት ሌሎች የሚመርጡለትን፣ የመረጡለትን በመጠበቅ ጊዜውን ሲያባክን ይታያል፡፡ ይህ ማለት ግን አኩሪ ተግባር እየፈፀሙ ያሉ ወጣቶች ጭራሽ የሉም ማለት አይደለም፡፡ ይሁን እንጂ ከለው ቁጥር አንፃር ሲታይ አብዛኛው ወጣት በብዙ ነገሮች ጥገኛ እንዲሆን በመገደዱ እራሱን እንዳይመለከት ጋርዶታል፡፡
ድሮ ድሮ እንኳን ስለራሱ፣ ስለሀገሩ ከዛም አለፍ ሲል ስለሌሎች ይጨነቅ የነበረው ወጣት ዛሬ ስለራሱ በራሱ መወሰን ተስኖት የተመረጠለት ካልተስማማው የመጨረሻ ምርጫውን ስደት ሲያደርግ ይስተዋላል፡፡ በዚህም መሐል ህጋዊና ህገወጥ የሚል ስያሜ ይሰጠዋል፡፡ ይሁን እንጂ ለስደት የዳረገውን ምክንያት ግን ደፍሮ የሚገልፅ አካል አልተገኘም፡፡ እንግዲህ እንዲህ የተፈረደበትን ወጣት ሀገር እያሳጡት ሀገር ተረካቢ እየተባለ ይቀለድበታል፡፡
ወጣትነት እጅግ ፈተና የበዛበት የተፈጥሮ የእድሜ ሂደት አካል ቢሆንም በርካታ ውጤታማ ስራዎችን ለመስራት ግን ከየትኛውም የዕድሜ ክልል የተሻለ ነው፡፡ የመኖሪያም ሆነ የመዋያ ምርጫው በሌሎች መልካም ፈቃድ ላይ ብቻ የተወሰነ በመሆኑ በተለይ በኢትዮጵያ ያለው ክስተት ወጣቶች ሆን ተብሎ ምርታማ እንዳይሆኑ የሚሰራ ይመስላል፡፡ ለዚህም ማረጋገጫ ይሆነን ዘንድ ጥቂቶቹን እንይ፡፡
የወጣት ማዕከላት
ቀደም ባለው የደረግ ስርዓት ግልፅና ቀጥተኛ ሶሻሊስት የነበረ ቢሆንም ወጣቱን በእስፖርትና በሌሎች የኪነ ጥበብ ዘርፎች ለማጎልበት ይረዳ ዘንድ በርካታ የተለያዩ የወጣት ማዕከላት ነበሩ፤ አሁን በነበሩ ቀረ እንጂ፡፡ በወቅቱ በተለያዩ ከተሞች ከስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ እስከ ሙዚቃና ቴአያትር (ድራማ መለማመጃ) በየከተማ ቀበሌው ይገኝ ነበር፡፡ለወጣቶቹ ታስቦ በተሰሩት ሜዳዎችና አዳራሾች ወጣቱ በአግባቡ ይጠቀምበት የነበረ ቢሆንም ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ነፃ የሐሳብ መንሸራሸርን በተመለከተ ግን ከስርዓቱ ውጭ እንደማይፈቀድ በግልፅ ስለሚታወቅ ጎጅ ቢሆንም ብዙም የሚገርም አይደለም፡፡
ዛሬ ደግሞ በአንፃሩ የነበሩ ሜዳዎች ዳግም ባናያቸውም በወጣቱ መዝናኛ ሰም የኢህአዴግ ካድሬ መመልመያ ሆነው አርፈዋል፡፡ የወጣት ማዕከል ተብሎ በተሰሩ አዳራሾች ምንም ከቀድሞ የተለየ ነገር የለም፡፡ ምክንቱም ዛሬም በአዳራቹ ስለ ኢህአዴግ ጥሩነት ለማውራትና የርካሽ ባዶ ፖለቲካ መጠቀሚያ ከመሆን ውጭ ወጣቱ ነፃ የሆነና ያመነበትን ርዕስ አንስቶ መወያየት አይችልም፡፡ ይህ የሆነው ግን በህግ ሳይሆን ከመጋረጃ በስተጀርባ ባልተፃፈው ትዕዛዝ ነው፡፡
በተለይ በአዲስ አበባ በርካታ የቀበሌ አዳራሾች ቢገነቡም እየሰጡት ያለው አገልግሎት ግን ሁሉንም ወጣት ሊያካትት በሚችል የተለያዩ ሐሳቦች ሊንሸራሸሩ በሚያስችል ሁኔታ ሳይሆን በኢህአዴግ ጥላ ለተሰበሰቡት ብቻ ነው፡፡ እንዲህም ቢሆን የሚሰጡት አገልግሎት ቢበዛ ቤተመፅሐፍ፣ ጂም እና የገላ መታጠቢያ አገልግሎት ነው፡፡ በዚህም የወጣቱ ፍላጎት በሁሉም የአዲስ አበባ ከተማም ይሁን በሀገር አቀፍ ምርጫው ሁሉን ያሳተፈ የወጣቱ ነው ማለት አይቻልም፡፡ ይህ ካልሆነ ደግሞ ወጣቱ በፍላጎቱ በልማት ላይ ተሳታፊ ነው ማለት አይቻልም፡፡ምክንያቱም ቁሳዊ የአዳራሽ ግንባታ የወጣቱን አስተሳሰብ በመቀየር ሰብዓዊ ልማት ማምጣት አልቻለምና፡፡
አስተሳሰብን ያህል ነገር ሁሉም በሌሎች ፍላጎትና ምርጫ ተፈጥሮን በሚሽር መልኩ አንድ እንዲሆን እየተደረገ ባለበት ሁኔታ ሁሉን አቀፍ ተሳትፎዓዊ የተደረገበት አሳታፊ ቁሳዊ ልማትን ማምጣት አይቻልም፡፡ ሰርተናል እየተባለ የሚዘፈንለት ቁሳዊ ልማትም ቢሆን የወጣቱን የመንፈስ ልዕልና ሊገነባ ባልቻለበት ሁኔታ በሀገሪቱ ላይ ሁለንተናዊ እምርታ ለውጥ ማየት ይናፍቃል፡፡ ቀድሞ በየአካባቢው የነበሩ ሜዳዎችም ቢሆኑ አንዳንዶቹ በነበሩበት ቢቀጥሉም አብዛኞቹ ባለመኖራቸው፣ አዳዲስ የመኖሪያ ቤት ግንባታ የተደረገባቸውም ሆነ እየተደረገባቸው ያሉ አካባቢዎች የወጣቶች ስፖርት ማዘውተሪያዎች ባለመታየታቸው ዋቱን ወደ አልባሌ ቦታ እንዲውል እያስገደዱት ይገኛሉ፡፡
ጎጂ የደባል ሱስ ግብዣ
በአሁን ሰዓት ወጣቱ በራሱ ጉዳይ እራሱ እንዲወስን ከማድረግ ይልቅ በደባል ሱስ ጥገኛ እንዲሆን የሺሻና ጫት ግብዣ እየቀረበለት ይገኛል፡፡ ይሄም በፊት እንደ ነውር ይታይባቸው በነበሩ አካባቢዎች ሳይቀር ዛሬ ዛሬ እንደመልካም እየታየ እስከ ዩኒቨርስቲዎች መዝለቁ የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡ እነኚህን ድርጊቶች የሚያበረታታ የመንግስት አካል ባይኖር ኖሮ መኖሪያ መንደር ድረስ ዘልቀው ባልታዩ ነበር፡፡
ከከፍተኛ የትምህርት ተቋም የተመረቁና የሚመረቁ ወጣቶችም ቢሆኑ ከ15ዓመታት በላይ በእውቀት ግብይት በትምህርት ቢያሳልፉም ዛሬ ግን 15 ቀናት በማይፈጅ ስልጠና ያውም ጥቂቶችን በኮብል ስቶን ድንጋይ ጠረባ ስራ እንዲሰማሩ ይደረጋል፡፡ በርግጥ ማንኛውም ሙያም ሆነ ስራ የሌሎችን ሰዎች መብትና ጥቅም እስካልነካ ድረስ የሚናቅ ባይሆንም ለዘመናት ያካበቱት እውቀት ግን ሜዳ ላይ ሲወድቅ የሀገር ሀብት በከንቱ መባከኑን ማሳየቱ አይቀርም፡፡ በአሁን ወቅትም የያዝነው 2005ዓ.ም.ን ጨምሮ በየዓመቱ ከ 80 ሺህ በላይ የሀገሪቱ ወጣቶች በተለያየ የትምህርት ዘርፍ ቢመረቁም በሙያቸው የሚሰማሩት ግን 10ሺህ እንዳማይሞሉ ይገለፃል፡፡ ይሄ ደግሞ የእውቀት፣የገንዘብና የጉልበት ብክነት መሆኑ ግልፅ ነው፡፡
በሙያቸው ተደራጅተው የስራ ዕድል እንዳይፈጥሩም ስርዓቱ እና የስነ ህዝብ ፖሊሲው ዜጎችን ሙሉ በሙሉ የመንግስት ኢኮኖሚ ጥገኛ ስላደረገ በሚፈልጉት ሙያ መሰማራት አይችሉም፡፡ ይህንንም ለመቅረፍ የገንዘብ ብድር ቢፈልጉ እንኳ የግድ አብዮታዊ ዴሞክራሲን ተቀብለው በኢትዮጵያዊነት ሳይሆን በኢህአዴግ አባልነት ቅድመ ሁኔታ በየቀበሌ ያሉ ተራ ካድሬዎች ከላይ በሚወርድ መመሪያ መሰረት ለማደራጀት ይሚክራሉ፡፡ ውጤቱ ግን ወጣቱን አምራች ኃይል ከማድረግ ይልቅ የሙያና የኢኮኖሚ ነፃነት ስለሌለው ጥገኛ እንዲሆን አስችለውታል፤እያስቻሉትም ነው፡፡ ይሄ ካልተቀየረ ደግሞ የሀገሪቱ ወጣት ጊዜውን፣እውቀቱንና ጉልበቱን በከንቱ እንዲያባክን ያደርጉታል፡፡
ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ በየመንደሩ እየፈሉ ያሉት የአልኮል መጠጥ ቤቶችና ጭፈራ ቤቶች አንዱ የልማት አካል እንጂ የሰብዓዊ ልማትን ወደ ኋላ የሚያስቀር ተደርጎ አልተወሰደም፡፡ በዚህ ምክንያት ወጣቱ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ የሰራበትንም በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲያውል ምቹ ሁኔታ እንኳ ሲፈጠርለት አይታይም፡፡
በአንፃሩ ደግሞ ለወጣቱ እጅግ ጠቃሚና አስፈላጊ እንደሆኑ የሚታወቁት የሐሳብ የበላይነት ላይ የሚደረጉ ውይይቶችና ክርክሮች ቦታ ባለመሰጠታቸው እንደ ሚዩዚክ ሜዴይ የመሳሰሉት የንባብን ባህል ለማዳበር የሚረዳው የመፅሐፍ ሐሳብ መወያያ አዳራሽ አጥተው አምስት ኪሎ በሚገኘው በጠባቧ ብሔራዊ ሙዝየም አዳራሽ ማየት ልማት ወዴት ወዴት ያሰኛል፡፡ ባንፃሩ አብዛኛውን ጊዜ የገዥው ኢህአዴግ ካድሬዎች መፈንጫ እየሆነ ያለውና በህዝብ አንጡራ ሃብት የተገነቡት የቀበሌ/የወረዳ አዳራሾች ደግሞ አብዛኛውን ጊዜ ከኢህአዴግ ስራና ካድሬዎች በስተቀር ኸረ የሰው ያለህ እያሉ ይገኛል፡፡ ይህ ሁሉ ታዲያ ለሰብዓዊ ልማት ትኩረት ባለመሰጡ ነገ ሀገር ተረካቢ በሚባለው ወጣት ላይ ይነገድበታል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በፊት የወጣቶች መዝናኛ የነበሩ የስፖርት ሜዳዎችና የመናፈሻ ቦታዎች አንዳንዶቹ የህንፃ ግንባታ ሲሰራባቸው እንደነ ሂልተን አዲስ ሆቴል ፊትለፊት የነበሩ መናፈሻዎች ደግሞ ተከልለው ወጣቶች ዝር እንዳይሉባቸው ተደርገዋል፡፡
ከሌሎች መጠበቅንና መቀበልን መምረጥ
የተሻለ ነገርን በራስ ከመወሰን፤ እንዲሳካም ከመጠየቅ ይልቅ በሌሎች ላይ ጥገኛ በመሆን በሁሉም ነገር የመጠበቅና የመቀበል ብቻ አዝማሚያ በስፋት በወጣቱ ያስተዋላል፡፡ በዚህም የራሱን ጉዳይ ሌሎች እንዲወስኑለት በመፍቀዱ የራሱን ሚና አሳልፎ እየሰጠ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ምርጫውን ከመፈለግ ይልቅ የመጣውን ብቻ የመቀበል ጉዳይ በስፋት ይስተዋላል፡፡
አማራጭ ሐሳቦችን ከራስ ጋር አስማምቶ ለመያዝም ሆነ የራስን ምርጫ ለማስተናገድ ይረዳ ዘንድ ነፃ የሆነ የሐሳብ ፍጭት ዕድል በመነፈጉ አሉታዊም ቢሆን ተቀብሎ የራስ ማድረግ እንደ አዋቂነትና ብልህነት እየተወሰደ ይገኛል፡፡ ይሄ ደግሞ የትውልድ የአስተሳሰብ ብክነትንና ምክነትን በማንፀባረቅ ተተኪው ትውልድ ከማለት ይልቅ ጠባቂው ቢባል የሚስማማው ይመስላል ፡፡
ከላይ ለተጠቀሱት ችግሮች ዋነኛ ምክንያት ደግሞ በተለይ በወጣቶች ላይ እየተሰራ ያለው ሰብዓዊ ልማት በቁሳዊ በመሸፈኑ የሚመጣ ኋላቀር እሳቤ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ገዥው ስርዓት የልማትን አስፈላጊነትና ምንነት በቅጡ ካለመረዳት የሚመጣ ደጋማ እሳቤ ሲሆን እራሱ ወጣቱም ቢሆን በእራሱ ላይ አሉታው ድርሻ እንዳለው ሊዘነጋ አይችልም፡፡ ስለዚህ እምርታዊ |የሀገር ዕድገትና ለውጥ ለማምጣትና ሁሉን አቀፍ ገቢራዊ ልማት ለማስመዝገብ ቅድሚያ ሰብዓዊ ልማት መቅደም ይኖርበታል፡፡ ያኔ ቁሳዊ ልማትን በሚፈለገው መጠንና ዓይነት ማምጣት ይቻላል፡፡
The Role of Development Aid in fuelling Corruption and Undermining Governance in Ethiopia
July 5, 2013
Seid Hassan- Murray State University-USA
My own research as well as the research of other scholars show that the control of donor resources allowed the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF), not only to consolidate political power that it seized in 1991, but also virtually penetrate the Ethiopian society at the grassroots level and expand its repressive and predatory tentacles.*
This paper also makes use of my ongoing studies regarding corruption in Ethiopia. The concluding part of the paper ties the corruptive practices of the TPLF/EPRDF when it was a liberation front (that is, the humanitarian aid-corruption nexus) with its current and similar activities (that is, the capture and misuse of development aid.) The paper exclusively focuses on the development aid -corruption nexus.
The paper uses theme-based cases (heavily donor-funded projects) in order to illustrate the captured nature of development aid and extent of corruption in…
View original post 789 more words
“ኢህአዴግ አንገቱን ታንቋል”
Source: www.goolgule.com
ዓለም ባንክ ርምጃ ለመውሰድ ጫፍ ደርሷል ኢህአዴግ ላይ ቀደም ሲል ሲቀርቡበት ከነበሩት ሪፖርቶች በተለየ ጥቅሞቹ ላይ ያነጣጠሩ አስደንጋጭ መረጃዎች እንደወጡበት ተሰማ። መረጃው የኢህአዴግን አንገት የማነቅ ያህል እንደሚቆጠርና ለተግባራዊነቱ የተንቀሳቀሱትን አካላት “የአስተዋይነት” ትግል ውጤት እንደሆነ ተጠቁሟል…
ኢህአዴግ በህዝብ ስም በብድርና በርዳታ የሚያገኘውን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ለፖለቲካ ስራ እንደሚያውለውና ለአፈና ተቋማቱ ማጠናከሪያ እንደሚጠቀምበት የተከሰሰበት ሪፖርት መጠናቀቁን የገለጹት የጎልጉል ታማኝ ምንጮች ናቸው። ምንጮቹ እንዳሉት ሪፖርቱ የቀረበለት የዓለም ባንክ በቅርቡ መረጃውን ተቀብሎ ርምጃ ይወስዳል ተብሎ ይጠበቃል። ኢህአዴግ ርምጃው ተግባራዊ ከመሆኑ በፊት ለማክሸፍ የተለመደውን ሩጫ መጀመሩ ተሰምቷል።
በኢህአዴግ ላይ የቀረበው ሪፖርት የመፍትሄ ሃሳብም ያካተተ እንደሆነ የተናገሩት የጎልጉል ምንጮች፣ የዓለም ባንክ የሥራ አስፈጻሚ ቦርድ ሪፖርቱን ሙሉ በሙሉ እንደሚቀበለውና ይፋ እንደሚያደርገው አስረድተዋል። የምርመራ ዘገባውን ስላጠናውና ስላቀረበው የኢንስፔክሽን ተቋምና የስራ ተሞክሮ በቂ ግንዛቤ ያላቸው እነዚህ ክፍሎች እንደሚሉት የዓለም ባንክ ቦርድ ይህ ተቋም ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ያቀረባቸውን ሪፖርቶች ላለመቀበል አንገራግሮ እንደማያውቅ ያስረዳሉ።
በሚመሩት ህዝብ ላይ ግፍ የሚፈጽሙ መንግስታትና በልማት ስም የሰብዓዊ መብት ጥሰት የሚያካሂዱ አገራት የሚፈጸሙ…
View original post 1,048 more words
