በወለጋ ሻምቡ ወህኒ ቤት አንድ ወታደር ሁለት አለቆቹን ገደለ

ትናንት ህዳር 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት በኦሮሚያ ክልል ወለጋ ውስጥ በሚገኘው ሆሮጉድሩ ወረዳ ሻምቡ ወህኒ ቤት አንድ ወታደር ሁለት አለቆቹን በመሳሪያ ገድሎ እጁን ሰጠ፡፡

ገዳዩ አለቆቹ በተደጋጋሚ በእስረኞች ላይ እና በሌሎች የበታች ሰራተኞች ላይ ጸደጋጋሚ በደል ሲፈፅሙ ይቃወም የነበረ ሲሆን ትናንት ግን እስካሁን በውል ባልታወቀ ምክንያት ሁለቱነብ አለቆቹን መግደሉን ምንጮቻችን ከስፍራው አስታውቀዋል፡፡ የወረዳው ፖሊሶች ዝርዝር መረጃውን እንዲሰጡን ተደጋጋሚ ጥረት ብናደርግም አልተሳካም፡፡

Leave a comment