ብስራት ወ/ሚካኤል
ብዙ ተስፋ ጥለን በህይወት ልናይህ
የጀመርከው አልቆ በለዛ አንደበትህ
ልናደምጠው ነበር አዲሱን ስራህን
ተስፋ ሆኖ ባይቀር ምኞት ቢሰምርልን
ይሁና…ምን ይደረጋል ከቁጭት በቀር
የሚወዱትን ማጣት እየጓጉ ማረር
በቃ እውን ሆነ ማለት ነው?
ዳግም ከድምፁ ውጭ በመድረክ ላናየው
ኦ…አንተ ሞት ለካ እንዲህ ጨካኝ ነህ
ተወዳጁ ኢዮቤን እንዲህ ትለያለህ
አሁን ምን ይባላል…አጣንህ በህይወት
በቃ ኢዮቤዬ… ነፍስህን ፈጣሪ በገነት ያኑራት
(ለድምፃዊ ኢዮብ መኮንን ነሐሴ 13 ቀን 2005 ዓ.ም.)