Monthly Archives: April, 2017

አቶ አሰፋ ጫቦ አረፉ

ዮሐንስ ሞላ

አቶ አሰፋ ጫቦ ከአባቱ ከጫቦ ሣዴ ሃማ ያሬና ከእናቱ ከማቱኬ አጀን ከተራራ አናት ላይ ከሚገኝ ሜዳማ ቦታ ላይ ጨንቻ ከተማ ነው የተወለደው፡፡ከጋሞ ሰንሰለት ተራራዋች አንዱ ጫፍ ላይ የሚገኝ ጠረጴዛ ነው ይላታል ጨንቻን ሲገልጣት ከ2-6ኛ ክፍል እዚያው ጨንቻ የተማረ ሲሆን በዘጠኝ ዓመቱ የጨንቻ ገብርዔል ዲያቆን በመሆንም አገልግሏል በድቁናው ባገኘው ካፒታልም ጥቂት የዶሮና የበግ ግልገል ገዝቶበታል ሐሙስ ሐሙስን እየጠበቀ ኤዞ ገበያ ዶሮና እንቁላል አየነገደ ይውል ነበር ከእነሱም ውስጥ ት/ቤት ድረስ እየተከተሉ ያስቸግሩት የዶሮና የበግ ግልገልም ነበረው እንደፈረንጆቹ pet መሆናቸው ነው፡፡

Assefa Chabo
የ8ኛ ክፍል ትምህርቱን በሻሸመኔ በኃላ ታሪኩን ሲያውቅ ስሙን ካላስቀየርኩ ብሎ ከታገለበት ከአጼ ናኦድ ት/ቤት ከ39 ተማሪዎች አንዱ በመሆን ነበር የተከታተለው የተዋቀረበትን ዋልታና ካስማ ያየበት ቆይታው በጋሞ ውስጥ ካሉ 40 ከሚሆኑ ‹ካዎ›ች አንዱ በሆኑት በዘመዱ በቀኛዝማች ኢሌታሞ ኢቻ ቤት በኖረበት ወቅት ነበር፡፡

ሲገልጻቸውም ‹በኢሌታሞና በሰዋች መሀከል የግንኙነት አጥር የለም፡፡ወግ ሳያበዙ ለህዝብ አሳቢና ተቆርቋሪ ናቸው ነው› የሚላቸው የጋሞ ካዎ የሚፈራ ሳይሆን የሚከበር ነው ይለናል፡፡ ገና በልጅነቱ ለህዝብ በመስራት እርካታ ማግኘት እንደሚቻልም የተገነዘበው በጉሌታ-አንዱሮ ግብር ተቀባይ ተደርጎ በቀኛዝማች ኤሌታሞ ሲመደብ ነው ፡፡ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ከአዲስ አበባ ከኮከበ ጽባህ አቋርጦ ሲቪል አቪዬሺን ተቀጥሮ ባህር ዳር ሄደ፡፡ ‹ሀ› ብሎ የመጀመሪያውን ስራውንና የመጀመሪያ ልጁንም ያገኘው ጎጃም ነበር፡፡ ‹ጎጃሜ ተነቀለ› ብሎ ፖሊስና እርምጃው ላይ ጽፎ ጠፍቶ እስከወጣ ድረስ እዚው ነበር፡፡ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሕግ ት/ቤት LLB አግኝቶ የተመረቀ ሲሆን በዓለም አቀፍ የህግ ተማሪዋች ውድድር ከውጭ የምስክር ወረቀት ከንጉሱም የወርቅ ኦሜጋ ሰዓት ተሸልሟል፡፡

በ 1960 የህግ ተማሪ ሆኖ በአፍሪካ አዳራሽ የቀድሞ ተማሪዎች ማህበር ስብሰባ ላይ ከመጮህ ጀምሮ ይህው እስከእልፈተ ሞቱ ድረስ ለአገርና ለወገን ዋይታውን አላቋረጠም ነበር ፡፡ በአጠቃላይ የአጥቢያ ፍ/ቤት ጸሐፊ፤የበጅሮንድ ጽ/ቤት ተላላኪና ጸሐፊ የአየር መርማሪ (metrology) የህግ አማካሪ ሆኖ ሰርቷል፡፡በፖለቲካው መስክ ከተማሪዎች ንቅናቄ ባሻገር የሁለት ድርጅቶች መስራችና መሪ ሲሆን ከ 1966-1967 የልጅ እንዳልካቸው አዲሱ ካቢኔና የደርግ አውራጃ አስተዳዳሪ ሆኖ ጋርዱላ ሄዶ ነበር፡፡ በጄኔራል መብራቱ ፍስሃ ታስሮ እስከተባረረ ድረስ የፖለቲካ ድርጅት መስራችና መሪ፤የአውራጃ አስተዳዳሪ የመንግሰትና የባለስልጣን አማካሪ፤የህዝብ ተከራካሪ በመሆን በለውጡ ውስጥ ሰርቶእል፡ ፡

በኃላም በራሱ ከግቢ የመራቅ ጥያቄ አነሳሽነት ‹‹በችሎታው መጠን ሥራ ይሰጠው›› የሚለውን ሻምበል ፍቅረስላሴ ወግደረስ የፈረመበትን ደብዳቤ ይዞ መገናኛ ሚኒስቴር ወረደ፡፡ ከዚያ ነው እንግዲህ በየካቲት 1971 ዓ.ም መጀመሪያ ወደ ደርግ ጽ/ቤት ታፍኖ ተወስዶ ከዚያም በማዕከላዊ ታስሮ ከ 10 ዓመት ከ 6 ወራት ከ 6 ቀናት በኃላ የተፈታው፤ ማዕከላዊ እስር ቤት የሰው ገበያ ነበር ብሎ ሲገልፀው በ10 ዓመት የእስር ዘመኔ ውስጥ ከ100.000ሺ በላይ ሰው አይቼበታለው ይለናል ካያቸውም ውስጥ በባህርይ፣በቁመና፣በአለባበስና በስነምግባራቸው ጥሩ አድርጎ በመጻህፉ ውስጥ ይገልጻቸዋል፡፡

እንደተፈታም የአስኮ ጫማ ሱቅ የነበረበት ፎቅ ላይ የጥብቅናና የንግድ አማካሪ ቢሮ በመክፈት ሙግቱን አስረዝሞ ገንዘብና ጊዜ ከማባከን ይልቅ አስቀድሞ በድርድርና ከፍ/ቤት ውጭ ለመጨረስ ያደረገው ጥረትም ከዚሁ ከራሱ ማንነት የመነጨ ነው፡፡ በሽግግር መንግስቱ የምክር ቤት አባል በመሆንም በ 1983 አርባ ምንጭ ሄዶ ነበር ሁሉም አልሆን ሲለው ያለውዴታ በግድ አሜሪካ በስደተኝነት መጥቶ መኖሩን ጀመረ፡፡

በተፈጥሮው ሰው መጥላት የማይፈልገው አንጋፋው የሰብዓዊ መብት ተሟጋች፣ ቀጥተኛው፣ ብዕረኛው አቶ አሰፋ ጫቦ የ 73 ዓመት ባለዕድሜው የአራት ልጆች አባትና የዘጠኝ ልጆች አያት ነበር ፡፡

‹የትዝታ ፈለግ› በሚል ርዕስ ለንባብ ያበቃውን መጽሐፉን በምናነብበት ወቅት ብዙ ወደማናቃቸው ጊዜያትና ግለሰቦች ከመውሰዱም ሌላ የአጻጻፍ ውበቱ እጅግ ያስደንቃል የባህሪይ አቀራረፅ ችሎታውና የአካባቢ ስዕላዊ መግለጫው ያረካል ‹‹ነፍጠኛ›› ማለት አማራ ብቻ ነው ማለት እምነት እንጂ እውነት አንዳልሆነና ‹‹ነፍጠኛ›› በሚል የሚበጠብጠንን ጥያቄ ለመመለስ ናችሁ የተባልነውን ሳይሆን ውስጣችን ገብተን ሆነን ያለነውን እንድናስተውል ይጎተጉተናል፡፡
ዋታካዳ እንደሚጠሩት ‹‹ጋንታይናው›› ‹ጋትዬ› አሰፋ ጫቦ ዛሬ አብዛኛው እየፈራ እየሸሸ ምክንያቱን በሚደረደርበት ወቅት እሱ ምን አቅብጦኝ ከደርግ ጋር ገጠምኩ; ብሎ አያውቅም አምኖ እንጂ ምናምን ፍለጋ ወይም ሰው ገፍቶት እንዳልገባ በግልጽ አስቀምጦልናል እንዲያውም ‹በመሸ በጠባ ቁጥር በጥሼ የምቀጥለው ማተብ› የለኝም ይል ነበር በንባብ የዳበረ የበሰለ መሆኑን ከማሳየቱም ሌላ ስለ አሜሪካ መምጣትና መኖር ያካፈለው ምክር በቀላሉ የሚታይ አይደልም ስለስደቱ ዓለም ችግርና ውጥንቅጥ ሲጽፍም ስደተኛው በሃብት ድህነትና በአእምሮ ድህነት መሃከል ያለው ልዩነት የጠፋበት መምሰሉን ፍንትው አድርጎ አቅርቧል በአጠቃላይ ጆሮ ጠገብነት ማወቅን አለመተካቱን ያሳውቀናል
ጀግና ፍለጋ ጦር ሜዳ መሪዋች አምባ የፖለቲካ ሰዋች አምባ እንሄዳለን፡፡

ሲገኝ አገር ያውቀዋል ፀሃይ ይሞቀዋል ያልታወቁ በየቤቱ የታጨቁ ተራሰው የሆኑ ያልተሰጣቸውን በመፈጸም የጀግኑ አሉ ይላል ጋሞ ይላል ፤ ጋሞ ግብር ገበረ እንጂ ሥርዓቱን አልገበረም በማለት ጥፋቱን ስህተቱን በማመን መቀበልና ባደባባይ ይቅርታ መጠየቅ የጋሞነት ገላጭ አብሮ የተወለደ የውሰጥ ባህርይ መሆኑን በመተንተን ለየት ስላለው የአገርና የህዝብ አስተዳደር ሥርዓት ሲያጫውተን አንዳንዶቻችን በአገራችን ውስጥ ይህ መኖሩን ባለማወቃችን እንቆጫለን ወደዛሬያችን ለማምጣት በምኞት እንጋልባለን
ሌላው የጋሽ አሰፋ ትልቅነቱ እንደአንዳንዶቹ ፀሃፊዋች በራሱ አራት ነጥብ ዘግቶ እመኑልኝ ሳይለን ያየሁትና የኖርኩት እንጂ ያጠናሁት አይደልም ይላል በትዝታዋቹ ውስጥ እየሾለከ የሁላችንንም ትዝታ የቆሰቆሰውን ያህል ዛሬ በአገራችን ስለተንሰራፋው ሥርዓትም በማዘን እየገለጸ ወደተሻለ እንድንጓዝ ይማፀነናል፡፡

በእስራት ብዛት የህዝብ ነጻነት ታፍኖ የቀረበት ዘመንም አገርም አለመኖሩን በማስረገጥ የጋራ ቤታችን የሚፈለገውን መጠነኛ ጥገና በማካሄድ ፈንታ መናድ የመረጡትን አውግዞአቸዋል፡፡አገራቸውን ባለማወቅ ወይም ለማወቅ ባለመፈለግ ነቀዝ የበላው ቤት እንድትሆን ስለማድረጋቸው በመውቀስ ወደምትፈለገዋ ከስህተቷ ልምድ የቀሰመች አዲሲቷ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጽያን እንድንገነባ ይጣራል፡፡

አብርሃም ሊንከን እንዳለውና ጋሽ አሰፋም በመጽሃፉ ላይ እንደጠቀሰው ‹‹ማንንም ያለቂም እንድንመለከት፣ሁሉንም በልግስና እንድናቅፍ፣በሃቅ ላይ እንድንጸና፣አምላክም ይህንን ሐቅ እንድናይ እንዲረዳን እንማጸን፡፡

ጋሽ አሰፋ ጫቦ ያመነበትን እንደተናገረና እንደሰራ ሃገርና ወገኑን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ እንደደከመ አለፈ፡፡ ይህን ታላቅ ሰው በህይወቱ እያለ በጣይቱ የትምህርትና የባህል ማህከል ጋብዘን በማስተናገዳችን ክብር ተሰምቶናል ፡፡ ብዕረⶉቻችን ጀግኖቻችን ጠበብቶቻችን ሳያልፉ ማክበር ግዴታችን መሆኑን እናምናለን፡፡

~ ጣይቱ የባህል ና የትምህርት ማህከል

Addis Ababa: When Name and Reality Don’t Match Up

Kebour Ghenna

Translate ‘Addis Ababa’ to a foreigner and her eyes glaze over at the thought of miles of beautiful parks, boulevards and streets lined up with ornamental prune trees, and pedestrian-friendly clean neighborhoods. Alas, the reality could not be further from the truth. Addis Ababa is today a dense, brutal, and crowded city, with serious deficiencies in housing, drinking water, power, sewerage, solid waste disposal, and other services. Everywhere we look, we see evidence of unthinkable inequality, deprivation and filth.

The Addis Ababa municipality office

Fifty years ago, my father likened to say ‘There is no garden in Addis Ababa… Addis is in a garden.’ I suppose with the speed of growth Addis witnessed in the past few decades, and the scarcity of means with which it could respond to it, things must have gone out of control. Yes, cities are messy, complex places to administer. But what cities can be, is smarter about how they approach the issue. Today, Addis Ababa has the exclusive opportunity to reinvent its city centre. It can not only rejuvenate itself, but also give a preview of how an African City of the 21st Century could look like and function.

These last ten years, as large amount of area is freed up right in the heart of the city, the chance to plan a completely new activity centre for the city has arisen. Unfortunately, the redevelopment so far seems to be utterly sterile. Look at Arat Kilo (my home quarter), where there was once a vibrant community, busy alleys, family owned businesses, artisan workshops, small soccer fields and more, is today being replaced by new residents, soulless new assemblage of buildings with absolutely zero character or taste. And yet, poor Arat Kilo could have been one of the tourist attraction of the city, had it been allowed to keep its mixed-use habitats, and high-density neighborhoods and was provided with sewage systems, water, electricity, roads, wi-fis and other state of the art amenities, regardless of how slummy or messy it looked.

Go further to AYAT and beyond, a featureless new quarter.
Over the past decade and a half, the nation’s developers and government officials have replicated discredited urban planning templates, importing ideas that were tested, failed and long since abandoned in places like Europe and the US.
But the most amusing development of all is the attempt by the city to create a so called financial centre between Mexico Square and the National Bank of Ethiopia – which meant for the authorities replicating the plans for the Loop in Chicago or Canary Wharf in London, or Wall Street in New York. Here the containers are mistaken for the contents. But no one goes to Mexico Square to see the buildings.

That’s not all, now check out the development around the UNECA, where monotonous hotel buildings and bunch of apartments completely masked one of the magnificent UN campuses in the world. Today that complex is almost out of sight. A repeat around the AU Commission campus may be developing.

In the whole, the wrong sort of architecture and urban planning has been favored – an approach that favors, horizontal grouping of buildings (of any kind) instead of, say, business. And what’s frightening is the lack of citizens’ engagement in policymaking and the design of public services. So, to any Addis Ababian willing to listen – before it’s too late – it’s time to claim back the essence of the new flower or the image of Addis Ababa.
Here are six modest ideas:

First, let’s decide on the kind of city we, the citizens, want to have and then start rebuilding our city the way we want it. Ideally government should provide the land and the infrastructure, but beyond that, we should be free to build what we need, neighborhood by neighborhood, each with its own main street, shops, banks, schools, hospitals, entertainment centers etc . Each complex becoming a small town, and their numbers would make up this sprawling capital. Indeed, this was how Addis was founded at the start of the 20th century, with the then aristocrats and army commanders setting up their own camps i.e. Ras Mulugeta Sefer, Dejazmach Zewedu Abba Koran, Dejach Wube are some among others.
Today, many misunderstand Addis Ababa as informal and illogical because of the dualist notion of the city as divided into polar opposites: Urban and rural, rich and poor, formal and informal, order and mess. But Ethiopian culture accepts that mess and order are inseparable: this is why Ethiopians are so tolerant of urban forms that the West would see as “irrational” or “messy” — neighborhoods develop and slowly integrate with the larger urban system on their own terms. Addis was built with no zoning rules to become a fantastically integrated mixed-use city. With some imagination, involvement, and incremental development we can still build what would be a prosperous city where the inhabitants would preserve their customs and social organization. In other words, a city with character.

Second, let’s make (not talk) Addis the greenest city of Africa, a city that builds electric light train, but also provides a new way of thinking about urban living. A city moving from a consumer society to a collaborative society; a city that has high acceptance of public transit, bicycle pathways, and pedestrian walkways; a city that can encourage and support residents to grow their own food. Utopia? Not at all! It is in fact within our ability to change, say, within a time span of twenty years. Encouraging, say, small plot or integrated farming, known as permaculture, is an initiative everyone can be involved in, and make a small difference in their community and surrounding environment, it can even create employment, lots of it, for young people. As you might imagine, for a green future in Addis Ababa, multiple actions need to be taken: from localized high-level policy frameworks, to harnessing residents’ love for nature.

Third, let’s rethink our deference to car travel (a copy paste of another value and culture) and stop crafting our landscape around automotive transport. Look at New York city, note the compactness of its development, the fertile mix of commercial and residential uses, and the availability of public transportation. All that has made automobile ownership all but unnecessary in most of New York city. So why not adopt the same vision for Addis, and promote biking, buses and modern traffic systems, as well the building of pleasant sidewalks.
Fourth, let’s stop pushing out lower wage residents and service workers out to the far-off peripheries, where opportunities are fewest, where they can barely afford to live, and where their economic conditions continues to sink. Aren’t they part of the fabric of Addis Ababa? The future of our city should not be a city of dull, boring, rich people only.

Fifth, let’s build an inclusive Addis Ababa with strong community bonds, incorporating resilience, innovations and technologies in areas such as infrastructure, governance and security. For this is a necessary first step to get political, business and civic leaders to agree on a shared vision and common agenda for joint action on the city’s economic growth and inclusion. Of course collaboration does not happen naturally, particularly in view of past experiences and the way our Kebeles work, where politics and the ruling party members dominate the discourse. Still, I think residents can come together and make Addis a hotbed of high tech and the leading startup cities in Africa. Let’s catch up Nairobi and Kigali.

Which leads me to my sincerest piece of advice: If we have any ambition for creating inclusive, resilient, green, healthy, just, smart or livable Addis Ababa, then we should, above all, effectively tackle corruption.

በቅርቡ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ሌተናት ጀነራል ጃጋማ ኬሎ የቀብር ስነ ስርዓት ተፈፀመ

ኢትዮጵያዊው ስመ ጥር ጀግና “የበጋው መብረቅ” አርበኛ ሌተናት ጀነራል ጃጋማ ኬሎ በተወለዱ በ96 ዓመታቸው መጋቢት 29 ቀን 2009 ዓ. ም. ይህችን ዓለም የተሰናበቱ ሲሆን፥ የቀብር ስነ ስረዓታቸውም ዛሬ እሁድ ሚያዝያ 1 ቀን 2009 ዓ. ም. በአዲስ አበባ መንበረ ጸባዖት ቅድስት ስላሴ ቤተ ክርስቲያን በክብር ተፈፅሟል።

General Jagema Kello.jpg

አርበኛው ጃጋማ በ1913 ዓ ም በቀድሞው ሽዋ ጠቅላይ ግዛት በምዕራብ ሸዋ በመጫና ጅባት አውራጃ፥ ጊንጪ ልዩ ስሙ ደንቢ ዮብዲ በሚባል ስፍራ ባላባት ከነበሩት ወላጆቻቸው ከአባታቸው ኬሎ ገሮ እና ከእናታቸው ወ/ሮ ጠላንዱ ኢናቱ በ1913 ዓ. ም. ተወለዱ። ወላጅ አባታቸውን በሞት ያጡት ጃጋማ ፥ የአድዋውን ሽንፈት ለመበቀል በአጼ ኃይለስላሴ ዘመን ጣሊያን ከ1928 1933 ዓ ም በኢትዮጵያ ላይ ዳግም ወረራ ባካሄደበት ወቅት ገና የ15 ዓመት ወጣት የነበሩት ጃጋማ፥ የሀገራቸውን ሉዓላዊነት እና ክብር ለማስጠበቅ አንድ የአጎታቸውን የእጅ የጦር መሳሪያ በመያዝ ሁለት የአጎታቸውን ልጆች አስከትለው ጫካ ገቡ።
General Jagama Kello 2.jpg

ከዚያም ሌሎች ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ወጣቶችን በማሳመንና በማስከተል በዕድሜና በልምድ የሚበልጧቸውን ጨምሮ ያለምንም ሳይንሳዊ ወታደራዊ ስልጠና ከ3000 በላይ አርብኞችን በመምራት ለድል በመብቃት ሀገራቸውን አስከብርዋል።

በአምስቱ ዓመት የጣሊያን ወረራ ወቅት ለፈፀሙት ጀብዱ ከንጉሰ ነገስቱ ከቀዳማዊ አጼ ኃይለስላሴ የወርቅ የእጅ ሰዓት እና ከበርጅን የሚባለውን ልዩ ካባ ተሸልመዋል።

General Jagema Kello 2

ከድል በኋላ በሀገር ውስጥና በአሜሪካ ሳይንሳዊ የሆነውን ዘመናዊ ወታደራዊ ስልጠና እና አስተዳደር ትምህርቶችን በመከታተልም በወቅቱ የሀገሪቱ የመጨረሻ ከፍተኛ ወታደራዊ የሌተናት ጀነራልነት ማዕረግ ላይ ከመድረሳቸው በተጨማሪ፥ የሀገሪቱ የጦር አዛዥ እና በተለያዩ የሀገሪቱ ጠቅላይ ግዛቶች ሀገረ ገዥ በመሆን አገልግለዋል።

%d bloggers like this: