Monthly Archives: August, 2013

የህዝብን ጥያቄ ማጣጣል የሚያመጣው መዘዝ

ቴዎድሮስ ባልቻ

በዓለም ላይ ህዝባዊ መሰረት የሌላቸው መሪዎች ሁልጊዜ ዜጎቻቸውን እንደሚጨቁኑ ይታወቃል፡፡ እነኚህ ወደስልጣን ሲመጡ የነፃ አስተዳደር ስርዓትን ለማስፈን በውስጣቸው ያለው አምባገነንነታቸው ስለሚጫናቸውና በህዝብ ላይ የፈፀሙት በደል ሲኖር ሁልጊዜ የሚመሩትን ህዝብ ያፍናሉ፡፡ ይህ እየበረታ ሲሄድ ደግሞ የፈራው  ህዝብ ድንገት ተነስቶ የተቃውሞ ድምፅ ሲያሰማ አሸማቃቂ ስያሜ ይሰጠዋል፡፡ ያኔ ህዝቡም ለጥያቄው ምላሽ እንደማያገኝ ሲገባው ወደ ህዝባዊ አመፅ መግባቱ ግድ ነው፡፡ ምክንያቱም የሰው ልጅ በተፈጥሮው ነፃነትን ይሻልና፡፡

ጨቋኞች ደግሞ በባህሪያቸው ሁልጊዜ ፈሪዎች ናቸው፤ ለዛም ነው ለህዝብ ድምፅ ጆሮአቸውን የማይሰጡት፡፡ ለዚህም እንደ ቱኒዚያ፣ ግብፅ፣ ሊቢያ፣ የመን እና ሶሪያን ማንሳት ይቻላል፡፡ ይሄ ደግሞ አሁን ባለንበት ሁኔታ በኢትዮጵያም መከሰቱ የማይቀር ይመስላል፡፡ ምክንያቱም የህዝብ ድምፅ ሊዘገይ ቢችልም ዋጋ አለው፡፡

በተለይ ባለፈው ሰኔ ወር በፈጣን የምጣኔ ሃብት ዕድገት ዓለምን እያስደመመች ያለችውን ለህዝቡም የዴሞክራሲ ስርዓትን በመዘርጋት እየታወቀች ያለችው ብራዚል መሪዎች ለህዝብ ድምፅ እንዴት ዋጋ እንደሚሰጡ ትልቅ ምሳሌ ናት፡፡ የሀገሪቱ የቀድሞ ፕሬዘዳንት የሀገራቸውንና የህዝባቸውን ጥቅም ለማንም አሳልፈው ያልሰጡት ሉላ ዳ ሲልቫ ብራዚልን በዓለም የምጣኔ ሀብት ከእንግሊዝ አስቀድመው ስድስተኛ ደረጃ ቢያደርሷትም አዲሷ መሪ ከህዝባዊ አመፅ ሊታደጓት አልቻሉም፡፡

አሁን በስልጣን ላይ ያለው የብራዚል መንግስት አስተዳደር በነዳጅ ዋጋ ላይ ድንገት የ 20 ሳንቲም የዋጋ ጭማሪ ሲያደርግ ሳይታሰብ የህዝቡ ለ ተቃውሞ ፈንቅሎ ይወጣል፡፡ ይሄኔ ፕሬዘዳንቷ በሀገሪቱ ቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ብለው የህዝቡን ድምፅ መስማታቸው በማረጋገጥ የተደረገው ጭማሪ እንደተነሳ አስታወቁ፡፡ ህዝቡ ግን ድሮም በኑሮ ውድነቱ ሆድ ብሶታልና ያለውን ችግር በመጠቆም ሰልፉን በመላ ሀገሪቱ ከተሞች በስፋት አቀጣጠሉት፡፡ ይሁን እንጂ ፕሬዘዳንቷ ለተቃውሞ የወጡትን ሰዎች አመስግነው ህዝቡ ያነሳቸው ችግሮች በአፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጡ አስታወቁ፡፡ የፀጥታ ኃይሎችም ቢሆኑ ድንገት ፈንቅሎ የወጣውን ህዝብ ከመጠበቅ በስተቀር ዜጎቻቸው ላይ ጉዳት ለማድረስ አልሞከሩም፡፡

በኢትዮጵያም ሰኔ 1966 ዓ.ም. በነዳጅ ዋጋ ላይ በተደረገው የ5 ሳንቲም የዋጋ ጭማሪ ሰበብ ህዝቡ ለተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ቢወጣም ንጉሱ አጼ ኃ/ስላሴም የህዝቡን ድምፅ መስማታቸውን በማረጋገጥ የተደረገውን የዋጋ ጭማሪ አንሰተናል አሉ፡፡ ይሁን እንጂ በተለይ የአዲስ አበባ ህዝብ ከነዳጅ ጭማሪው በስተጀርባ የነበረው ጭቆና ስላለ የተቃውሞ ሰልፉን እንደማያቆሙ በማስታወቅ በወቅቱ እንደ መምህራን ማኀበር ያሉ ነፃ የሙያ ማኀበራትና መከላከያ ሰራዊት ከንጉሱ ይልቅ ከህዝቡ ጎን መቆማቸውን አረጋገጡ፡፡በወቅቱ ግን ንጉሱ ለተቃውሞ የወጣውን ህዝብ ጣያቄም ሆነ ድምፅ አላጣጣሉም ነበር፡፡ የዚህ እርሾ ንጉሱን መስከረም 2 ቀን 1967ዓ.ም. ከስልጣናቸው አወረዳቸው፡፡

በቅርቡ የመሐመድ ቡዓዚዝ እራሱን ማቃጠሉና አረቡ አብዮት መከሰቱን ተከትሎ የቱኒዚያ ህዝብ በቤን ዓሊ ላይ ተቃውሞ ሲያሰማ ፕሬዘዳንቱ ህዝቡን በክፉ ከመፈረጅ ይልቅ ከስልጣን ወርደው በሳውዲ ዓረቢያ ጥገኝነት ሊጠይቁ ችለዋል፡፡ ነገር ግን በግብፅ፣ በሊቢያ፣ በየመንና በሶሪያ መሪዎች ላይ ህዝቡ ተቃውሞ ሲያሰማ መሪዎቹ ከማጣጣላቸው በተጨማሪ ህዝቡን አሸባሪ፣ የአልቃይዳ ተላላኪ፣…እያሉ ይፈርጁ ነበር፡፡ በዚህ ወቅት ተቃውሞ ያቀረበውን ህዝብ አሸባሪ ካሉት መሪዎች መካከል የሶሪያው በሰር አላሳድ በጦራቸው ህዝብን ለመጨረስ ቢሞክሩም እሳቸው እስካሁን ሰላም አላገኙም፡፡ በአንፃሩ በአፍሪካ መሪዎች እጅግ የተፈሩና የተከበሩ የነበሩት የሊቢያው መሪ ሙዓሙር ጋዳፊ ከአማረው ቤተመንግስታቸው አምልጠው ለፍሳሽ ማስወገጃ በተውልድ አካባቢያቸው ቤንጋዚ ላይ ባሰሩት ቱቦ ተደብቀው ለማምለጥ ሲሞክሩ የውርደት ሞትን ተከናንበዋል፡፡

የግብፁ ሆስኒ ሙባረክ ደግሞ 1.2 ሚሊዮን ልዩ ደህንነት እንዳላቸው ቢታወቅም የህዝቢ ቁጣ ፈንቅሎ በመውጣቱና ለህዝብ ጥያቄ አዎንታዊ መልስ ከመስጠት ይልቅ ማስፈራራትና ዛቻ ቢፈፅሙም ከሞቀና ከተከበሩበት ቤተመንግስት በውርደት ተባረው ቆመው መሄድ እንኳ ሳይችሉ በህመምተኛ አልጋ ላይ ሆነው ለፍርድ መቅረባቸው የማይረሳ ነው፡፡ የየመኑም ቢሆኑ ከስልጣኔ አልወርድም ፣ ወይፍንልች እኔ አብደላ ሳላ ያሉት ፕሬዘዳንት የህዝቡን ድምፅ ከመስማትና በጎ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ፍረጃና ማስፈራራቱን ቢያያዙትም አልሆነላቸውም፡፡ በመጨረሻም  ለተቃውሞ የወጣውን ህዝብ በድጋሚ ለማስፈራራትና ደጋፊዎቻቸውን ከጎን በማሰለፍ ህዝቡን ለስልጣናቸው ሲሉ ሊከፋፍሉ ሲሞክሩ በአደባባይ ንግግር ላይ ሳሉ የጥይት እሩመታ አስተናግደው ከሞት ቢተርፉም ሳይወዱ በግድ ስልጣን በቃኝ ብለው ከሀገራቸው ውጭ በስደት ጥገኝነት ለመኖር ተገደዋል፡፡

በዘመነ ኢህአዴግ በኢትዮጵያም የታመቀ ህዝባዊ ብሶት እንዳለ የኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ ጥናት ያረጋገጠ ቢሆንም እውነትነት ስለመኖሩ ለኢትዮጵያውያን ነጋሪ አያሻም፡፡ በተለይ በኢትዮጵያ ያለው ችግር እስከዛሬ በሀገሪቱ ታይቶ የማይታወቀው  የዘረኝነት ከፋፍለህ ግዛ የቅኝ አገዛዝ ስልት ከጥቂት ለስርዐሳቱ ከቀረቡ ቡድኖች በስተቀር ያለው የፖለቲካ፣ምጣኔ ሃብትና ማኀበራዊ ችግር እንዲሁ በቀላሉ የሚቀረፍ አይመስልም፡፡ በዚህም ምክንያት አብዛኛው ህዝብ መስርዓቱ ምንደኛ በሆኑ በመንደር ካድሬዎች የአፈና ቋፍ ውስጥ በመውደቅ በጓዳ ሲያጉረመርም ደፋሮች ደግሞ በአደባባይ ተቃውሟቸውን በአደባባይ ማሰማታቸው አልቀረም፡፡

መንበረ ስልጣኑን በህዝብ ተመርጬ ስልጣን ይዣለሁ የሚለው አካል  በህዝብ ተመርጦ ዛሬም ድረስ ሀገርና ህዝብ ይጎዳሉ የሚሏቸው ተግባራት በገዥው ስርዓት ሲፈፀሙ ልክ እንደ ደቡብ አፍርካ አፓርታይድ ስርዓት አሊያም እንደነ ሆስኒ ሙባረክና ሙዓሙር ጋዳፊ አስተዳደር የሚቃወሟቸውን አሸባሪ ብሎ መፈረጅና ማሰር እንደ ፋሽን እየታየ ሲሆን ይህም በስልጣን ላይ ያለው አካል ህዝባዊ ይሁንታ አለኝ ብሎ ስልጣን የመያዝ ምንነት አልገባውም፣ አሊያም ለማወቅም የሚፈልግ አይመስልም፡፡ ምክንያቱም ህዝባዊ እውቅና ያለው ፤ ያውም በምርጫ ይሁንታ አግኝቻለሁ የሚል አካል በተለይም በዓለም ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ 96.9 % የህዝብ ድምፅ አግኝቻለሁ የሚል እንዴት ህዝባዊ ተቃውሞ እንደሚፈራ ሲታሰብ እጅግ የሚደንቅ ተግባር ነውና፡፡

በእንዲህ ዓይነት ሁኔታም በርካቶች የዚህ ሰለባ የሆኑ ሲሆን አሁን አሁን ግን ሰው ከፍርሃት ወጥቶ ኢህአዴግን ደግፎ ካልሆነ ተቃውሞ ማሰማት ባልተፃፈ ህግ የተከለከለ ቢሆንም ህዝቡ ግን ተቃውሞ ለማሰማት የሚታገስ አይመስልም፡፡ ስለሆነም የራሱ አባላትን ጨምሮ ጥያቄ እንዲያነሱ የሚያደርጉ የፍትህ መጓደል፣ የኑሮ ውድነት፣ ስራ አጥነት፣ የዜጎች በግፍ መፈናቀል፣…ሰውን ሰላም የነሳው ይመስላል፡፡ በዚህም ምክንያት በመላ ሀገሪቱ በሚባል ደረጃ የታፈኑ ድምፆች በስፋት መስተጋባት ጀምረዋል፡፡

በተለይ በቅርቡ በግንቦት 2005 ዓ.ም. ሰማያዊ ፓርቲ በአዲሳ አበባ የተቃውሞ ሰላማዊ ማድረጉ፣ አንድነት ፓርቲ ደግሞ በያዝነው ሐምሌ 2005 ዓ.ም. በጎንደርና በደሴ ያደረገው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፎች ከአፈናው አንፃር ሲታይ መቆሚያ ያለው አይመስልም፡፡ በተለይ በሰልፎቹ ላይ ፓርቲዎቹ ካዘጋጁት መፈክር በተጨማሪ በሀገራችን ሰላም አጣን፣ፍትህ አጣን፣…የሚሉ ድምፆች መበራከት የነገውን ቀን ለመተንበይ አስቸጋሪ አያደርገውም፡፡

በስልጣን ላይ ያለው የኢትዮጵያ መንግስት በበኩሉ እነኙህ ድምፆች እንዳይሰሙ የመንደር ካድሬዎች በየቤቱ እየሄዱ ሰው ሰላማዊ ሰልፍ እንዳይወጣ እንዲያስፈራሩ መደረጉን ከደሴና ከጎንደር ነዋሪዎች በስፋት የተሰማ ሲሆን ህዝቡን ለተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ከመውጣት ያገደው ግን አልነበረም፤ ያውም በደሴ ወደ 50 ሺህ በጎንደር ደግሞ ወደ 40ሺህ ሰው፡፡ አሁን ባለው ሁኔታም መንግስት የህዝቡን ድምፅ ከመስማትና ከማሳዳመጥ ይልቅ ለሰልፉ የወጡትን ሰዎች የሙስሊም አክራሪዎች ናቸው፣ በሰልፉ የወጣው ህዝብ ትንሽ ነው እያለ ለማጣጣል መሞከሩ አሁንም ለህዝብ ያለውን አመለካከትና አምባገነኖች መውደቂያቸው ሲደርስ የሚፈፅሙትን ቅደም ተከተል ተግባር ከማንፀባረቅ ይልቅ የሚፈይደው አንዳች ነገር የለም፡፡ ይህ አካሄድ ለነ ሙባረክና ለነ ጋዳፊም አልሰራምና፡፡

በተለይ አንድነት ፓርቲ አሁን በያዘው አቋም እና እቅድ የሚቀጥል ከሆነ ሀገር አቀፍ ህዝባዊ ንቅናቄ መጀመሩና ሰማያዊ ፓርቲም በነሐሴ ወር ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ መጥራቱ በቅርቡ ከወጣው ህዝብ በብዙ ሺህ እጥፍ ሊወጣ እንደሚችል ይገመታል፡፡ ለዚህ ዋነኛ ምክንያት ደግሞ መንግስት የህዝቡን የተቃውሞ ድምፅና ጥያቄ ከመስማትና እርምት ለመውሰድ ከመሞከር ይልቅ ለማጣጣል መሞከሩ ህዝቡን የበለጠ ለተቃውሞ እንዲነሳሳ ማድረጉ አይቀሬ ነው፡፡ ምናልባት መንግስት ከዚህ በኋላ እንደባለፉት 8 ዓመታት ለተቃውሞ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ለመውጣት እውቅና አልሰጥም ቢል እንኳ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ያላቸው ፓርቲዎች የመሪነት ሚናቸውን መወጣት ከቻሉ ህዝቡን ከመውጣት የሚያግደው አይኖርም፡፡ ምክንያቱም የታፈኑ ድምፆች እያየሉ ሲሄዱ በድንገት አንድ ቀን መፈንዳታቸው አይቀርምና፡፡

አንድነት ፓርቲ ሐምሌ 7 ቀን 2005ዓ.ም. እንዳካሄደው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ከሆነ መንግስት የፀጥታ ኃይሎች በህዝቡ ላይ እርምጃ እንዲወስዱ ቢያዝ እንኳ የፀጥታ ኃይሉ እሱም የማኀበረሰቡ አካል በመሆኑ በመጨረሻ ህዝባዊ ወገንተኝነት ማሳየቱ የማይቀር ነው፡፡ ስለዚህ የህዝብን የተቃውሞ ሰልፍ እና አቤቱታ ማጣጣል ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እጅግ ማመዘኑ የማይቀር ስለመሆኑ በያዝነው ዓመት የምናየው እውነታ ሊሆን እንደሚችል ይጠበቃል፡፡

ከ1997ዓ.ም. ምርጫን ተከትሎ ኢህአዴግ ከወሰዳቸው የጭካኔ እርምጃ በኋላ ሰው በመኝታውና በጓደው ካልሆነ በቀር የተቃውሞ ድምፅ ማሰማት ይፈራ የነበረ ሁላ አሁን አሁን ግን በተለያየ የትራንስፖርት መስክ (በየታክሲ፣ አውቶቡስ ውስጥ፣…)፣ በየንግድ ተቋማትና በየቢሮ የቅሬታ ድምፆች በድፍረት መደመጥ ጀምረዋል፡፡ ይሄ ደግሞ የታፈኑ ድምፆች ቀስበቀስ መውጣታቸው ይበል የሚያሰኝ ሲሆን በዚህም የመንግስት ግትር አቋም የሚቀጥል ከሆነ ባልታሰበ ሰዓት አንድ የለውጥ ክስተት መፈጠሩ የማይቀር ነው፡፡ ምክንያቱም የሰው ልጅ በባህሪው እንደተጨቆነ እና እንደታፈነ ዘለዓለም የሚኖርበት የህይወት ሂደት የለውምና፡፡

Sinai Desert: A Brutal Prison and Grave for Thousands of Ethiopian, Somali, and Eritrean Refugees

By Betre Yacob

 

“We were 16 people. Once we first arrived inside the house, we were asked for money. One guy said straight away that he won’t be able to pay. They [the captors] wanted to make him an example; so they undressed him in front of us and started beating and poking him with big wooden sticks. They then inserted a stick into his… He was bleeding all over. After more beatings, they poured petrol on him and set him on fire. After he died, they left his body in the room with us until it became rotten and worms started crawling. They forced all of us in turns to hold him.”

This story may seem to be taken from a Hollywood horror movie as it is so horrific. But, unfortunately, it is a true story. It is what an Eritrean survivor, held captive in Sinai for eight months after being kidnapped from Eastern Sudan, said recently while describing his ordeal to Amnesty International.

Kidnapped mostly from Eastern Sudan, many Ethiopian, Somali, and Eritrean refugees are held captive in Sinai Desert by Bedouin criminal gangs [people-traffickers] with the objective to obtain tens of thousands of dollars in ransom money in exchange for their release. During their captivity, they are subjected to several acts of extreme violence and brutality, including rape of men and women and other forms of sexual violence. Some of those who are unable to pay a ransom are simply killed like what we have seen here above in the story; some others are murdered to demonstrate to the families of other captives the seriousness of the threats. Many die as a result of routine torture.

Lamlam, 17, is another survivor. She experienced extremely brutal abuses. She says that everything was a nightmare more than one can imagine. “The kidnappers would make me lie on my back and then they would get me to ring my family to ask them to pay the ransom they wanted,” she says. “As soon as one of my parents answered the phone, the men would melt flaming plastic over my back and inner thighs and I would scream and scream in pain. This, they hoped, would put extra pressure on my mother and father to find the money.”

The New York Times estimates that 7,000 Ethiopian, Somali, and Eritrean refugees have been abused this way over the last four years, and that 4,000 of them have died. The victims include men, women, children, and even accompanying infants. The majorities of them are also estimated to be aged between 15—25. However, some NGOs and international organizations place the number of the victims far higher. According to different human rights organizations, this new form of brutal ‘business’ has been escalating, as the impunity guaranteed to the criminals continues. Reports indicate that there have been no prosecutions of criminals responsible for the abuses so far.

Different testimonies and reports shows that the methods of tortures that are often used to increase the urgency of captives’ pleas to relatives to pay the money to secure their release are extremely brutal and often lead to a wish to die. These include electrocution; pouring gasoline over the body and setting it on fire; burning with cigarette butts or heated rubber and metal objects; water-drowning; amputation of limbs; beatings with objects such as metal chains, sticks and whips; suspension from the ceiling and suspension in contorted positions for prolonged periods of time; hanging by hair; and forcing to stand for extended periods of time in desert heat. According to testimonies, captives often face a combination of these all methods.

In its latest report Amnesty International said that victims have also reported having fingernails pulled out. The group further said: “Many have also reportedly been deprived of food, water, medical treatment and showers for prolonged periods. Many former captives also reported being chained throughout the duration of their captivity, often to other captives.” A research conducted by Tilburg University and Europe External Policy Advisors shows that women are tortured while pregnant – and their pregnancies are often the result of the rapes they suffer. If they find themselves pregnant, women hostages are told that the ransom will double once their baby is born. Many hostages succumb to the torture. This torture can be functional as it takes place to extort the ransom from relatives, but it can also be gratuitous.

Different reports indicate that ransoms are often paid despite the amounts demanded by the criminals are very excessive—often from USD 30,000 —50,000. Relatives sell their possessions such as houses and lands, to get the money demanded and free the hostages suffering from extreme acts of brutality; many borrow while some go from church to church begging people to contribute. Some hostages are, however, killed even after their ransom has been paid after many up and down.

Kidnapping in Eastern Sudan,

Many Ethiopian, Somali, and Eritrean, who left their repressive and impoverished countries in search of a better security and life, get kidnapped and become hostage every single day. The significant majority of the victims are, however, Eritrean. Different researches indicate Eritrean refugees are often kidnapped on their way to refuge camps in East Sudan, where asylum-seekers undergo a refugee status determination procedure and are issued with documentation. There are, however, significant reports of kidnapping from inside refuge camps, particularly from Shagarab. There are also some incidents from Mai Aini camp in Ethiopia.

The kidnappings are mainly carried out by Sudanese criminal networks made up of local tribesmen with the support of different individuals— often Eritreans. There are also allegations of the involvement of members of the Sudanese security forces and corrupted Eritrean military officials working around Eritrea-Sudan border. According to testimonies, once the Eritreans refugees are kidnapped, they are soon sold to the major criminal gangs known as Rashaida in East Sudan. They are then forcibly transported to Sinai in harrowing journeys that last for several weeks, and sold to Bedouin criminal networks that held them hostage and torture them to extract ransom payments from their families. Reports indicate that during the journey to Sinai refugees are subjected to violence, including beatings and rape, and cruel treatment, including deprivation of food and water.

Eritrea

2013 UNHCR regional operations profile – East and Horn of Africa

Working environment

As in previous years, in 2012 the East and Horn of Africa region continued to draw the attention of the world for the scope and magnitude of the humanitarian challenges facing it. There are more than 7.3 million people of concern to UNHCR in the East and Horn, with assessed needs for 2013 amounting to more than USD 1 billion. The biggest operation in the region remained the response to the Somali emergency, followed closely by the Sudanese refugee situation.

Throughout 2012 the East and the Horn saw armed conflict in Somalia, Sudan, South Sudan and the Democratic Republic of the Congo (DRC). The incursion into Somalia by Kenyan forces to bolster the activities of the already present African Union forces (AMISOM) was a significant event during the year.

The security situation in Dadaab, Kenya which hosts more than half a million Somali refugees, took a serious turn for the worse at the beginning of the year. Humanitarian workers were taken hostage and reportedly taken across the border to Somalia. Roadside bombs and improvised explosive devices frequently targeted the Kenyan personnel responsible for camp security, resulting in a number of deaths and injuries among both police officers and refugees.

The creation of South Sudan last year has not ended the conflict between the two Sudans, with clashes largely driven by issues left unresolved in the Comprehensive Peace Agreement between the two countries. Among the contentious issues were the sharing of resources and the presence of proxy militias on both sides of the border. The conflict drove refugees into Ethiopia and South Sudan. Particularly in South Sudan, refugees moved into areas which lacked basic infrastructure or host communities and were largely inaccessible during the rainy season, raising huge challenges in providing protection and humanitarian assistance. Many refugees had experienced crop failure in Sudan before seeking refuge. Isolated, refugees had to depend mostly on themselves as well as the assistance they received from the humanitarian community. The confluence of all these factors has resulted in many refugee children and other vulnerable groups being malnourished, and many have died.

Humanitarian access in Sudan, particularly in the contested regions of South Kordofan and Blue Nile, has become increasingly limited. A tripartite agreement to allow humanitarian assistance into these regions was signed in August, but it remains to be seen how this will alleviate the situation. In Darfur, clashes between rebels and the Sudanese Government continue to cause more displacement. Clashes between government forces and a new rebel group known as M23 in the eastern DRC have forced more than 41,000 refugees to seek protection in Uganda. Many of them have been moved away from the transit centre at Nyakabande to settlements, including the Rwamwanja site, which is being rehabilitated. Some have chosen to monitor the situation back home from the transit centre, while a small number have returned home.

Strategy in 2013

UNHCR is maintaining and strengthening its emergency response capability throughout the region to ensure that arriving refugees receive robust protection and assistance. The strategy requires enhanced coordination with other core humanitarian actors such as WFP, UNICEF, donors and NGOs, a well maintained regional stockpile, and careful management of standing arrangements with partners for the rapid deployment of assistance and personnel.

Among UNHCR’s top priorities is ensuring adequate assistance in life-saving sectors such as water, shelter, health, sanitation and core relief items. Unfortunately, needs in many other important areas, such as livelihoods, support for host communities, alternative energy and education, have been impossible to fill or insufficiently addressed due to funding constraints.

In 2013, logistics and supply management will be of critical importance to the programmes in South Sudan and Ethiopia due to the remoteness of the areas hosting refugees, the absence of basic infrastructure and ongoing insecurity. UNHCR has already had to invest heavily in infrastructure, such as road construction and maintenance, in South Sudan.

While the number of new arrivals from Sudan has dropped because of the rains, it is expected that more will come after the rainy season ends at the close of the year. Air and ground attacks in Sudan’s Southern Kordofan State in September drove a new influx of about 100 refugees a day into South Sudan, where UNHCR and its partners will ensure enough food is available.

A smaller number of arrivals is expected in western Ethiopia, where UNHCR will continue to transfer refugees away from transit sites and improve facilities and services in new settlements.

Some 170,000 Somali refugees have sought protection and assistance in the Dollo Ado region of Ethiopia, overwhelming the local population of 130,000 people. The refugees are currently hosted in five camps, with a sixth to be opened to accommodate those currently in transit centres and decongest some of the existing camps. It is likely that more Somalis will arrive, especially as military action inside Somalia continues. The aim is to have robust livelihood interventions to reduce refugees’ dependence on humanitarian aid. Innovative projects in sectors such as livelihoods, agriculture and alternative energy will also be implemented.

Uganda continues to receive Congolese refugees as a result of the ongoing conflict in the eastern DRC. While regional initiatives to end the conflict have not borne fruit, the number of arrivals has gone down and a few refugees from the transit sites have returned home. For those remaining, UNHCR will continue to improve key life-sustaining sectors such as shelter, health, water and sanitation.

Floods in 2012 have greatly affected most of the camps hosting refugees from the Central African Republic (CAR) in Chad. UNHCR will repair and reinforce structures affected by the rains. A new, small influx of CAR refugees in July and August was assisted within the existing operation. UNHCR will continue to monitor conditions in the CAR and prepare for a possible larger influx.

Constraints

As in previous years, many of the political, economic and social issues fuelling conflicts in the East and Horn region remained unresolved, resulting in continued displacement. The Sudan situation, which is still unfolding, has drawn heavily on UNHCR’s emergency preparedness and response capacity.

Security for refugees as well as logistical problems in South Sudan and Ethiopia continue to be of great concern. Secure access to populations of concern is another factor that has affected the humanitarian community. In Kenya, a new dimension in providing humanitarian safety and security emerged in early 2012 with the kidnapping of humanitarian workers in Dadaab, some of whom are still in captivity, and the use of improvised explosive devices. These dangers curtailed protection and assistance activities. UNHCR is now working with the Kenyan authorities under the aegis of the Security Partnership Project to restore the humanitarian character of the camps.

In Sudan, the lack of access to contested areas in Darfur has impaired UNHCR’s capacity to provide protection and assistance. Likewise, in South Kordofan, it has been difficult if not impossible to ascertain the situation of an estimated 300,000 IDPs in the region.

In Unity State in South Sudan, where some 64,000 people have sought refuge, there are challenges in maintaining the humanitarian character of Yida camp. Efforts to convince refugees to move away from the border will continue in 2013.

The lack of access in Somalia, where fighting continued to cause untold suffering, is expected to remain a serious constraint in 2013.

In Uganda and Ethiopia, the shortage of funding for assistance to refugee-hosting communities and the rise in the number of new arrivals have undermined local community support and threatened the protection environment. As in previous years, refugees in urban centres in Uganda and Kenya may not receive meaningful assistance due to funding constraints.

Operations

The operations in Chad, Djibouti, Ethiopia, Kenya, South Sudan, Somalia, Sudan and Uganda are described in separate chapters.

People of concern to UNHCR in Eritrea are mainly Somali, Sudanese and Ethiopian asylum-seekers and refugees. The Government of Eritrea recognizes Somali and Sudanese refugees on a prima facie basis. Somali and Sudanese refugees are camp-based and reside in Emkulu and Elit camps. Ethiopian refugees, recognized under UNHCR’s mandate, reside mainly in the Eritrean capital, Asmara.

Ongoing international and regional efforts to bring stability to Somalia improved substantially with the inauguration of a president and prime minister in in 2012, as well as the fall of the port town of Kismayo, the last Al Shabaab stronghold. There is a growing sense that the situation in Somalia could gradually evolve into something more peaceful. Against this backdrop, there have been calls to re-examine the basic planning parameters for the Somali refugee operations, with a view to conditions improving in future and thereby allowing for safe and dignified voluntary returns. UNHCR stands ready to facilitate such a process.

The Regional Support Hub

As in previous years, the Regional Support Hub (RSH) will provide operational support and technical advice to countries in the East and Horn of Africa as well as to operations in the Central Africa and the Great Lakes region. A total of 23 specialists and many deployees from NGO partners provide support through the RSH supplementing sectoral gaps and capacity constraints in operations in the region. The RSH was instrumental in early 2012 in helping to devise an Operations Continuity Plan, following security incidences in Dadaab, Kenya. The framework helped to keep the humanitarian work functioning in the face of serious security threats.

The Regional Liaison Office to the African Union and the UN Economic Commission for Africa

This Regional Liaison Office is attached to the African Union and plays a significant role in ensuring that continent-wide issues that affect populations of concern to UNHCR are taken into account in the deliberations and resolutions of the African Union. Progress has been made with regard to ensuring that African governments ratify the AU Convention for the Protection and Assistance of Internally Displaced Persons in Africa and that its various provisions are transposed into national law. These efforts will continue in 2013.

Financial information

UNHCR operations in the subregion have seen a significant increase in their financial requirements over the last five years, mainly due to a rise in the number of emergency refugee situations, including the Somali influx and the surge in the number of Sudanese crossing into Ethiopia and South Sudan. UNHCR’s budgetary requirements to protect and assist people of concern in the East and Horn of Africa region in 2013 will amounted to about USD 1.13 billion.

 

ነፍስህን በገነት ያኑራት

ብስራት ወ/ሚካኤል

eyob

ብዙ ተስፋ ጥለን በህይወት ልናይህ
የጀመርከው አልቆ በለዛ አንደበትህ
ልናደምጠው ነበር አዲሱን ስራህን
ተስፋ ሆኖ ባይቀር ምኞት ቢሰምርልን
ይሁና…ምን ይደረጋል ከቁጭት በቀር
የሚወዱትን ማጣት እየጓጉ ማረር
በቃ እውን ሆነ ማለት ነው?
ዳግም ከድምፁ ውጭ በመድረክ ላናየው
ኦ…አንተ ሞት ለካ እንዲህ ጨካኝ ነህ
ተወዳጁ ኢዮቤን እንዲህ ትለያለህ
አሁን ምን ይባላል…አጣንህ በህይወት
በቃ ኢዮቤዬ… ነፍስህን ፈጣሪ በገነት ያኑራት
(ለድምፃዊ ኢዮብ መኮንን ነሐሴ 13 ቀን 2005 ዓ.ም.)

የሰመሃል መለስ ዜናዊ 5 ቢሊዮን ዶላር ጉዳይ

የኢትዮጵያ መንግስት ግልፅነትና ተጠያቂነት በሀገሪቱ እንደሚያስፈልግ የተለያዩ ተቋማት በቢሮው ግድግዳ ላይ አሊያም አንድ ለእና በሆነው ኢቴቪ በአመራሮቹ ቢደሰኮርም ከወሬ ባለፈ ሲተገብሩት ግን አይታይም፡፡ በዚህም ምክንያት በሀገሪቱ ግልፅነትና ተጠያቂነት የወሬ ቃልኪዳን እንጂ የተግባር ሲሆን ባለመታየቱ የተለያዩ አስገራሚ ክስተቶች እየተሰሙ ይገኛሉ፡፡ ከነዚህም መካከል የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት የገንዘብ ሙስና ዋነኛው ነው፡፡meles
ሟቹ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ በገንዘብ በኩል ደሃ ነኝ ሲሉ ከርመው ግብዓተ መሬት ከተፈፀመላቸው በኋላ በ http://www.therichest.org/celebrity networth ዓለም አቀፍ ድህረገፅ አማካኝነት በዓለማችን ካሉ ጠቅላይ ሚኒስትሮች በ 3 ቢሊዮን የአሜሪካድን ዶላር ሁለተኛ ሃብታም መሆናቸውን አነበብን፡፡ ድህረገፁ ይዋሻል እንዳይባል እስካሁን ቅሬታ ያልቀረበበት፣ተዓማኒነትና ተቀባይነት በመኖሩ የተለያዩ የበለፀጉ የዓለም ሀገሮችን ጨምሮ የተለያዩ ሀብታም ነጋዴዎችንና የሀገር መሪዎችን ሃብት መዝግቦ ይፋ ያደርጋል፡፡ በዚህም መሰረት የደሃዋ ሀገር በተለይም ከ12 ሚሊዮን በላይ ህዝቧ በቀን አንድ እንኳ የሚላስ የሚቀመስ ምግብ አጥተው ዜጎቿ በርሃብ የሚሰቃዩበትን አንዳንዶቹም እንደቅጠል በሚረግፉባት ኢትዮጵያ መሪ የነበሩት አቶ መለስ ባለፀጋ መሆናቸውን አበሰረን፡፡
ሰውዬም ሆኑ ባለቤታቸው ወ/ሮ አዜብ መስፍን በፖለቲካ ስልጣን የሀገር መሪ ከመሆናቸው ውጭ ምንም ዓይነት ሃብትም ሆነ የንግድ ስር ዘርፍ እንደሌላቸው እንዲሁም ደሃ ነን ሲሉ ለሀገሬው ህዝብ አዋጅ አዋጅ ማለታቸው በተለያየ ጊዜ በቴሌቪዥን የተናገሯቸው ቃላቶች ምስክሮች ናቸው፡፡ እኛም ያንን አምነን በገንዘብ ደሃ ናቸው ብለን ለማመን ስናገራግር ኸረ ከበርቴ ናቸው የሚል መረጃ ብቅ አለ፡፡የሳቸው ሳያንስ ሰሞኑን ደግሞ የልጃቸው ሰምሃል መለስ የ5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ቼክ እነሆ እኔም አለሁኝ አለ፡፡

የአቶ መለስ ዜና እና የወ/ሮ አዜብ መስፍን ልጅ የሆነችው ሰመሃል መለስ በአሜሪካ በአንድ ኒዮርክ በሚገኝ ባንክ የ5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር የምታንቀሳቅስበት ቼክ መገኘቱ በእንግሊዝ ፓርላማ እ.አ.አ. ሐምሌ 10 ቀን 2013 ዓ.ም. (ሐምሌ 2 ቀን 2005 ዓ.ም.)ተገለፀ፡፡ ለዚህም ሰመሃል መለስ ብሩን የምታንቀሳቅስበት ቼክ ቅጂ ነው የተባለውም ከላይ እንደምትመለከቱት በአስረጅነት አብሮ ቀርቧል፡፡ ይህንንም ያቀረቡት በእንግሊዝ አንድ ዩኒቨርስቲ ውስጥ መምህር የሆኑትና የአቶ መለስን አስተዳደር በማስረጃ አስደግፈው እጅግ የሚኮንኑት ዶ/ር ወንድሙ መኮንን ናቸው፡፡semehal
በአሁን ሰዓትም ሰመሃል መለስ 5 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር በስሟ ታንቀሳቅሰዋለች ስለተባለው ጉዳይም ጉዳዩ የቀረበለት በእንግሊዝ ፓርላማ የአፍሪካ ጉዳይ ኃላፊ በሆኑት ሚመለከታቸው አካላት የማጣራት ስራ እየተሰራ እንደሆነም እየተገለፀ ይገኛል፡፡ በተለይ የኢህአዴግ አጋር በመሆን፣ ለመለስ አስተዳደር ጥብቅና በመቆምና ለኢትዮጵያም ከፍተኛ እርዳታ በመስጠት የምትታወቀው እንግሊዝ በሰማል መለስ ስም ተቀመጠ የተባለው ብር ትክክለኛ ሆኖ ከተገኘ የራሷን እርምጃ ልትወስድ እንደምትችል ይጠበቃል፡፡
አሁን አቶ መለስ ልጅ ስም ሰነድ(ቼክ) ተገኘ በተባለውም ሆነ የኢህአዴግ ባለስልጣናት ቅዱስ አድርገው የሚስሏቸው አቶ መለስ አላቸው ስለተባለው 3 ቢሊዮን ዶላር የኢትዮጵያው የስነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽንም ሆነ እራሱ መንግስት እስካሁን የሰጠው ምላሽም ሆነ ማስተባበያ የለም፡፡ ይህ የሚያሳየው ደግሞ መንግስት አቶ መለስም ሆኑ ልጃው ሰመሃል አላቸው የተባለውን ቢሊዮን ዶላሮች አምኖ ተቀብሏል እንደማለት እንደሆነ እየተነገረ ይገኛል፡፡
በተለይ የህግ ባለሙያው አቶ ዘረሰናይ እንዳሉት ከሆነ የአባትና ልጅ ቢሊዮን ዶላሮች ጉዳይ ደግሞ ሙስናን እታገላለሁ ለሚለው የአቶ ኃይለማርይም አስተዳደር እንዲሁም ለፌደራሉ የስነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ትልቅ ፈተና ነው፡፡ ምክንያቱም ይህ ጉዳይ ምላሽ ተነፍጎት የመንደር ሌቦችንና ትናንሽ የመንግስት ሌቦችን እዣለሁ መባሉ ከእንግዲህ የሚታመን እና የሚዋጥ እንደማይሆን አስተያየቶች እየተሰጡ ይገኛሉ፡፡
መንግስት በበኩሉ ከእንግዲህ ሙስናን ለመዋጋት መታገስ አይገባኝም ቢልም ሰርዓቱ በራሱ የሙስና ተግባር ላይ መሰረት ያደረገ በመሆኑ መያዝ የሚገባቸውን ጨክኖ አይዝም በሚል ይታማል፡፡ ከፌደራሉ የመንግስት ሰራተኞች በተጨማሪ በክልሎች ላይ ስልጣናቸውን ተገን በማድረግ ሙስና የሚፈፅሙ የመንግስት ሰራተኞች ላይ በቅርቡም በኦሮሚያ ክልል እርምጃ መወሰድ መጀመሩን እሰየው፣ በሌሎችም በሁሉም ክልሎች ተጠናክሮ ይቀጥል የሚሉ እንዳሉ ሁሉ የለም ህዝብ የሚያውቃቸው ባለስልጣናት እስካልተያዙ ድረስ በዚህ መፎከር ተገቢ አይደለም የሚሉ አልታጡም፡፡
በተለይ ሰሞኑን የአቶ መለስ ልጅ አላት በተባለው ገንዘብ ዙሪያ እሳ የየትኛውም መንግስት ሰራተኛም ሆነ ነጋዴ ስላልሆነች የገንዘቡ ትክክለኛነት ከተረጋገጠ ወላጆቿ ስልጣናቸውን አላግባብ በመጠቀም ከህዝብ የዘረፉት ስለሚሆን ጉዳዩ ትኩረት ተሰጥቶት ምላሽ ሊቸረው እንደሚገባ እየተጠቆመ ይገኛል፡፡ ይህም የተለያዩ የማኀበራዊ ድህረ-ገፆች ላይ በስፋት መወያያ እየሆነ መገኘቱ ጉዳዩ ይበልጥ ትኩረትን ስቧል፡፡ ይህንንም ተከትሎ መንግስት በተለይ ከዳያስፖራ የአባይ ግድብን ጨምሮ ለተለያዩ ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ ድጋፍ ቢጠይቅ እንኳ አሉታዊ ተፅዕኖ ይኖረዋል፡፡ ዓለም አቀፍ ለጋሾች ምንም እንኳ ሁልጊዜም ቢሆን ድጋፍ ሲያደርጉ ከሀገሮቹ ይልቅ የራሳቸውን ጥቅም ታሳቢ ቢያደርጉም ለኢትዮጵያ የሚሰጠው እርዳታና ብድር ለባለስልጣናቱ ኪስ ማደለቢያ ነው በሚል የራሳቸውን እርምጃ እንዲወስዱ እንዲህ ዓይነቱን መረጃ የሰሙ ዜጎቻቸው ለኢትዮጵያ የሚደረገውን ድጋፍ በመቃወም አሉታዊ ተፅዕኖ ማሳደራቸው አይቀርም፡፡

ምንጭ፡- ኢቦኒ መፅሔት

ወጣቱ ወዴት እየተመራ ነው?

ብስራት ወ/ሚካኤል

ልማት ትርጓሜው እጅግ ሰፊ ቢሆንም ጥቅል ሐሳቡ ግን ለሰው ልጆችም ሆነ የተፈጥሮ ሚዛንን በመጠበቅ በማኀበረሰቡ ዘንድ ይሁንታን ያስገኘ ለኑሮ ተስማሚ ሁኔታን በመፍጠር ውጤታማ የሆነ ተጨባጭ እውነታን ያዘለ ክንውን ነው፡፡ ይህም ሰብዓዊና ቁሳዊ ይባላል፡፡ ይህን በተመለከተ በተለይ ሰብዓዊ ልማት የሚባለው ቁሳዊ የሚባለውን ልማት ሊያመጣ የሚችል የሰው ልጆች የባህሪ አስተሳሰብ አዎንታዊ ለውጥ ነው፡፡ ይህ ለውጥ የማኀበረሰቡን በጎ አሴቶችን አጠናክሮ በመቀጠል አሉታዊ የሚባሉትን በማረምና አዳዲስ አዎንታዊ ለውጦችን ከልማዳዊ አኗኗር ጋር በማስማማት በስልጣኔ ቀላልና ምቹ ሁኔታን መፍጠር ነው፡፡ ያኔ ቁሳዊ ልማቱን በሚፈለገው ደረጃ ማምጣት ይቻላል፡፡ የዚህ ልማት ውጤታማ ተግባርና የስልጣኔ ዝመና ሽግግር ትልቁን ሚና የሚጫወተው ወጣቱ ሲሆን ለዚህም አበረታች የሞራል ስንቅ ያስፈልጋል፡፡
በተለይ በኢትዮጵያ ከሀገሪቱ አብላጫው የህዝብ ቁጥር ልቆ የሚታየው ወጣቱ ነው፡፡ የዛን ያህል ደግሞ ከምርታማነት ይልቅ ጥገኛ እንዲሆን የተፈረደበት ይመስላል፡፡ በተለይ በአሁን ወቅት በኢትዮጵያ የራሱን ዕድል በራሱ መወሰን ተስኖት ሌሎች የሚመርጡለትን፣ የመረጡለትን በመጠበቅ ጊዜውን ሲያባክን ይታያል፡፡ ይህ ማለት ግን አኩሪ ተግባር እየፈፀሙ ያሉ ወጣቶች ጭራሽ የሉም ማለት አይደለም፡፡ ይሁን እንጂ ከለው ቁጥር አንፃር ሲታይ አብዛኛው ወጣት በብዙ ነገሮች ጥገኛ እንዲሆን በመገደዱ እራሱን እንዳይመለከት ጋርዶታል፡፡
ድሮ ድሮ እንኳን ስለራሱ፣ ስለሀገሩ ከዛም አለፍ ሲል ስለሌሎች ይጨነቅ የነበረው ወጣት ዛሬ ስለራሱ በራሱ መወሰን ተስኖት የተመረጠለት ካልተስማማው የመጨረሻ ምርጫውን ስደት ሲያደርግ ይስተዋላል፡፡ በዚህም መሐል ህጋዊና ህገወጥ የሚል ስያሜ ይሰጠዋል፡፡ ይሁን እንጂ ለስደት የዳረገውን ምክንያት ግን ደፍሮ የሚገልፅ አካል አልተገኘም፡፡ እንግዲህ እንዲህ የተፈረደበትን ወጣት ሀገር እያሳጡት ሀገር ተረካቢ እየተባለ ይቀለድበታል፡፡
ወጣትነት እጅግ ፈተና የበዛበት የተፈጥሮ የእድሜ ሂደት አካል ቢሆንም በርካታ ውጤታማ ስራዎችን ለመስራት ግን ከየትኛውም የዕድሜ ክልል የተሻለ ነው፡፡ የመኖሪያም ሆነ የመዋያ ምርጫው በሌሎች መልካም ፈቃድ ላይ ብቻ የተወሰነ በመሆኑ በተለይ በኢትዮጵያ ያለው ክስተት ወጣቶች ሆን ተብሎ ምርታማ እንዳይሆኑ የሚሰራ ይመስላል፡፡ ለዚህም ማረጋገጫ ይሆነን ዘንድ ጥቂቶቹን እንይ፡፡
የወጣት ማዕከላት
ቀደም ባለው የደረግ ስርዓት ግልፅና ቀጥተኛ ሶሻሊስት የነበረ ቢሆንም ወጣቱን በእስፖርትና በሌሎች የኪነ ጥበብ ዘርፎች ለማጎልበት ይረዳ ዘንድ በርካታ የተለያዩ የወጣት ማዕከላት ነበሩ፤ አሁን በነበሩ ቀረ እንጂ፡፡ በወቅቱ በተለያዩ ከተሞች ከስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳ እስከ ሙዚቃና ቴአያትር (ድራማ መለማመጃ) በየከተማ ቀበሌው ይገኝ ነበር፡፡ለወጣቶቹ ታስቦ በተሰሩት ሜዳዎችና አዳራሾች ወጣቱ በአግባቡ ይጠቀምበት የነበረ ቢሆንም ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ነፃ የሐሳብ መንሸራሸርን በተመለከተ ግን ከስርዓቱ ውጭ እንደማይፈቀድ በግልፅ ስለሚታወቅ ጎጅ ቢሆንም ብዙም የሚገርም አይደለም፡፡
ዛሬ ደግሞ በአንፃሩ የነበሩ ሜዳዎች ዳግም ባናያቸውም በወጣቱ መዝናኛ ሰም የኢህአዴግ ካድሬ መመልመያ ሆነው አርፈዋል፡፡ የወጣት ማዕከል ተብሎ በተሰሩ አዳራሾች ምንም ከቀድሞ የተለየ ነገር የለም፡፡ ምክንቱም ዛሬም በአዳራቹ ስለ ኢህአዴግ ጥሩነት ለማውራትና የርካሽ ባዶ ፖለቲካ መጠቀሚያ ከመሆን ውጭ ወጣቱ ነፃ የሆነና ያመነበትን ርዕስ አንስቶ መወያየት አይችልም፡፡ ይህ የሆነው ግን በህግ ሳይሆን ከመጋረጃ በስተጀርባ ባልተፃፈው ትዕዛዝ ነው፡፡
በተለይ በአዲስ አበባ በርካታ የቀበሌ አዳራሾች ቢገነቡም እየሰጡት ያለው አገልግሎት ግን ሁሉንም ወጣት ሊያካትት በሚችል የተለያዩ ሐሳቦች ሊንሸራሸሩ በሚያስችል ሁኔታ ሳይሆን በኢህአዴግ ጥላ ለተሰበሰቡት ብቻ ነው፡፡ እንዲህም ቢሆን የሚሰጡት አገልግሎት ቢበዛ ቤተመፅሐፍ፣ ጂም እና የገላ መታጠቢያ አገልግሎት ነው፡፡ በዚህም የወጣቱ ፍላጎት በሁሉም የአዲስ አበባ ከተማም ይሁን በሀገር አቀፍ ምርጫው ሁሉን ያሳተፈ የወጣቱ ነው ማለት አይቻልም፡፡ ይህ ካልሆነ ደግሞ ወጣቱ በፍላጎቱ በልማት ላይ ተሳታፊ ነው ማለት አይቻልም፡፡ምክንያቱም ቁሳዊ የአዳራሽ ግንባታ የወጣቱን አስተሳሰብ በመቀየር ሰብዓዊ ልማት ማምጣት አልቻለምና፡፡
አስተሳሰብን ያህል ነገር ሁሉም በሌሎች ፍላጎትና ምርጫ ተፈጥሮን በሚሽር መልኩ አንድ እንዲሆን እየተደረገ ባለበት ሁኔታ ሁሉን አቀፍ ተሳትፎዓዊ የተደረገበት አሳታፊ ቁሳዊ ልማትን ማምጣት አይቻልም፡፡ ሰርተናል እየተባለ የሚዘፈንለት ቁሳዊ ልማትም ቢሆን የወጣቱን የመንፈስ ልዕልና ሊገነባ ባልቻለበት ሁኔታ በሀገሪቱ ላይ ሁለንተናዊ እምርታ ለውጥ ማየት ይናፍቃል፡፡ ቀድሞ በየአካባቢው የነበሩ ሜዳዎችም ቢሆኑ አንዳንዶቹ በነበሩበት ቢቀጥሉም አብዛኞቹ ባለመኖራቸው፣ አዳዲስ የመኖሪያ ቤት ግንባታ የተደረገባቸውም ሆነ እየተደረገባቸው ያሉ አካባቢዎች የወጣቶች ስፖርት ማዘውተሪያዎች ባለመታየታቸው ዋቱን ወደ አልባሌ ቦታ እንዲውል እያስገደዱት ይገኛሉ፡፡
ጎጂ የደባል ሱስ ግብዣ
በአሁን ሰዓት ወጣቱ በራሱ ጉዳይ እራሱ እንዲወስን ከማድረግ ይልቅ በደባል ሱስ ጥገኛ እንዲሆን የሺሻና ጫት ግብዣ እየቀረበለት ይገኛል፡፡ ይሄም በፊት እንደ ነውር ይታይባቸው በነበሩ አካባቢዎች ሳይቀር ዛሬ ዛሬ እንደመልካም እየታየ እስከ ዩኒቨርስቲዎች መዝለቁ የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡ እነኚህን ድርጊቶች የሚያበረታታ የመንግስት አካል ባይኖር ኖሮ መኖሪያ መንደር ድረስ ዘልቀው ባልታዩ ነበር፡፡
ከከፍተኛ የትምህርት ተቋም የተመረቁና የሚመረቁ ወጣቶችም ቢሆኑ ከ15ዓመታት በላይ በእውቀት ግብይት በትምህርት ቢያሳልፉም ዛሬ ግን 15 ቀናት በማይፈጅ ስልጠና ያውም ጥቂቶችን በኮብል ስቶን ድንጋይ ጠረባ ስራ እንዲሰማሩ ይደረጋል፡፡ በርግጥ ማንኛውም ሙያም ሆነ ስራ የሌሎችን ሰዎች መብትና ጥቅም እስካልነካ ድረስ የሚናቅ ባይሆንም ለዘመናት ያካበቱት እውቀት ግን ሜዳ ላይ ሲወድቅ የሀገር ሀብት በከንቱ መባከኑን ማሳየቱ አይቀርም፡፡ በአሁን ወቅትም የያዝነው 2005ዓ.ም.ን ጨምሮ በየዓመቱ ከ 80 ሺህ በላይ የሀገሪቱ ወጣቶች በተለያየ የትምህርት ዘርፍ ቢመረቁም በሙያቸው የሚሰማሩት ግን 10ሺህ እንዳማይሞሉ ይገለፃል፡፡ ይሄ ደግሞ የእውቀት፣የገንዘብና የጉልበት ብክነት መሆኑ ግልፅ ነው፡፡
በሙያቸው ተደራጅተው የስራ ዕድል እንዳይፈጥሩም ስርዓቱ እና የስነ ህዝብ ፖሊሲው ዜጎችን ሙሉ በሙሉ የመንግስት ኢኮኖሚ ጥገኛ ስላደረገ በሚፈልጉት ሙያ መሰማራት አይችሉም፡፡ ይህንንም ለመቅረፍ የገንዘብ ብድር ቢፈልጉ እንኳ የግድ አብዮታዊ ዴሞክራሲን ተቀብለው በኢትዮጵያዊነት ሳይሆን በኢህአዴግ አባልነት ቅድመ ሁኔታ በየቀበሌ ያሉ ተራ ካድሬዎች ከላይ በሚወርድ መመሪያ መሰረት ለማደራጀት ይሚክራሉ፡፡ ውጤቱ ግን ወጣቱን አምራች ኃይል ከማድረግ ይልቅ የሙያና የኢኮኖሚ ነፃነት ስለሌለው ጥገኛ እንዲሆን አስችለውታል፤እያስቻሉትም ነው፡፡ ይሄ ካልተቀየረ ደግሞ የሀገሪቱ ወጣት ጊዜውን፣እውቀቱንና ጉልበቱን በከንቱ እንዲያባክን ያደርጉታል፡፡
ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ በየመንደሩ እየፈሉ ያሉት የአልኮል መጠጥ ቤቶችና ጭፈራ ቤቶች አንዱ የልማት አካል እንጂ የሰብዓዊ ልማትን ወደ ኋላ የሚያስቀር ተደርጎ አልተወሰደም፡፡ በዚህ ምክንያት ወጣቱ ሰርቶ ከመለወጥ ይልቅ የሰራበትንም በአግባቡ ጥቅም ላይ እንዲያውል ምቹ ሁኔታ እንኳ ሲፈጠርለት አይታይም፡፡
በአንፃሩ ደግሞ ለወጣቱ እጅግ ጠቃሚና አስፈላጊ እንደሆኑ የሚታወቁት የሐሳብ የበላይነት ላይ የሚደረጉ ውይይቶችና ክርክሮች ቦታ ባለመሰጠታቸው እንደ ሚዩዚክ ሜዴይ የመሳሰሉት የንባብን ባህል ለማዳበር የሚረዳው የመፅሐፍ ሐሳብ መወያያ አዳራሽ አጥተው አምስት ኪሎ በሚገኘው በጠባቧ ብሔራዊ ሙዝየም አዳራሽ ማየት ልማት ወዴት ወዴት ያሰኛል፡፡ ባንፃሩ አብዛኛውን ጊዜ የገዥው ኢህአዴግ ካድሬዎች መፈንጫ እየሆነ ያለውና በህዝብ አንጡራ ሃብት የተገነቡት የቀበሌ/የወረዳ አዳራሾች ደግሞ አብዛኛውን ጊዜ ከኢህአዴግ ስራና ካድሬዎች በስተቀር ኸረ የሰው ያለህ እያሉ ይገኛል፡፡ ይህ ሁሉ ታዲያ ለሰብዓዊ ልማት ትኩረት ባለመሰጡ ነገ ሀገር ተረካቢ በሚባለው ወጣት ላይ ይነገድበታል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በፊት የወጣቶች መዝናኛ የነበሩ የስፖርት ሜዳዎችና የመናፈሻ ቦታዎች አንዳንዶቹ የህንፃ ግንባታ ሲሰራባቸው እንደነ ሂልተን አዲስ ሆቴል ፊትለፊት የነበሩ መናፈሻዎች ደግሞ ተከልለው ወጣቶች ዝር እንዳይሉባቸው ተደርገዋል፡፡
ከሌሎች መጠበቅንና መቀበልን መምረጥ
የተሻለ ነገርን በራስ ከመወሰን፤ እንዲሳካም ከመጠየቅ ይልቅ በሌሎች ላይ ጥገኛ በመሆን በሁሉም ነገር የመጠበቅና የመቀበል ብቻ አዝማሚያ በስፋት በወጣቱ ያስተዋላል፡፡ በዚህም የራሱን ጉዳይ ሌሎች እንዲወስኑለት በመፍቀዱ የራሱን ሚና አሳልፎ እየሰጠ ይገኛል፡፡ ስለሆነም ምርጫውን ከመፈለግ ይልቅ የመጣውን ብቻ የመቀበል ጉዳይ በስፋት ይስተዋላል፡፡
አማራጭ ሐሳቦችን ከራስ ጋር አስማምቶ ለመያዝም ሆነ የራስን ምርጫ ለማስተናገድ ይረዳ ዘንድ ነፃ የሆነ የሐሳብ ፍጭት ዕድል በመነፈጉ አሉታዊም ቢሆን ተቀብሎ የራስ ማድረግ እንደ አዋቂነትና ብልህነት እየተወሰደ ይገኛል፡፡ ይሄ ደግሞ የትውልድ የአስተሳሰብ ብክነትንና ምክነትን በማንፀባረቅ ተተኪው ትውልድ ከማለት ይልቅ ጠባቂው ቢባል የሚስማማው ይመስላል ፡፡
ከላይ ለተጠቀሱት ችግሮች ዋነኛ ምክንያት ደግሞ በተለይ በወጣቶች ላይ እየተሰራ ያለው ሰብዓዊ ልማት በቁሳዊ በመሸፈኑ የሚመጣ ኋላቀር እሳቤ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ ገዥው ስርዓት የልማትን አስፈላጊነትና ምንነት በቅጡ ካለመረዳት የሚመጣ ደጋማ እሳቤ ሲሆን እራሱ ወጣቱም ቢሆን በእራሱ ላይ አሉታው ድርሻ እንዳለው ሊዘነጋ አይችልም፡፡ ስለዚህ እምርታዊ |የሀገር ዕድገትና ለውጥ ለማምጣትና ሁሉን አቀፍ ገቢራዊ ልማት ለማስመዝገብ ቅድሚያ ሰብዓዊ ልማት መቅደም ይኖርበታል፡፡ ያኔ ቁሳዊ ልማትን በሚፈለገው መጠንና ዓይነት ማምጣት ይቻላል፡፡

%d bloggers like this: