Tag Archives: Ethio-Yemen

ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖት በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር ዋለ

በየመን ሰንዓ የሚገኘው ኢትዮጵያዊው ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖትበየመን ሁቲ አማጽያን ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ፡፡ ጋዜጠኛው እንዲታሰር ጠቁሞ ያስያዘው ለጊዜው ማንነቱ ያልታወቀ ኢትዮጵያዊ ጥቆማ ሲሆን፤ ለእስር ሲዳረግ የተገለፀለት ምክንያት በየመን የሚገኘውን መረጃ ከየመን ወደ ውጭ ታወጣለህ እና በተደረጂ ስደተኞች ስም ገንዘብ ትቀበላለህ የሚል እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡

ጋዜጠኛ ግሩም ተ/ኃይማኖት ከልጁ ጋር

ጋዜጠኛ ግሩም ተ/ኃይማኖት ከልጁ ጋር

ጋዜጠኛው በመካከለኛው ምስራቅ በተለይም በየመን ያሉ ወቅታዊ ጉዳዮችን ለህዝብ በማሳወቅ የሚታወቅ ሲሆን፤ በየመን ኢትዮጵያውን ስደተኞች የደረሰባቸውን ችግርናወቅታዊ ሁኔታም ለህዝብ በማድረስ ይታወቃል፡፡ ጋዜጠኛ ግሩም ከመታሰሩ በስተቀር እስካሁን ፍርድ ቤት ይቅረብ አይቅረብ የተገለፀ ነገር የለም፡፡ በአሁን ሰዓት በየመን የተረጋጋ መንግሥትም ሆነ ሁኔታ እንደሌለ ይታወቃል፡፡
ምንጭ፡፤ ነብዩ ሲራክ

24 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በየመን ባህር ሰጥመው ሞቱ

yemen1ባለፈው ሰኞ ታህሣሥ 20 ቀን 2007 ኣ.ም. በጀልባ ወደ የመን ሊገቡ የሞከሩ 24 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ሞቻ በምትባል የየመን ወደብ ከተማ አቅራቢያ በደረሰባቸው የጀልባ መስጠም አደጋ መሞታቸውን የየመን የሀገር ውስጥ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ እንደሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገለፃ ከሆነ በጀልቧ ተሳፍረው ከነበሩት ውስጥ በህይወት የተረፉ ስለመኖራቸውም ሆነ በአደጋው የሞቱትን በለመለየት ወደ ሀገራቸው ለመመለስ የተደረገ ጥረት አለመኖሩንም ሳይጠቁሙ አላለፉም፡፡

በቅርቡ ህዳር 28 ቅን 2007 ዓ.ም. በተመሳሳይ ሁኔታ በዚሁ በየመን የወደብ ከተማ በሆነችው ሞቻ አቅራቢያ 70 ኢትዮጵያውያን በሚጓዙበት ጀልባ በደረሰ አደጋ ህይወታቸው ማለፉ አይዘነጋም፡፡ ይሁን እንጂ እስካሁን ባህር አቋርጠው የምን ሊገቡ ሲሉ ህይወታቸው ላለፈው 94 ኢትዮጵያውያን ጉዳይ የኢትዮጵያ መንግስትም ሆነ በአቅራቢያው ያሉ የኢትዮጵያ ኤምባሲና ቆንፅላ ፅህፈት ቤት አምባሳደሮች ያሉት ነገር የለም፡፡ በየ ዓመቱ የህንድ ውቅያኖስን እና ቀይ ባህርን በጀልባ አቋርጠው ወደ የመን ሊገቡ የሚሞክሩ በርካታ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እየሞቱ ቢሆንም አደጋውን ለመቀነስ በኢትዮጵያ መንግስት በኩል የተደረገ ጥረት አለመኖሩን መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡

yemenአብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች የመንን ወደ ሌላ ሶስተኛ ሀገር ለመሸጋገር የሚጠቀሙባት በመሆኑ የስተኞች ጣቢያ እንደማይመዘገቡና እገዛም እንደማይደረግላቸው ተጠቁሟል፡፡ የመን ባህር አቋርጠው ከሚገቡ አብዛኞቹ ስደተኞች መካከል ጥቂቶች ብቻ በተለይም በፈረንጆቹ 2014 መጨረሻ የመን በሚገኘው በተባበሩት መንግስታት ከፍተኛው የስደተኞች ኮሚሽን እገዛ የተደረገላቸው 9,500 ኢትዮጵያውን እነደነበሩ የድርጅቱ መረጃ አመልክቷል፡፡

ከመንግስት በሚደርስባቸው የፖለቲካ ጫና እና በሀገሪቱ ከተከሰተው የኢኮኖሚ ችግር በተፈጠረው የኑሮ ውድነት የተነሳ የሚሰደዱ ኢትዮጵያውያን ዜጎች ቁጥር በየ ዓመት እየጨመረ መሄዱ ይታወቃል፡፡