አንድነት እና መኢአድ የፊታችን ሐሙስ ውህደት ሊፈራረሙ ነው

 

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት(መኢአድ) ነገ ሐሙስ መጋቢት 11 ቀን 2006 ዓ.ም. ቅድመ ውህደት ሊፈራረሙ ነው፡፡ ፓርቲዎቹ እስካሁን በተናጠል የሚደረገው ፖለቲካ ትግል ለሀገሪቱም ሆነ ለህዝቧ እንዲሁም ለራሳቸው አዋጭ አለመሆኑን በማመን ተዋህደው አንድ ጠንካራ የፖለቲካ ማኀበር መስርቶ ለመታገል የሚያስችላቸውን ስምምነት በመጨረስ ቅድመ ውህደቱን ለመፈራረም ቀነ ቀጠሮ መያዛቸው ታውቋል፡፡ ይሁን እንጂ ዋናው የውህደት ስምምነት የሚጠናቀቀው የሁለቱም ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባዔ ጥሪ ተደርጎ ሲፀድቅ ሲሆን፤ከዚህ ቀደም የሁለቱም ጠቅላላ ጉባዔ አባላት ውህደቱ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ ውሳኔ ማሳለፋቸው አይዘነጋም፡፡ በዚህም ምክንያት ስምምነቱ ተጠናቆ የፊታችን ሐሙስ ድርድሩን ሲያካሂዱ የነበሩት አካላትና የሁለቱም ፓርቲ አመራሮች በተገኙበት የአንድነት ፓርቲ ፕሬዘዳንት ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው እና የመኢአድ ፕሬዘዳንት አቶ አበባው መሐሪ ፓርቲያቸውን በመወከል ስምምነቱን እንደሚፈራረሙ ይጠበቃል፡፡udj

ሁለቱም ፓርቲዎች የፕሮግራም ልዩነት እንደሌላቸው የሚታወቅ ሲሆን፤ በተለይ አንድነት ፓርቲ ከዚህ ቀደም ከብርሃን ፓርቲ ጋር በመዋሃድ በፖለቲካው እንቅስቃሴ ለውጥ መፍጠር ችሏል፡፡ አሁን ደግሞ ከመኢአድ ጋር በመዋሃድ ጠንካራ የፖለቲካ እንቅስቃሴ ለማድረግ ስምምነት ላይ ደርሷል፡፡ የውስጥ አዋቂ ምንጮች እንዳረጋገጡት ከሆነ አንድነት ከመኢአድ በተጨማሪ ከሌሎችም ፓርቲዎች ጋር ውህደት ለመፍጠር አንድ ግብረኃይል በማቋቋም ሰፊ ስራ እየሰራ መሆኑንና በቅርቡም ሌሎች ፓርቲዎችም አብረውት ሊዋሃዱ እየተንቀሳቀሱ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡ አንድነት ከመድረክ አባል ፓርቲዎች ጋር በግንባር ተጣምሮ እስካሁን ቢቆይም በአባላቱ የሚጠበቀው ለውጥ ባለመምጣቱ ውህደት ላይ ማተኮሩ ይነገራል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ እንደሚመለክተው ከሆነ፤ በአሁን ወቅት ተመዝግበው የእውቅና ሰርተፍኬት የተሰጣቸው 66 የፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳሉ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጂ ከአራት ፓርቲዎች ውጭ ሌሎቹ ከምርጫ ወቅት በስተቀር የት እንዳሉና ምን እየሰሩ እንደሆነ ለማወቅ አልተቻለም፡፡ በዚህም ምክንያት ህዝቡ በተለያየ ጊዜ በጥቂቱም ቢሆን ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችን ከተናጥል ይልቅ አንድ ጠንካራ የፖለቲካ ድርጅት ሆነው እንዲቀርቡ በተደጋጋሚ መጠየቁ ይታወሳል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: