Daily Archives: October 13th, 2013

በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የመጀመሪያው ማጣሪያ ጨዋታ በናይጄሪያ አሸናፊነት ተጠናቀቀ

 

bbbየኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን ለብራዚሉ ዓለም ዋንጫ 2014 ማጣሪያ በአዲስ አበባ ስታዲየም ዛሬ ጥቅምት 3 ቀን 2006 ዓ.ም. ከናይጄሪያ አቻው ጋር ባደረገው ጨዋታ 2 ለ 1 ተሸነፈ፡፡ በውጤቱም ኢትዮጵያ 1፡ 2 ናይጄሪያ በመሆን ተጠናቀቋል፡፡ በጨዋታውም የኢትዮጵያ ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ከፍተኛ ብልጭ የበላይነቱን ቢያረጋግጥም፤የኢትዮጵያ የፊት አጥቂ ሳላዲን ሰይድ ያገባት ጎል በዳኛው ተሽራለች፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በኢትዮጵያ እግር ኳስ ብሔራዊ ቡድን የበረኛው ክልል አካባቢ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ባለቀ ሰዓት ናይጄሪያ ልታሸንፍ ችላለች፡፡

ሁለቱም ቡድኖች ጎሉን ያስቆጠሩት በሁለተኛ አጋማሽ ሰዓት ሲሆን ለኢትዮጵያ በ56ኛው ደቂቃ የመሪነት ጎሉን በግራ አቅጣጫ ያስቆጠረው በኃይሉ አሰፋ (ቱሳ) ነው፡፡ ናይጄሪያ ደግሞ አንዱን በጨዋታ ስታገባ ሁለተኛውን ጎል ግን በተሰጣት ፍፁም ቅጣት ምት ነበር፡፡ በተለይ የአዲስ አበባ ስታዲየም በተመልካቾች የብሔራዊ ቡድኑን መለያ በመልበስ እጅግ አሸብርቀው ለሜዳው ደምቀት ሰጥተውታል፡፡ ቀጣዩ የደርሶ መልስ በናይጄሪያ በሚደረገው ጨዋታ ለዓለም ዋንጫ የመጨረሻው ውጤት ይታወቃል፡፡

በጎጃም ሶስት ወረዳዎች መንግስትን አስደነገጡ

በጎጃም ጎንቻ ሲሶ፣ ሁለት እጁ እነብሴ እና እነብሴ ሳር ምድር ወረዳ የሚገኙ ነዋሪዎች ሰሚ ያጣ ህዝብ በሚል
መንግስት ጥያቄዎቻችንን ባስቸኳይ ካልመለሰልን የራሳችንን እርምጃ እንወስዳለን ሲሉ አስጠነቀቁ፡፡ በተለይ
ነዋሪዎቹ ቢቸና፣ደጀን፣ሞጣ ባህርዳር ደረጃውን የጠበቀ መንገድ ለማስራት ከዚህ ቀደም የሞቱት ጠቅላይ ሚኒስትር
አቶ መለስ ዜናዊ ቃል ቢገቡም እስካሁን አልተሰራም፤ አሁን ደግሞ የመንገድ ግንባታው ተሰርዟል ተብለናል በሚል
መስከረም 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ማታ በወረዳዎቹ ከተሞች ላይ በራካታ መፈክሮች ያሉት ፖስተሮችን ለጥፈው
አድረዋል፡፡

በደል የወለደው ቁጭት በሚል ርዕስ ግብር ያለልማት ብዝበዛ ነው፣አንድ መንግስት መንገድ ለመስራት ስንት ዓመት
ይፈጅበታል፣ የሚሉ ይገኙበታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በርካት ጥያቄዎችንም ማንሳታቸው ታውቋል፡፡ይህንም የአካባቢው
አመራሮች መስከረም 29 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት አይተው በመደናገጥ ፖስተሮችን ያስቀደዱ ሲሆን፤ ህዝቡ አሁንም
ጥያቄያችን ካልተመለሰ በአካባቢያችን ያሉ ትምህርት ቤቶች፣ ሶቆችና አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ተዘግተው የተቃውሞ
ሰልፍ እንወጣለን ሲሉ በማስጠንቀቃቸው እስካሁንም በአካባቢው ውጥረቱ አይሏል፡፡ በዚህ ጉዳይ የአካባቢውን
ባለስልጣናት ለማናገር ጥረት ብናደርግም ለጊዜው አልተሳካም፡፡

%d bloggers like this: