ኣሸጎዳ የንፋስ መብራት ማመንጫ ሃይል ዲናሞ በመቃጠሉ ምክንያት ከጥቅም ውጭ ሆነ
በመቀሌ ምስራቃዊ ክፍል የሚገኝ የኣሸጎዳ በንፋስ የሚሰራ ኤለክትሪክ ማመንጫ ሃይል በዲናሞ መቃጠል ምክንያት ከስራ ውጭ መሆኑ ታውቋል። የተቃጠለው ዲናሞ 150 ሜጋዋት የማመንጨት ኣቅም የነበረው ሲሆን ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት በመቃጠሉ ሃይል የማመንጨት ኣቅሙ ሙሉ በሙሉ ማቆሙ ታውቋል።
የተቃጠለው ዲናሞ ቅያሪ በሃገር ውስጥ እንደሌለና ከፈረንሳይ ሃገር እንደሚመጣ ታውቋል። የህወሓት የ40 ዓመት የልደት በዓል እንደ ታላቅ ውጤትና ማጣፈጫ ተደርጎ ሊወሰደ ታስቦ የነበረ ሲሆን ባልታወቀ ምክንያት መቃጠሉ በክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት ከፍተኛ ቁጣና ድንጋጤ መፍጠሩ ታውቋል።
የትግራይ ባለስልጣናት እንደ ግዝያዊ መፍትሄ ኣድርገው የወሰዱት የየካቲት በዓል እስኪያልፍ ከፈርንሳይ በክራይ እንዲመጣና ብልሸት እንዳልደረሰው ኣስመስሎ በማሳለፍ በዓሉ ከተጠናቀቀ በሗላ ዲናሞው ወደ ፈረንስይ እንዲመለስ የሚል ትእዛዝ ኣስተላልፈዋል።
የህወሓት ባለስልጣናት የየካቲት በዓል ታዳሚዎች ኣሳፋሪ በሆነ ድራማ ኣጭበርብረው ለመመልስ ከፈረንሳይ ዲናሞ ተከራይተው ካሳዩሗቹ በሗላ ተመልሰው ወደ መጣበት ይመልሱታል። ህወሓት የዲናሞው መቃጠል ለየካቲት በዓል ማክበርያ ካወጣችው 1 ቢልዮን ብር ወጪ የምታወጣው ተጨማሪ ግዙፍ ብር ይሆናል።
በሆሳዕና ከተማ የመብራት ኃይል ገመድ ተበጥሶ የሰው ህይወት አጠፋ
በደቡብ ክልል ሆሳዕና ከተማ የኤልክትሪክ ገመድ ተበጥሶ የ13 ዓመት ልጅ ህይወት ማጥፋቱ ተገለፀ፡፡ አደጋው የደረሰው በጎፈር ሜዳ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ቦቢቾ በተባለ ቀበሌ ሰኞ መጋቢት 8 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት ለረጅም ጊዜ ምሰሶው ሊወድቅ የደረሰ የኤሌክትሪክ ገመድ ተበጥሶ አንድ የ13 ዓመት ልጅ ከመኖሪያ ቤቱ ወደ ትምህርት ቤት እየሄደ ሳለ በደረሰ አደጋ ወዲያው ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል፡፡ 
አዲስሚዲያ ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገለፁት ከሆነ ምሰሶው በመንገድ ጥገና ቁፋሮ ምክንያት በመላላቱ የኤሌክትሪክ ገመዱ ረግቦ እንደነበርና ይህንንም በመፍራት በተደጋጋሚ ለከተማው መስተዳደርና በከተማው ለሚገኝ የመብራት ኃይል ዲስትሪክት ቅሬታ ቢያቀርቡም ሰሚ ባለማግኘታቸው አደጋው መድረሱን አስታውሰዋል፡፡ ከሟቹ ልጅ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ኮርፖሬሽን ላደረሰው የቸልተኝነት አደጋ ምን ምላሽ እንዳለው ለማጣራት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወደ ሆኑት አቶ ምስክር ነጋሽ ደውለን ለማጣራት ብንሞክርም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡
