Tag Archives: Ethiopian Muslims Community Committee

ሰበር ዜና፤ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ተፈረደባቸው

አዲስ አበባ ቦሌ ክፍለ ከተማ ሲኤምሲ በሚገኘው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ምድብ ችሎት፤ ዛሬ ሐምሌ 27 ቀን 2007 ዓ.ም. በ አቡበከር አህመድ የክስ መዝገብ ክስ ተመስርቶባቸው ከ3 ዓመታ በላይ ጉዳያቸው በፍርድ ቤት ሲታይ የነበረው የኢትዮጵያ ሙስሊሙ ማኀበረሰብ መፍትሄ አፈፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ የቅጣት ውሳኔ አስተላለፈ፡፡ የኮሚቴው አባላትም ከ7 ዓመት እስከ 22 ዓመት በሚደርስ ፅኑ እስራት እና ለ5 ዓመታት ከማኀበራዊ መብቶቻቸውም እንዲታገዱ የቅጣት ውሳኔ መተላለፉ ተጠቁሟል፡፡

 የኢትዮጵያ ሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት


የኢትዮጵያ ሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት

ዛሬ በተላለፈባቸው የቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸው 18ቱ የኮሚቴው አባላት፡-
አቡበከር አህመድ፣ አህመዲን ጀበል፣ ያሲን ኑሩ እና ካሚል ሸምሱ እያንዳንዳቸው 22 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል፡፡
በድሩ ሁሴን፣ ሳቢር ይርጉ፣ መሃመድ አባተ፣ አቡበከር አለሙ እና ሙኒር ሁሴን እያንዳንዳቸው 18 ዓመት እስር ሲፈረድባቸው፤
ሼህ መከተ ሙሄ፣ አህመድ ሙስጠፋ፣ ሼህ ሰኢድ አሊ ጁሃር፣ ሙባረክ አደም እና ካሊድ ኢብራሂም እያንዳንዳቸው 15 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል፡፡
ቀሪዎቹ ሙራድ ሽኩር፣ ኑሩ ቱርኪ፣ ሼህ ባህሩ ኡመር እና ጋዜጠኛ ዩሱፍ ጌታቸው እያንዳንዳቸው 7 ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል፡፡
የዛሬውን ፍርድ በተመለከተም ድምፃችን ይሰማ ተቃውሞውን በመግለፅ፤ የሚከተለውን የትግል ስልት አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመግለፅ 6 ነጥቦች ያሉት የአቋም መግለጫ ማውጣቱን ቢቢ ኤንን ጨምሮ የተለያዩ ዘገባዎች አመልክተዋል፡፡
የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ከመቋቋሙ በፊት በጥር 2004 ዓ.ም. ይፋ ጥያቄ መነሳት የጀመረው በአዲስ አበባ አወሊያ ትምህርት ቤት ጋር ተያይዞ እንደነበር የሚታወስ ሲሆን፤ የተጠ የቁ 3 መሰረታዊ ጥያቄዎች በወቅቱ ምላሽ ባለማግኘታቸው አሁን የተፈረደበት ኮሚቴ ሊቋቋም መቻሉንና ኮሚቴው አባላት ከመታሰራቸው በፊት በመፍትሄው ዙሪያ ከሚመለከታቸው የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች ጋር በይፋ ውይይት ሲደረግ እንደነበር አይዘነጋም፡፡

የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት በተመሰረተባቸው ክስ ጥፋተኛ ተባሉ

አቡበከር አህመድ (የኮሚቴው ሰብሳቢ)

አቡበከር አህመድ (የኮሚቴው ሰብሳቢ)

ከ35 ወራት የፍርድ ሂደት ቆይታ በኋላ ዛሬ ሰኔ 29 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ የወንጀል ችሎት በእስር ላይ ባሉት የኢትዮጵያ ሙስሊሙ ማኀበረሰብ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሜቴ አባላት በሆኑት በእነ አቡበክር አህመድ የክስ መዝገብ የአቃቤ ህግን እና የመከላከያ ምስክሮችን ቃል በንባብ አሰምቶ ማጠናቀቁን ተከትሎ ዛሬ በ18 ተከሳሾች ላይ ፍርድ ሰጥቷል።
ከ1ኛ እስከ 9ኛ ያሉት ተከሳሾች በተከሰሱባቸው በፀረ ሽብር ህጉ አንቀፅ አራት ላይ በተዘረዘሩት መቀስቀስ፣ ማነሳሳት እና ማሴር በሚሉ ወንጀሎች ጥፋተኛ ተብለዋል።

court symbol
ቀሪዎቹ ተከሳሾች በፀረ ሽብር ህጉ አንቀፅ አራት ላይ በተጠቀሰው በመሳተፍ ወንጀል ጥፋተኛ ተብለዋል።
ፍርድ ቤቱ በተከሳሾቹ ላይ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለሀምሌ 27 ቀን 2007 ዓመተ ምህረት ቀጠሮ ሰጥቷል።
ተከሳሾቹ እና አቃቤ ህግ ከሀምሌ 27 ቀደም ብለውም የቅጣት ማቅለያ እና ማክበጃ አስተያየታቸውን እንዲያቀርቡም አዟል።
ፍርድ ቤቱ ዛሬ ጠዋት ከከሳሽና ከተከሳሽ በኩል በተካሄዱ ክርክሮች አምስት ጭብጦችን መመርመሩ ነው የተመለከተው።
ከአምስቱ ጭብጦች መካከል መንግስት በእስልምና ሃይማኖት ጣልቃ ገብቷል አልገባም? የሃይማኖቱ ተከሳሾችን ከፋፍሏል አልከፋፈለም? እና የመጅሊሱ ምርጫ ከህገ መንግስቱ ጋር ተጋጭቷል? አልተጋጨም? የሚሉት ተጠቃሾች ናቸው።
ችሎቱ እነዚህን ጭብጦች ሲመረምር በተለያዩ ሃገራት ከሃይማኖት ጋር በተያያዘ የሚራመዱ አሰራሮችን ማየቱን በችሎት መግለፁ ተጠቁሟል፡፡
ከዚህ ሰፊ ሃተታ በኋላ መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ አለመግባቱን፣ ተከታዮችን አለመከፋፈሉንና የመጅሊሱ ምርጫ ከህገ መንግስቱ ጋር ሳይቃረን በሃይማኖታዊ ስርአት መካሄዱን ከምስክሮችና ከማስረጃ ቃል በማገናዘብ አረጋግጫለሁ ማለቱን ተከትሎ ነው ከሰዓት በኋላ ፍርድ መስጠቱን ኤቢሲ ዘገባ አመልክቷል፡፡