የቃሊቲ ማረሚያ ቤት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን በምስክርነት እንደማያቀርብ አሳወቀ
የቃሊቲ ማረሚያ ቤት በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በመከላከያ ምስክርነት የተጠቀሰውን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ በምስክርነት እንደማያቀርበው ለልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በደብዳቤ አሳውቋል፡፡ ማረሚያ ቤቱ ታህሳስ 4 ቀን 2008 ዓ.ም ለልደታ ፍርድ ቤት በላከው ደብዳቤ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ‹‹የ18 አመት ፅኑ እስራት የተፈረደበት በመሆኑና ከአሁን ቀደም ምስክር ሆኖ ከማረሚያ ቤቱ ወጥቶ መስክሮ ስለማያውቅ ለመስክርነት ለማቅረብ እንቸገራለን›› ብሏል፡፡

እስክንድር ነጋ ለእነ ዘላለም ወርቃገኘው በመከላከያ ምስክርነት ከተቆጠረ በኋላ ከህዳር 13 ቀን 2008 ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ቀጠሮዎች በምስክርነት ሳይቀር የቀረ ሲሆን ዛሬ ታህሳስ 6 ቀን 2008 ዓ.ም ማረሚያ ቤቱ በላከው ደብዳቤ መሰረት ሳይቀርብ ቀርቷል፡፡ ከአንድ አመት በፊት ከ6 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት ተኩል ለ30 ደቂቃ ሲጠየቅ የነበረው እስክንድር ነጋ በአሁኑ ወቅት እንዳይጠየቅ ተከልክሏል፡፡ በተጨማሪም ማረሚያ ቤቱ በተደጋጋሚ እስክንድር ነጋ የታሰረበትን ክፍል በመፈተሽ መፅሃፍ ቅዱስን ሳይቀር መነጠቁም ይታወሳል፡፡
ምንጭ፡- ነገረ ኢትዮጵያ
Ethiopia: Lethal Force Against Protesters
Military Deployment, Terrorism Rhetoric Risk Escalating Violence
Human Rights Watch
(Nairobi)
Ethiopian security forces have killed dozens of protesters since November 12, 2015, in Oromia regional state, according to reports from the region. The security forces should stop using excessive lethal force against protesters.

Police and military forces have fired on demonstrations, killing at least 75 protesters and wounding many others, according to activists. Government officials have acknowledged only five deaths and said that an undisclosed number of security force members have also been killed. On December 15, the government announced that protesters had a “direct connection with forces that have taken missions from foreign terrorist groups” and that Ethiopia’s Anti-Terrorism Task Force will lead the response.
“The Ethiopian government’s response to the Oromia protests has resulted in scores dead and a rapidly rising risk of greater bloodshed,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director at Human Rights Watch. “The government’s labelling of largely peaceful protesters as ‘terrorists’ and deploying military forces is a very dangerous escalation of this volatile situation.”
Protests by students began in Ginchi, a small town 80 kilometers southwest of Ethiopia’s capital, Addis Ababa, when authorities sought to clear a forest for an investment project. Protests quickly spread throughout the Oromia region, home of Ethiopia’s estimated 35 million Oromo, the country’s largest ethnic group.
They evolved into larger demonstrations against the proposed expansion of the Addis Ababa municipal boundary, known as the “Addis Ababa Integrated Development Master Plan.” Approximately 2 million people live in the area of the proposed boundary expansion and many protesters fear the plan could displace Oromo farmers and residents living near the city.
Since mid-November, the protesting students have been joined by farmers and other residents. Human Rights Watch received credible reports that security forces shot dozens of protesters in Shewa and Wollega zones, west of Addis Ababa, in early December. Several people described seeing security forces in the town of Walliso, 100 kilometers southwest of Addis Ababa, shoot into crowds of protesters in December, leaving bodies lying in the street.
Numerous witnesses told Human Rights Watch that security forces beat and arrested protesters, often directly from their homes at night. Others described several locations as “very tense” with heavy military presence and “many, many arrests.” One student who took part in protests in West Shewa said, “I don’t know where any of my friends are. They have disappeared after the protest. Their families say they were taken by the police.”
Local residents in several areas told Human Rights Watch that protesters took over some local government buildings after government officials abandoned them. Protesters have also set up roadblocks to prevent the movement of military units into communities. Some foreign-owned commercial farms were looted and destroyed near Debre Zeit, 50 kilometers southeast of Addis Ababa, news media reported.
Human Rights Watch has not been able to corroborate the precise death toll and many of the details of individual incidents because of limited independent access and restricted communications with affected areas. There have also been unconfirmed reports of arrests of health workers, teachers, and others who have publicly shown support for the protest movement through photos and messages on social media.
The United Nations Basic Principles on the Use of Force and Firearms by Law Enforcement Officials provide that security forces shall as far as possible apply nonviolent means before resorting to the use of force. Whenever the lawful use of force is unavoidable, the authorities should use restraint and act in proportion to the seriousness of the offense. Lethal force may only be used when strictly unavoidable to protect life.
The Ethiopian government should respect freedom of expression and peaceful assembly, Human Rights Watch said. While police have the responsibility to maintain order during protests, they should only use force when strictly necessary and in a proportionate manner.
Ethiopia’s government regularly accuses people who express even mild criticism of government policy of association with terrorism. Dozens of journalists, bloggers, protesters, and activists have been prosecuted under the country’s draconian 2009 Anti-Terrorism Proclamation.
On December 16, 2015, Prime Minister Hailemariam Desalegn said that the government “will take merciless legitimate action against any force bent on destabilizing the area.” The same day, Getachew Reda, the government communication affairs office minister, said that “an organized and armed terrorist force aiming to create havoc and chaos have begun murdering model farmers, public leaders and other ethnic groups residing in the region.” While there have been some recent reports of violence by protesters, according to information obtained by Human Rights Watch, the protests have overwhelmingly been peaceful.
Ethiopia’s pervasive restrictions on independent civil society and media mean that very little information is coming from affected areas although social media are filled with photos and videos of the protests. Authorities have cut mobile phone coverage in some of the key areas, particularly areas where there is significant military deployment, raising concerns over the potential crackdown. In communities where there is mobile phone coverage, witnesses reported repeated gunfire and a heavy military presence.
The authorities’ response to past protests in Oromia raises serious concerns for the safety of protesters and others arrested, Human Rights Watch said. In Oromia in April and May 2014, security forces used live ammunition against largely peaceful student protesters, killing several dozen people, and arrested hundreds more. Some of those arrested are still detained without charge. Former detainees told Human Rights Watch that they were tortured and otherwise ill-treated in detention. On December 2, 2015, five Oromo students were convicted under the counterterrorism law for their role in the protest movement. There has been no government investigation into the use of excessive force and live ammunition during the 2014 protests.
While both the 2014 and current protests are ostensibly responding to the Addis Ababa expansion plan, they also derive from deeper grievances, Human Rights Watch said. Many Oromos have historically felt marginalized and discriminated against by successive Ethiopian governments, and Oromos are often arbitrarily arrested and accused of belonging to the Oromo Liberation Front (OLF), which waged armed struggle in the past and which the government designates a terrorist organization.
Under the UN Basic Principles on the Use of Force and Firearms, in cases of death or serious injury, appropriate agencies are to conduct a review and a detailed report is to be sent promptly to the competent administrative or prosecutorial authorities. The government should ensure that arbitrary or abusive use of force and firearms by law enforcement officials is punished as a criminal offense. Superior officers should be held responsible if they knew or should have known that personnel under their command resorted to the unlawful use of force and firearms but did not take all measures in their power to prevent, suppress, or report such use.
The Ethiopian government should support prompt, independent investigations into the events in Oromia region, including by UN and African Union (AU) human rights experts on freedom of expression, peaceful assembly and association. Governments and intergovernmental organizations, including the AU, should raise concerns about the excessive use of force against protesters and call on Ethiopia to respect fundamental human rights in its response to the protests, Human Rights Watch said.
“Ethiopia’s security forces seem to have learned nothing from last year’s protests, and, instead of trying to address the grievances that are catalyzing the protests, are shooting down more protesters,” Lefkow said. “Concerned governments and institutions should call on Ethiopia to halt its excessive use of force and stop this spiral into further violence.”
Source: https://www.hrw.org/news/2015/12/18/ethiopia-lethal-force-against-protesters
በኦሮሚያ ያለው ተቃውሞ የቀጠለ ሲሆን፤ በመንግሥት የተገደሉ ሰዎች ቁጥርም 82 መድረሱ ተሰማ
በተለይ ከህዳር 21 ቀን 2008 ዓ.ም. በኦሮሚያ ምዕራብ ሸዋ ጊኒጪ የተጀመረው የተማሪዎች የአዲስ አበባ እና የፊንፊኔ ልዩ ዞን ኦሮሚያ ክልል የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላን ትግበራን በመቃወም እስከ ታህሳሥ 3 ቀን 2008 ዓ.ም. 76 ሰዎች በመንግሥት በተወሰደ ሃይል እርምጃ መገደላቸውን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ መድረክ በበኩሉ መግለጫውን እስኪሰጥ በረደሰው መደረጃ መሰረት በመንግሥት የተገደሉ ሰዎች ቁጥር 32 ደረስው እንደነበር አስታውቋል፡፡ የሟቾቹ ቁጥር ዛሬም የጨመረ መሆኑን መረጃዎች የጠቆሙ ሲሆን፤ የሟጮች ቁጥር ከ82 በላይ መድረሱን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ከተገደሉት መካከልም ከ10ዓመት ህፃን የአንደኛ ደረጃ ተማሪ እስከ 78 ዓመት አዛውንትና የልጆች አባት እንደሚገኙበት መረጃዎች የጠቆሙ ሲሆን፤ በርካታ ሰዎችም መቆሰላቸውን እና መታሰራቸውም ታውቋል፡፡
መድረክ የመንግሥት እርምጃን በማውገዝ ታህሳሥ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. መግለጫ፤ ከሁለት ሳምናታት በላይ በዘለቀው የኦሮሚያ ክልል ከተሞች ተቃውሞ 32 ሰዎች በመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን አስታውቋል፡፡ መድረክ የተገደሉትን ሰዎች ስም ዝርዝር እና አካባቢም በመግለጫው ጠቅሷል፡፡
በክልሉ በተለያዩ ከተሞች እየተካሄደ ባለው ህዝባዊ ተቃውሞ ዛሬ ረቡዕ ታህሳሥ 6 ቀን 2008 ዓ.ም. ድረስ እንደቀጠና በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎችም የተገደሉ እንዳሉ ተጠቁሟል፡፡ በተለይ የተቃውሞ ሰልፉ ዛሬም ከቀጠለባቸው ከተሞቸ መካከል በምዕራብ ሐረርጌ አሰቦት፣ በምበአርሲ አሰላ፣ በምዕራብ ሸዋ ኢጃጂ፣በኢሉባቦር መቱ፣ በምዕራብ ወለጋ ነጆ እና ቢላ፣ በምስራቀረ ጎጃም ነቀምት እንዲሁም በቡራዩ ጨምሮ በተለያዩ ከተሞችና ተቋማት ተቃውሞው ተጠናክሮ መቀጠሉ ታውቋል፡፡ ዛሬ በነጆ በነበረው ተቃውሞም 4 ሰዎች መገደላቸውንም መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ የዛሬዎቹን ግድያዎች ጨምሮ ሶስተኛ ሳምንት ባስቆጠረው ህዝባዊ ተቃውሞ በመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በተወሰደ የኃይል እርምጃ የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ከ82 በላይ መድረሱን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡በክልሉ ባሉ ከተሞች ባሉ የተለያዩ ትምህርት ተቋማት ትምህርት መቋረጡ ታውቋል፡፡
ህዝባዊው ተቃውሞው ከክልሉ ተወላጆች በተጨማሪ በሀገር ውስጥ ከሀገር ውጭ ባሉ በርካታ ሰዎች የአጋርነትና ድጋፍ እንደተቸረው እየተገለፀ ሲሆን፤ በዚህም ምክንያት በተለይ በክልሉ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ የአካባቢው የኢህአዴግ አመራሮችና ከየት እንደመጡ ባልታወቁ የስርዓቱ አካላት ባካባቢው ያሉ አማራና ኦሮሞን ለማጋጨት ተደጋጋሚ ሙከራ ማድጋቸውን እና በዚህም 4 የአካባቢው የአማራ ተወላጆች ሲገደሉ፣ ቤቶቻቸው የተቃጠሉና ንብረቶቻቸው ባልታወቁ ሰዎች እንዲዘረፍ በማድረግ በርካቶች መፈናቀላቸውን ከአካባቢው የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡ ተቃውሞውን ክህዝቡ ጥያቄ በተቃራኒ ወደ እርስ በርስ ብሔር ግጭት ለማድረግ የተሞከረውንም ድርጊት የአካባቢው የኦሮሞ ማኀበረሰብ አዛውንቶችና ወጣቶች እንዲቆም ማድረጋቸውን እና በድርጊቱም የተበሳጩ የአካባቢው ነዋሪዎች መካከል የርስ በርስ የብሔር ግጭት ለመፍጠር ሲሰሩ ከነበሩ የገዥው ስርዓት የአካባቢው የኦህዴድ/ኢህአዴግ አመራር አካላት መካከል አንዱ ወዲያው መገደሉንና ሌሎቹ ሸስተው ከአካባቢው ማምለጣቸውን የአዲስ ሚዲያ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡ የተፈናቀለው ህዝብም ወደነበረበት አካባቢ እንዲመለስ የአካባው አዛውንቶችና ወጣቶች እየሰሩ እንደነበርም መረጃዎች አመልክተዋል፡፡

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት በሚኒስተሩ አቶ ጌታቸው ረዳ አማካኝነት በሰጠው መግለጫ በኦሮሚያ ከተሞች በተቀሰቀሰው ህዝባዊ ተቃውሞ የመንግሥት አካላት ላይ ጉዳት መድረሱን በመግለፅ መንግሥት የኃይል እርምጃውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ ይሁን እንጂ ሚኒስትሩ በታቀውሞው በመንግሥት አካላት ላይ ደረሰ ስላሉት ጉዳይ በዝርዝር የገለፀቱት ነገር ባይኖርም፤ በተቃውሞ ሰልፉ ስለተገደሉ ሰዎች ግን ያሉት ነገር የለም፡፡ በትናትነው ዕለት የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት፣ የፌደራሉ የፀረ ሽብር ግብረ ኃይል የመንግሥት የኃይል እርምጃ እንደሚቀጥል ማስጠንቀቂያ መስጠታቸው የሚታወስ ቢሆንም፤ የህዝቡ ተቃውሞ ግን ዛሬም በተለያዩ ከተሞች ተጠናክሮ መቀጠሉ ታውቋል፡፡
በተለይ መንግሥት በሰላማዊ መንገድ ተቃውሞ እያደረጉ ባሉ ሰዎች ላይ መንግሥት እየወሰደ ያለውን የኃይል እርምጃ ከሀገር ውስጥ መድረክ እና ሰማያዊ ፓርቲ በመቃወምና በማውገዝ መግለጫ ማውጣታቸው አይዘነጋም፡፡ በተመሳሳይም ቢሮአቸውን በውጭ ያደረጉ እንደ ኦነግ እና አርበኞች ግንቦት ሰባትን ጨምሮ የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች የመንግሥትን ድርጊት አውግዘዋል፡፡
ጠቅላይ ፍርድ ቤት በአቶ አንዳርጋቸው ላይ የቀረበውን የአቃቤ ህግ ይግባኝን ውድቅ አደረገ
ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ምስክር ሆነው እንዳይቀርቡ ያቀረበውን ይግባኝ ዛሬ ህዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም በዋለው ችሎት ውድቅ አደርጎታል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ድረስ ለተጠቀሱት ተከሳሾች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ ተጠይቆ የነበር ቢሆንም ማረሚያ ቤቱ በተደጋጋሚ ሳያቀርባቸው ቀርቷል፡፡

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ምስክርነት በተጠሩበት ወቅት የፌደራል አቃቤ ህግ “አቶ አንዳርጋቸው በእነ ጀኔራል ተፈራ ማሞ መዝገብ እና በእነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ መዝገብ ላይ ክስ ቀርቦባቸው በእድሜ ልክና በሞት እንዲቀጡ ተወስኖባቸው የህዝባዊ መብታቸው የተሻረ በመሆኑ በምስክርነት ሊቀርቡ እንደማይችሉ መቃወሚያ አቅርቦ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ይሁንና ፍርድ ቤቱ ተከሳሾቹ አቶ አንዳርጋቸው እንዲቀርቡላቸው የጠየቁት ለዋስት አሊያም ልዩ አዋቂ ምስክር ሆነው ሳይሆን ነበሩበት የተባለውን ጉዳይ ለመናገር በመሆኑ ለምስክርነት ሊቀርቡ ይገባል” በሚል የፌደራል አቃቤ ህግ ያቀረበውን ተቃውሞ ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል፡፡
የልደታ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሀምሌ 13 ቀን 2007 ዓ.ም ቀርበው ምስክርነት እንዲሰጡ ከወሰነ በኋላ የቃሊቲ ማረሚያ ቤት “ትዕዛዝ አልደረሰኝም፣ የተፃፈው ለቃሊቲ ሳይሆን ለአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት የሚል ነው” እና ሌሎችም ምክንያቶች በማቅረብ በተደጋጋሚ አቶ አንዳርጋቸውን ሳያቀርብ ቀርቷል፡፡ በስተመጨረሻም ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም ማረሚያ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው ቃሊቲ እንደሌሉ በደብዳቤ አሳውቋል፡፡ በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ ከ2ኛ እስከ 5ኛ ከተከሰሱት መካከል አቶ ደናሁን ቤዛ (3ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን (4ኛ ተከሳሽ) ውጭ ያሉት የፍትህ ሂደቱ እየተጓተተባባቸው በመሆኑ የአንዳርጋቸው ፅጌ ምስክርነት ቀርቶ በሌሎች መረጃዎች ውሳኔ እንዲሰጥላቸው ሲጠይቁ ሁለቱ ተከሳሾች ግን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሊመሰክሩላቸው እንደሚገባ ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ አቅርበው ነበር፡፡
በዚህም መሰረት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለፀረ ሽብር ግብረ ኃይልና አቶ አንዳርጋቸውን ጠይቀውታል ለተባሉት የብሪታኒያ አምባሳደር ደብዳቤ መፃፋቸው ይታወቃል፡፡ ይሁንና ተከሳሾቹ ለሶስቱ አካላት ደብዳቤውን በፃፉበት ማግስት የፌደራል አቃቤ ህግ ከወራት በፊት ለልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ መመስከር አይገባቸውም ብሎ አቅርቦት የነበረውን መከራከሪያ መሰረት በማድረግ አቶ አንዳርጋቸው ምስክር እንዳይሆኑ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ጠይቆ ነበር፡፡
የአቃቤ ህግን ይግባኝ ያየው ጠቅላይ ፍርድ ቤትም ዛሬ ህዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም በዋለው ችሎት “አንድ ሰው ለምስክርነት ይቅረብ አይቅረብ በሚል ይግባኝ ሊጠየቅበት አይገባም፡፡ ካስፈለገ ግለሰቡ የሰጡት ምስክረነት መረጃው ተመዝኖ የሚሰጠው ፍርድ ላይ ይግባኝ ሊባል ይችላል፡፡ እኛም ጉዳዩን ለማጣራት ምስክርነቱ እንዲቋረጥ አድርገን የነበር ቢሆንም አሁን ግን እንዲቀጥል ወስነናል፡፡ የአቃቤ ህግን ይግባኝም አልተቀበልነውም” ሲል ይግባኙን ውድቅ አድርጓል፡፡ አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ምስክር መሆን የለባቸውም ብሎ ያቀረበው ክርክር በፍርድ ቤት ውድቅ ሲሆንበት ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ነው፡፡
በእነ ዘመነ ካሴ መዝገብ ከተከሰሱት በተጨማሪ በእነ ዘላለም ወርቅአገኘሁ የክስ መዝገብ ከተከሰሱት መካከል 1ኛ ተከሳሽ አቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በመከላከያ ምስክርነት ጠርቷቸዋል፡፡ በሌሎች የክስ መዝገቦች ከአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጋር ተገናኝታችኋል የተባሉ ተከሳሾችም አቶ አንዳርጋቸውን የመከላከያ ምስክር አድርገው ሊጠሯቸው እንደሚችሉ ምንጮቹን ዋቢ በማድረግ ነገረ ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡
በኦሮሚያ ክልል ባሉ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ላይ መንግሥት በወሰደው የኃይል እርምጃ ከ5 በላይ ሰዎች ሲገደሉ፤ በርካቶች ቆስለዋል
ህዳር 20 ቀን 2008 ዓ.ም. በምዕራብ ሸዋ ጊኒጪ ከተማ እንደገና የተጀመረው አዲሱን የአዲስ አበባ እና የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞችን የተቀናጀ ማስተር ፕላን ትግበራን የተቃወሙ ተማሪዎች ላይ መንግሥት በወሰደው የኃይል እርምጃ እስካሁን የ5 ሰዎች ህይወት መጥፋቱ እና በርካታ ተማሪዎችም መጎዳታቸው ታውቋል፡፡ በተለይ እንደ አዲስሚዲያ ምጮች ከሆነ፤ የተማሪዎች ተቃውሞ በምዕራብ ኢትዮጵያ በጊኒጪ፣ በአምቦ፣ በምዕራብ ወለጋ የተቀጣጠለው ተቃውሞ ሌሎችንም የምዕራብ ሸዋ ከተሞችን አዳርሶ ወደ ምስራቅ ኢትዮጵያ ሐረማያ ዩኒቨርስቲ መድረሱ ታውቋል፡፡

በተለይ በሐረማያ ዩኒቨርስቲ ህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ጥያቄ ባነሱ ተማሪዎች ላይ መንግሥት በወሰደው የኃይል እርምጃ 1 ተማሪ ሲገደል፣ ቁጥራቸው እስካሁን በውል ያልታወቁ በርካቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው ታውቋል፡፡ በተለይ ህዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም. ሐረማያ ዩኒቨርስቲ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸው በዩኒቨርስቲው ክልኒክ እና በሐረር ሆስፒታል የህክምና እርዳታ ሲደረግላቸው ከነበሩት መካከል በዩኒቨርስቲው ክልኒክ የህክምና እርዳታ ሲደረግለት የነበረ አንድ ተማሪ ህይወቱ ማለፉን ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በተማሪዎች ላይ እየወሰዱ ባሉት የኃይል እርምጃ በምዕራብ ወለጋ ግሊሶ ከተማ ሌላ አንድ ተማሪ መገደሉ የተጠቆመ ሲሆን፤ እስካሁን በፀጥታ ኃይሉ የተገደሉ ተማሪዎች ቁጥርም 5 መድረሱ ታውቋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ በሱሉልታ ጫንጮ የአንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ባነሱት ተመሳሳይ ጥያቄ በርካታ ተማሪዎች በመንግሥት በተወሰደባቸው የኃይል እርምጃ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡ ተቃውሞው በኦሮሚያ ክልል ካሉ አንደኛ ደረጃ እስከ ዩኒቨርስቲ የተቀጣጠለ ሲሆን፤ በተለይ በጫንጮ አንደኛ እና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መንግሥት በወሰደው የኃይል እርምጃ የአንደኛ ደረጃ ህፃን ተማሪዎች ላይ ሳይቀር ጉዳት መድረሱን ምስልን አስደግፈው የአካባቢው ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡

መንግሥት በተማሪዎች ላይ እየወሰደ ባለው የኃይል እርምጃ ከክልሉ ተወላጆች በተጨማሪ በርካታ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ላይ ቁጣን የቀሰቀሰ ሲሆን፤ ተቃውሞው ወደክልሉ ሌሎች ከተሞች እና ዩኒቨርስቲዎችም እየተዛመተ በመሆኑ በየአካባቢው ከተሞች ባሉ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እና ዩኒቨርስቲዎች ከፍተኛ የፀጥታ ጥበቃ ቁጥጥር ላይ መሆናቸው ተሰምቷል፡፡ ተቃውሞው ወደባሌ መዳወላቡ ዪኒቨርስቲም መዛመቱ መዛመቱን ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡
በደቡብ ምዕራብ ሸዋ በበቾ እና በቱሉቦሎ ከተማ እንደዚሁም በደቡብ ሸዋ ወሊሶ አካባቢ በዲላላ ከተማ ውስጥ ያሉ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ተቃውሞ እያደረጉ እንደሆነም የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ዘገባ አመልክቷል፡፡ የተቃውሞው ዋነኛ ምክንያትም መንግሥት ይፋ ያደረውና እስካሁንም ከህዝብ ጋር ያልተመከረበትና ተግባራዊ ለማድረግ ከመንቀሳቀስ በስተቀር በምስጢር ተይዟል የተባለለት አዲሱ የአዲስ አበባ እና የአካባቢው የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች የጋራ የተቀናጀ ማስተር ፕላን በአካባቢው ያሉ ገበሬዎችን ያለ በቂ ካሳ ያፈናቅላል፣ የአካባቢው ኦሮሞ ማኀበረሰብ ባህልና ቋንቋ ያጠፋል እና ኦሮሚያ ክልልን ለሁለት ይከፍላል የሚሉ ጥያቄዎች እንደሚገኙበት ለአዲስ ሚዲያ የደረሱ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡
በተያያዘ ዜና፤ አዲሱ የአዲስ አበባ እና የኦሮሚያ ልዩ ዞን ከተሞች የተቀናጀ የጋራ ማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ ባለፈው ግንቦት 2006 ዓ.ም. ተቀስቅሶ በነበረው ተመሳሳይ የተማሪዎች ተቃውሞ ከ40 በላይ ወጣቶች ሲገደሉ፤ በርካቶች መጎዳታቸው አይዘነጋም፡፡ ይህንንም ተከትሎ ተቃውሞውን አነሳስታችኋል ተብለው የታሰሩ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አሉ፡፡ በተለይ ዛሬ ህዳር 23 ቀን 2008 ዓ.ም. በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ልደታ ምድብ ችሎት ከግንቦት 2006 ዓ.ም. ጀምሮ በእስር ላይ ከነበሩት 6 ተማሪዎች መካከል 5ቱን ጥፋኛ ሲል መበየኑን እና እንዲከላከሉ ለማክሰኞ ጥር 10 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ መስጠቱን ታውቋል፡፡ ጥፋተኛ ተብለው እንዲከላከሉ ከተበየነባቸው ተማሪዎች መካከል አበበ ኡርጌሳ፣ መገርሳ ወርቁ፣ አዱኛ ኬሶ፣ቢሊሱማ ዳመነ እና ተሾመ በቀለ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ከተማሪ ተሾመ በቀለ በስተቀር የቀሪዎቹ አራቱን ተከሳሾች የዋስትና መብት ጥያቄ ውድቅ መደረጉንም የአዲስ ስታንዳርድ ዘገባ አመልክቷል፡፡