Tag Archives: Africa

የ28ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔና አዳዲስ ክስተቶች

–  ኢትዮጵያ ከግብፅና ከደቡብ ሱዳን ጋር ያደረገችው ቆይታ
–  ለኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር የተጠበቁት ዕጩ አለመመረጥ
–  የሞሮኮ ከ33 ዓመታት በኋላ ወደ ኅብረቱ መመለስ
–  ዶ/ር ድላሚኒ ዙማ ለደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንትነት መወዳደር

au-2017

የአፍሪካ ኅብረት 28ኛው የመሪዎች ጉባዔ ከሰኞ ጥር 22 ቀን ጀምሮ ለሦስት ቀናት በአዲስ አበባ ሲከናወን፣ ከወትሮ ለየት ያሉ አዳዲስ ክስተቶች ታይተውበታል፡፡ ዋና ዋና ከተባሉት ክስተቶች መካከል ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ፣ ለጉባዔው አዲስ አበባ ከተገኙት የግብፅ ፕሬዚዳንት አቡዱልፈታህ አልሲሲና ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ከወትሮው ለየት ባለ ሁኔታ መወያየታቸው አንዱ ነው፡፡

ለአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት ይመረጣሉ ተብሎ ትልቅ ተስፋ የተጣለባቸው የኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር አሚና መሐመድ ወድቀው፣ የቻድ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሙሳ ፋቂ መሐማት መመረጣቸው ሁለተኛው ክስተት ነው፡፡ ሦስተኛው ሞሮኮ እ.ኤ.አ. በ1984 ሯሳን ከቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አግልላ ከቆየች ከ33 ዓመታት በኋላ መመለሷ ነው፡፡ አራተኛው ክስተት የኅብረቱን ኮሚሽን ሊቀመንበርነት የሚያስረክቡት ዶ/ር ንኮሳዛና ድላሚኒ ዙማ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ተወዳዳሪ ይሆናሉ መባሉ ነው፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ ካለፈው ዓመት ጀምሮ በተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ቁጣ ሳቢያ በተከሰተው ቀውስ ከጀርባ የግብፅ ተቋማት እጅ እንዳለበት በመንግሥት ከተገለጸ በኋላ፣ በሁለቱ አገሮች መካከል የነበረው ግንኙነት የበለጠ ውጥረት ውስጥ ገብቶ ነበር፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት የግብፅ መንግሥትን በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ መጠየቁ ለተፈጠረው ውጥረት በምክንያትነት ተወስቷል፡፡

በ28ኛው የኅብረቱ የመሪዎች ጉባዔ ላይ የተገኙት የግብፅ ፕሬዚዳንት ከጠቅላይ  ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጋር የነበራቸው ቆይታ ፍሬያማ ነበር ተብሏል፡፡ በተለይ ሁለቱ መሪዎች በጎንዮሽ ባደረጉት ውይይት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መስማማታቸውን አስታውቀዋል፡፡ በኢትዮጵያና በግብፅ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት በማጠናከር መተማመን መፍጠር እንደሚያስፈልግ፣ የአካባቢውን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና የፀጥታ ትብብር በማጠናከር የሁለቱን አገሮች ወንድማማችነት የሚጎዳ ማንኛውንም ዓይነት ድርጊት መቆጣጠርና መገደብ፣ ታላቁ የህዳሴ ግድብን በተመለከተ የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ የጋራ ቴክኒክ ኮሚቴ አማካይነት በትብብር የመሥራት አስፈላጊነት፣ በሁለቱ አገሮችና በዓለም አቀፍ ጉዳዮች ላይ በመሪዎችና በተቋማት ደረጃ መረጃ በመለዋወጥ ተከታታይ ምክክሮች ማድረግ፣ የሕዝብ ለሕዝብ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱን የበለጠ ለማሳደግ፣ የመገናኛ ብዙኃንም ወሳኝ ሚና እንዲጫወቱ መደረግ እንዳለበት ስምምነት ላይ መድረሳቸው ታውቋል፡፡ ኢትዮጵያና ግብፅ ስትራቴጂካያዊ ግንኙነታቸውን የሚጎዱ ማናቸውንም ችግሮች በጋራ ለመከላከል መስማማታቸው ተገልጿል፡፡

የሁለቱ አገሮች መንግሥታት ውጥረት ውስጥ እንዳሉ በሚነገርበት በዚህ ወቅት፣ በዲፕሎማሲያዊ አቀራረብ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተነጋግረው መግባባት ላይ መድረሳቸው እንደ አዲስ ክስተት ታይቷል፡፡ በተለይ ደግሞ ሁለቱ መሪዎች በቋሚነት በተለያዩ ጊዜያት በሁለቱ አገሮች ጉብኝት ለማድረግ መስማማታቸው፣ ይህንንም ከወዲሁ ለመጀመር ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም በቅርቡ ግብፅን እንዲጎበኙ በፕሬዚዳንት አልሲሲ ተጋብዘዋል፡፡ በቅርቡ በሳዑዲ ዓረቢያ ከፍተኛ ባለሥልጣን የተመራ ልዑክ የታላቁን የህዳሴ ግድብ መጎብኘቱ በግብፅ መገናኛ ብዙኃን ከመጠን በላይ በመራገቡ፣ የሁለቱን አገሮች ግንኙነት ከድጡ ወደ ማጡ ያደርገዋል ተብሎ መሠጋቱ አይዘነጋም፡፡ አሁን ከሁለቱ መሪዎች የተሰማው የመግባባት መግለጫ ግን ሥጋቱን ረገብ ያደረገው መስሏል፡፡

በኢትዮጵያና በደቡብ ሱዳን መካከል የነበረውን መልካም ግንኙነት ያበላሸዋል የተባለው ሰሞንኛ ክስተት፣ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር በቅርቡ ወደ ካይሮ አቅንተው ፀረ ኢትዮጵያ ስምምነት አድርገው ተመልሰዋል የሚል ዜና መሰማቱ ነበር፡፡ ለኅብረቱ 28ኛ የመሪዎች ጉባዔ አዲስ አበባ የተገኙት ፕሬዚዳንት ኪር፣ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ጋር ከተወያዩ በኃላ የተናፈሰውን ወሬ አስተባብለዋል፡፡ ሁለቱን አገሮች በተመለከተ ማንኛውም ዓይነት ወሬ ቢናፈስ ተቀራርበው ለመነጋገር ምንም አያዳግታቸውም ካሉ በኋላ፣ ‹‹ግንኙነታችን ግን ተጠናክሮ ይቀጥላል፤›› ብለዋል፡፡ ‹‹በመሠረተ ቢስ ወሬ ምክንያት ግንኙነታችን እንዲጎዳ አንፈልግም፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ፕሬዚዳንት ኪር ኢትዮጵያን በቅርቡ እንዲጎበኙ የጋበዙ ሲሆን፣ ፕሬዚዳንቱም ግብዣውን በደስታ መቀበላቸውን ገልጸዋል፡፡ በንግድና ኢንቨስትመንት በመሠረተ ልማት፣ በሰላምና ፀጥታ ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመሥራት መስማማታቸውን ሁለቱ መሪዎች ይፋ አድርገዋል፡፡

ደቡብ አፍሪካዊቷ ዶ/ር ንኮሳዛና ድላሚኒ ዙማን በአዲስ ተመራጭ ለመተካት በተካሄደው ምርጫ ያልተጠበቀ ውጤት ተገኝቷል፡፡ ለአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት የተወዳደሩት ኬንያዊቷ ዶ/ር አሚና መሐመድ፣ ቦትስዋናዊቷ ፔሎኖሚ ቬንሰን ሞታይ፣ ቻዳዊው ሙሳ ፋቂ መሐማት፣ ኢኳቲሪያል ጊኒው አጋፒቶ ምባ ሞካይና ሴኔጋላዊው አብዱላዩ ባዚላይ ነበሩ፡፡ ከዕጩ ተወዳዳሪዎቹ መካከል ከፍተኛ ግምት የተሰጠው ለኬንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሚና መሐመድ ቢሆንም፣ ቻዳዊው ሙሳ ፋቂ መሐማት በድምፅ ብልጫ አሸንፈዋል፡፡ ዕጩዎችን ለመምረጥ ሰባት ዙር ምርጫ ተካሂዶ በመጨረሻው የቻድ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ላለፉት አራት ዓመታት የኅብረቱን ኮሚሽን በሊቀመንበርነት ከመሩት ዶ/ር ድላሚኒ ዙማ የኮሚሽን ሊቀመንበርነት ተረክበዋል፡፡ በዚህ ምርጫ የፈረንሣይኛ ተናጋሪ አገሮች ተፅዕኖ በማየሉ ምክንያት፣ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ከፍተኛ ልምድ የነበራቸው ኬንያዊቷ ዶ/ር አሚና ተሸንፈዋል፡፡ ለኬንያዊቷ መሸነፍ የተለያዩ ምክንያቶች ቢሰጡም፣ እሳቸውን ለማስመረጥ ከፍተኛ ጥረት ያደረጉት የኬንያ መንግሥት ባለሥልጣናት በሞሮኮና በሰሃራዊት ዓረብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ መካከል መዋለላቸው መንስዔ መሆኑን ለጉዳይ ቅርበት ያላቸው ዲፕሎማቶች መናገራቸው ተሰምቷል፡፡ ከሁለቱ ባላንጣ ወገኖች ለአሚና ይገባ የነበረው ድምፅ ወደ ቻዱ ዕጩ ሳይሄድ እንዳልቀረ ተገምቷል፡፡

የ56 ዓመቱ ሙሳ ፋቂ መሐማት በመጨረሻው ዙር 39 ድምፅ በማግኘት 54 አገሮች አባል የሆኑበትን የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበርነት ጨብጠዋል፡፡ ዶ/ር ድላሚኒ ዙማ ደግሞ አዲስ አበባን ከለቀቁ በኋላ በቀጣዩ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንትነት ምርጫ በመወዳደር የቀድሞ ባለቤታቸውን ጃኮብ ዙማ መንበር ለመቆናጠጥ እንዳሰቡ ተሰምቷል፡፡ ዶ/ር ድላሚኒ ዙማ በደቡብ አፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ ውስጥ ተሰሚነት ካላቸው ፖለቲከኞች መካከል በዋነኝነት የሚጠቀሱ ሲሆን፣ ከዚህ ቀደም የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ነበሩ፡፡ የኅብረቱን ኮሚሽን ሊቀመንበርነት ካስረከቡ በኋላ በኢትዮጵያ ለነበራቸው ቆይታ ለኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ከፍተኛ ምሥጋና አቅርበዋል፡፡ በተለይ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለኅብረቱ ጉባዔዎቹ መሳካት ላደረጓቸው ትብብሮች አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡

የዘንድሮው የመሪዎች ጉባዔ ሌላው ክስተት የሞሮኮ ጉዳይ ነው፡፡ ሞሮኮ ከ33 ዓመታት ቆይታ በኋላ ወደ አፍሪካ ኅብረት ለመመለስ ባደረገችው እንቅስቃሴ መጠነኛ እንቅፋት ቢገጥማትም በድል ተወጥታዋለች፡፡ ወደ ኅብረቱ አባልነት ለመመለስ በሞሮኮ ጥያቄ ያቀረበችው በሐምሌ 2008 ዓ.ም. በሩዋንዳ ኪጋሊ ተካሂዶ በነበረው የመሪዎች ጉባዔ ነው፡፡ በአዲስ አበባው የአሁኑ የመሪዎች ጉባዔ ሰኞ ጥር 22 ቀን 2009 ዓ.ም. ጥያቄውን የመረመረው በከፍተኛ ክርክር ታጅቦ ነበር፡፡ በተለይ ደቡብ አፍሪካና አልጄሪያ በሞሮኮ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ያሰሙባት ሲሆን፣ ከ53 አገሮች የ39 አገሮችን ድጋፍ አግኝታ ወደ አባልነቷ ተመልሳለች፡፡ አሥር አገሮች ድምፅ እንዳልሰጧት ታውቋል፡፡

ሞሮኮ እ.ኤ.አ. በ1984 በአዲስ አበባ በተካሄደው የቀድሞው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ውሳኔ አኩርፋ ነበር አባልነቷን የተወችው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የራሷ ግዛት እንደሆነች ለምታስባት ሰሃራዊት ዴሞክራቲክ ዓረብ ሪፐብሊክን የወቅቱ የአፍሪካ ድርጅት በአባልነት መቀበሉ ነበር፡፡ በዚህ ሳቢያ ለ33 ዓመታት ከመድረኩ የጠፋቸው ሞሮኮ ከዚህ ጉባዔ በፊት ባደረገችው ቅስቀሳና የማግባባት ዲፕሎማሲ ሥራ ፍላጎቷን አሳክታለች፡፡ በተለይ ባለፈው አንድ ዓመት ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች በንጉሧ መሐመድ ስድስተኛ የተደረጉ ጉብኝቶችና የኢንቨስትመንት ስምምነቶች የዚህ ጥረት ማሳያ ናቸው ተብሏል፡፡ ሞሮኮ ወደ አፍሪካ ኅብረት በመመለስ ተፅዕኖ ፈጣሪ አገር ለመሆን ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላት በስፋት ይነገራል፡፡

የአፍሪካ ኅብረት 28ኛው የመሪዎች ጉባዔ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውይይት ያደረገ ሲሆን፣ በተለይ ተሰናባቹ የኅብረቱ ሊቀመንበር የቻድ ፕሬዚዳንት ኢድሪስ ዴቢ ከአሁን በኋላ በአፍሪካ የሚደረጉ ምርጫዎች ለዜጎች ሥጋት መፍጠር አይኖርባቸውም ብለዋል፡፡ አዲሱ ተመራጭ ሊቀመንበር የጊኒ ፕሬዚዳንት አልፋ ኮንዴ ደግሞ የኅብረቱን ተደማጭነት ለመጨመርና ድምፁን ለማስተጋባት ጥረት እንደሚያደርጉ በንግግራቸው ገልጸው፣ አፍሪካ በአንድ ድምፅ መናገር እንጂ መከፋፈል እንደሌለባት ኮንዴ አሳስበዋል፡፡ በአባል አገሮች መካከል ትብብር እንዲጠናከር፣ ለ700 ሚሊዮን አፍሪካዊያን የኢነርጂ ልማት እንደሚያስፈልግና በወጣቱ ላይ ኢንቨስት ሊደረግ ይገባል ብለዋል፡፡
በዘንድሮው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ በክብር እንግድነት ከተገኙት መካከል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒ ጉተሬዝና የፍልስጤም ፕሬዚዳንት መሐመድ አባስ ተጠቃሽ ናቸው፡፡

ምንጭ፦ሪፖርትር

የጀርመኗ መራሒተ መንግሥት አንገላ መርከል መንግሥት ለተቃዋሚዎችና ለሲቪክ ማኅበራት ሰፊ የፖለቲካ ዕድል እንዲሰጥ ጠየቁ

ብርሃኑ ፈቃደ
– ፖለቲካዊ አለመግባባቶች በምክክር እንዲፈቱና ለወጣቶች የሥራ ዕድል መፍጠር የመንግሥት የቤት ሥራ መሆኑን አሳሰቡ

– ከተቃዋሚ ፓርቲዎችና ከሲቪክ ማኅበራት ጋር በአገሪቱ ጉዳይ ተነጋገሩ

angela-merkel-and-hailemariam-in-ethiopia

ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ሰኞ መስከረም 30 ቀን 2009 ዓ.ም. አዲስ አበባ የገቡት የጀርመኗ መራሒተ መንግሥት አንገላ መርከል፣ የኢትዮጵያ መንግሥት በፖለቲካ መስክ ለተቃዋሚዎችም ሆነ ለሲቪክ ማኅበራት ሰፊ ዕድል እንዲሰጥ ጠየቁ፡፡ የፖለቲካ አለመግባባቶች በውይይትና በምክክር እንዲፈቱም አሳሰቡ፡፡
መርከል ማክሰኞ ጥቅምት 1 ቀን 2009 ዓ.ም. በብሔራዊ ቤተ መንግሥት ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት እንደተናገሩት፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎች መደመጥ አለባቸው፡፡ ሲቻልም በተወካዮች ምክር ቤት ጭምር እንዲሳተፉ በማድረግ ድምፃቸው እንዲሰማ፣ ውይይትና ክርክር እንዲያደርጉ መንገዱን ማመቻቸት ይገባል፡፡

‹‹መነጋገር በጣም ጠቃሚ እንደሆነ ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር በተነጋገርንበት ወቅት ገልጫለሁ፡፡ የሲቪክ ተቋማትን ማሳተፍና በጠረጴዛው ዙሪያ እንዲገኙ መጋበዝ ይገባል፡፡ ጥሩ ትምህርት ቤቶች ሠርታችኋል፡፡ ከጎበኘኋቸው የአፍሪካ አገሮች ይልቅ እዚህ ብዙ ጥሩ ነገሮች ተሠርተዋል፡፡ ነገር ግን ለወጣቶች ሥራ መፍጠር ካልቻላችሁ የተሠራው ሁሉ ምንም ትርጉም አይኖረውም፤›› ያሉት መራሒተ መንግሥት መርከል፣ ‹‹ከአገሪቱ ግማሽ ያህሉ ሕዝብ በወጣቶች የተገነባ ነው፡፡ ወጣቶች ደግሞ ስሜታቸውን ባገኙት መንገድ መግለጽ ይፈልጋሉ፡፡ በማኅበራዊ ሚዲያዎችና በሌሎችም የሚሰማቸውን ለመግለጽ ይፈልጋሉ፡፡ ቅሬታውቸውን ሲገልጹም ትዕግሥት ላይኖራቸው ይችላል፤›› ብለዋል፡፡ በውይይትና በመነጋገር ጥሩ የመፍትሔ ሐሳቦች እንደሚመነጩ ሲመክሩም፣ በአገራቸው የፖለቲካ ሥርዓት በውይይትና በመነጋገር አብዛኞቹ ለውጦች እንደሚመነጩ አብራርተዋል፡፡ በዚህም አገር የቱንም ያህል አስቸጋሪና ከባድ ቢሆን በመነጋገር ችግሮችን መፍታት ይገባል ብለዋል፡፡

መንግሥት እንዲህ ያሉ አሳሳቢ ችግሮችን ለመፍታት ወጣቶችን በኢኮኖሚ መስክ በተገቢው መንገድ ተጠቃሚ እንደሆኑ ከማድረግ ባሻገር፣ ነፃ ሚዲያም ለአገሪቱ ዴሞክራሲያዊ ህልውና ወሳኝ እንደሆነ በመግለጽ መንግሥት ትኩረትም ቦታም እንዲሰጠው ጠይቀዋል፡፡

‹‹ዴሞክራሲያችን እንጭጭና ያልጠነከረ በመሆኑ በርካታ ችግሮች አሉበት፡፡ በየፈርጁ ያሉብንን ችግሮች ከማመን ተቆጥበን አናውቅም፤›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም፣ በአገሪቱ ይበልጥ የፖለቲካ ምኅዳሩን የሚያሰፉ ዕርምጃዎች እንደሚወሰዱ ከመራሒተ መንግሥት መርከል ጋር በመሆን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት አስታውቀዋል፡፡ አሳታፊና ለበርካቶች ዕድል የሚፈጥሩ፣ ለሲቪክ ማኅበራትም ቦታ የሚሰጡ ፖለቲካዊ ዕርምጃዎች እንደሚወሰዱ ጠቁመዋል፡፡ በምርጫ ሥርዓቱ ላይ ያሉትን ችግሮች ለመቅረፍ ማሻሻያዎች እንደሚደረጉም አስታውቀዋል፡፡ የጠቅላይ ሚኒስትሩም ሆነ የመርከል ማብራሪያዎች በአብዛኛው በፓርላማው በፕሬዚዳንቱ ከቀረበው የመንግሥት የሥራ ዕቅድ ጋር ተመሳሳይነት ያላቸው ነበሩ፡፡

ወጣቶች ሥራ በማጣት በዚህም ሳቢያ በተፈጠረባቸው መከፋትና ተስፋ መቁረጥ መንግሥት ላይ ተቃውሞ ማሰማታቸው ተገቢ እንደሆነ ያመኑት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ መንግሥት የተነሳበትን ተቃውሞ ትክክለኛ መሆኑን እንደሚቀበልም አስታውቀዋል፡፡ ከ15 ሚሊዮን ያላነሱ ወጣቶች በሥራ ፍለጋና በትምህርት ላይ እንደሚገኙ የጠቀሱት አቶ ኃይለ ማርያም፣ መንግሥት የሥራ ዕድሎችን በሚፈለገው መጠን ማሟላት እንዳልቻለ አምነዋል፡፡

ይሁንና ተቀባይነት ያላቸውን ተቃውሞች ተገን በማድረግ የተከሰቱት ብጥብጦችና ንብረት የማውደም ዕርምጃዎች ተቀባይነት የላቸውም ብለዋል፡፡ በርካታ ፋብሪካዎች፣ የውጭና የአገር ውስጥ ባለሀብቶች የገነቧቸው ኢንዱስትሪዎችና ሀብቶች መቃጠላቸውን በመግለጽ፣ እንዲህ ያሉትን ብጥብጦች ጉዳት ያስከተሉት ‹‹ከውጭ ጠላቶች›› ጋር የሚያብሩና ‹‹መሣሪያ የታጠቁ›› አካላት ናቸው በማለት በአገሪቱ የተቀጣጠለውን ፖለቲካዊ ቀውስ ለማብረድ መንግሥት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መደንገጉን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስረድተዋል፡፡ ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መደንገግ በኋላም በአገሪቱ አንድም ብጥብጥ እንዳልተከሰተ ጠቁመዋ፡፡

የተከሰቱትን ግጭቶችና ብጥብጦች ለመቆጣጠር የፀጥታ ኃይሎች የወሰዱት ዕርምጃ ተመጣጣኝነትን በሚመለከት ተጠይቀውም፣ ‹‹መሣሪያ ካነገቱ ታጣቂዎች ጋር መነጋገር የሚቻለው በመሣሪያ ብቻ ነው፤›› ያሉት አቶ ኃይለ ማርያም፣ ይሁንና የፀጥታ ኃይሎች የወሰዱት ዕርምጃ ተመጣጣኝ ስለመሆኑና ከሚፈቀድላቸው በላይ ኃይል ስለመጠቀማቸው ምርመራ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል፡፡

በተከሰተው ቀውስ ምክንያት የሟቾች ቁጥር ከ500 በላይ ስለመድረሱ የተጠየቁት አቶ ኃይለ ማርያም፣ ግጭቶቹን የሚያባብሱት የታጠቁ ሰዎች የሚያደርጉት እንቅስቃሴ የሟቾችን ቁጥር ከዚህም በላይ ሊያሻቅበው እንደሚችል ገልጸዋል፡፡ ጉዳዩንም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እያጣራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተከሰቱ ግጭቶች የሟቾች ቁጥር 190 ያህል እንደደረሰ፣ ከዚህም ቀደም በተከሰተው ግጭት በኦሮሚያ 178 ሰዎች፣ በአማራ ክልል ደግሞ 120 ሰዎች መሞታቸውን ኮሚሽኑ ይፋ እንዳደረገ በመጥቀስ ከጀርመን ጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

የተቀሰቀሱ ግጭቶችን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች የሚወስዷቸው ዕርምጃዎች ተመጣጣኝነት ላይ የሚነሱትን ክሶች መነሻ በማድረግም፣ መንግሥታቸው የጀርመንን ድጋፍ እንደሚሻና ሥልጠና እንዲሰጥም ጠይቀዋል፡፡ ብጥብጥን ለመቆጣጠርና ግጭቶች ደም አፋሳሽ ከመሆናቸው በፊት በሠለጠነ መንገድ ለመቆጣጠር የፀጥታ ኃይላቸውን ጀርመን እንድታሠለጥንላቸው ያቀረቡትን ጥያቄ የተቀበሉት መርከል፣ ድጋፍ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል፡፡

በሁለቱ መሪዎች በተሰጠው መግለጫ ወቅት መራሒተ መንግሥት መርከል ከተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ጋር ስለሚያደርጉት ውይይት አጀንዳ ምንም ዓይነት ማብራሪያ ሳይሰጡ ቀርተዋል፡፡ ሁለቱ መሪዎች በፀጥታና በደኅንነት ጉዳዮች፣ ስደተኞችን በተመለከቱ ተግባራትና በሌሎችም ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ በሁለትዮሽ ውይይታቸው ወቅት መነጋገራቸው ታውቋል፡፡

ጀርመን በኢትዮጵያ መንግሥት አሸባሪ ተብለው ከተፈረጁ የተቃዋሚ ቡድኖች መካከል እንደ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ያሉት የሚገኙባት እንደመሆኗ፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ሁለቱ መሪዎች ተነጋግረው እንደሆነ ሪፖርተር ጥያቄ ያቀረበላቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ተወልደ ሙሉጌታ፣ መሪዎቹ እንዲህ ባሉ ነጥቦች ላይ በተናጠል እንዳልተነጋገሩ ገልጸዋል፡፡

መራሒተ መንግሥት መርከል ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ያደረጉትን ውይይት አጠናቀው፣ በጀርመን ድጋፍ በአፍሪካ ኅብረት ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገነባውንና በቀድሞው የታንዛኒያ መሪ ጁሊየስ ኔሬሬ ስም የተሰየመውን የፀጥታና የደኅንነት መሥሪያ ቤት መርቀዋል፡፡ ስድስት ያህል የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችን አነጋግረው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበርና የውጭ ግንኙነት ኃላፊ ዶ/ር መረራ ጉዲና ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ከመራሒተ መንግሥት መርከል ጋር በአገሪቱ በተካሄዱ ተቃውሞዎችና የመንግሥት ምላሽ፣ በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ጉዳዮች ላይ ተነጋግረዋል፡፡
አገሪቱ በወሳኝና አሳሳቢ ጊዜ ላይ እንዳምትገኝ የገለጹት ዶ/ር መረራ መንግሥት እንደወትሮው ‹‹የተቀባባና የተሽሞነሞነ መግለጫውን›› ትቶ ትክክለኛ ለውጥ በአፋጣኝ እንዲያመጣ፣ የሚደረጉ ለውጦችም ወደፊት በታሳቢነት ሳይሆን አሁኑኑ ሊደረጉ እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡ አንገላ መርከል የአገሪቱ ተቃዋሚዎች፣ ሲቪክ ማኅበራትና ሌሎችም የሚገኙበትን ሁኔታ እንደሚገነዘቡና በሚደርስባቸው ጫናም ሐዘኔታ እንዳደረባቸው ዶ/ር መረራ ገልጸዋል፡፡

አንገላ መርከል ወደ አገራቸው ከተመለሱ በኋላ ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ ወደፊት እንደሚጠብቁ የገለጹት ዶ/ር መረራ፣ እሳቸውን ጨምሮ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ፣ የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን፣ የሴቶች ማኅበራት ተወካዮች በተገኙበት ከመራሒተ መንግሥት መርከል ጋር መነጋገራቸው በማውሳት ሪፖረተር ጋዜጣ ዘግቧል፡፡

Our World lost the Greatest Icon

 

Our World lost African the greatest   icon, in December 5, 2013. Who is Nelson Mandella has died yesterday midnight aged 95. He was prisoner at very cold island of Roben for 27 years. He struggle Racism the so called appartide in South Africa until to free in 1993. Then He was a president of new bright South Africa 1994-1999.mandella

Madella is a father of justice, peace, love and a good symbol for all over the world. And also he was a bridge for giveness. His work and role is not only for South Africa but also worldwide. His fruit will be above statue. Now who likes Mandella in Africa as well as the world? He is just gift of God Rather than his positive role for the people. Today our world especially Africa needs another Mandella for the nation otherwise they might be back as earlier. Really today our World lost its icon.

Opposition Political Parties Showing Reservation to the Ethiopian National Transitional Council (ENTC)

By Betre Yacob.

Ethiopian National Transitional Council (ENTC)Opposition political parties in Ethiopia are said to have been showing reservation to the Ethiopian National Transitional Council (ENTC), which has been working to overthrow the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) tyrannical regime that has been abusing, oppressing and exploiting its own people.

One ENTC leadership told this writer in an interview that although opposition political parties working in Ethiopia expressed their support to the Council (ENTC) — most of them have so far shown reservation to work together.

“When we formed ENTC, we had anticipated the joining of the other political groups under this umbrella. Hence the structure of the organization was designed in a bi-cameral way where organizations will have one wing with their voices and votes, and the public will be on the other end. To that effect, written invitations were sent to all the organized groups that are struggling for change in Ethiopia. Unfortunately, this did not work out as the opposition parties had some reservations even though they expressed support to the council”, he said.

The leadership, who said that the opposition political parties needed time to feel comfortable to rally behind the idea and join this new organization, said that —recognizing the problem —the general assembly of the council had passed a resolution in July 2012— to mobilize the public and, in the mean time, work closely with the other political parties and civic organizations.

“Accordingly, we are working together with other political parties in defining the roadmap and target around the alternative that ENTC believes yields success. Along with several other political parties and civic organizations, we have formed the “Joint Coordinating Committee of Ethiopian Democratic Forces” to help strengthen the cooperation. This committee is comprised of subcommittees and task forces which help develop the working relationships between the organizations”, he said.

The leadership also said that studying the past history of Ethiopian politics and assessing current political situations in Ethiopia, ENTC believed that along with the struggle for freedom— it was not too early to start thinking and planning of what was beyond.

“We believe that creation of an all-inclusive transitional government will help us have a framework and readiness that is required if the regime falls. In addition to that, having this institution beforehand will force the disparate political groups to work under one umbrella strengthening the struggle, hence two birds with one stone. Currently ENTC is calling for the formation of such an institution”, he explained.

Different political analysts argue that the Ethiopian National Transitional Council (ENTC) has been the first ever and wise development in the Ethiopian opposition politics. They are optimistic that the council will strengthen the Ethiopian struggle for freedom by bringing opposition political parties —which have been so fragmented.

The Ethiopian National Transitional Council (ENTC) was officially established in Dallas, USA on July 3, 2012, by Ethiopians from all over the world. It has been given the objective to overthrow the EPRDF regime and facilitate a peaceful transition of power to opposition political parties through participatory, fair, and democratic election.

Since its establishment, the council have done so many successful activities. For instance, it has managed to organize and mobilize Ethiopians that were part of the silent majority at the grassroots level in different local councils / chapters from all over the world including some in Africa. In addition, it has been doing meaningful works to influence western governments, which are the backbone of the tyrant regime in Ethiopia, to stand for the demand of the Ethiopian people.