አቃቤ ህግ እስማኤል ዳውድ ላይ ምስክሮቹን ሲያስደምጥ፤ የአቶ አለነ ማህፀንቱ የዋስትና መብት ጥያቄ ውድቅ ተደረገ

ኢዩኤል ፍስሃ ዳምጤ

የአንድነት ፓርቲ አባልና የሚሊየኖች ድምፅ ጋዜጣ አምደኛ የነበረው ወጣት እስማኤል ዳውድ በዛሬው እለት በአራዳ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት 5ኛ ወንጀል ችሎት ቀረበ፡፡

እስማኤል ዳውድ

እስማኤል ዳውድ

ወጣት እስማኤል፣ በፍርድ ቤት የቀረበው መዝገቡ የአቃቤ ህግ ምስክሮችን ለማድመጥ በዛሬው እለት በተያዘው ቀነ ቀጠሮ መሠረት ነው፡፡ አቃቤ ሀግ በእስማኤል ላይ እንዲመሰክሩ ካዘጋጃቸው 4 ምስክሮች መሃል ሁለቱን ማስደመጡን የተከሳሹ ጠበቃ አቶ ገበየሁ ይርዳው ገልፀዋል፡፡ አንደኛ ምስክር እስማኤል፣ ሰልፉ ላይ መገኘቱን ገልጾ ፈፀመ ስለተባለው ድርጊት እንደማያውቅ ማስረዳቱን ያወሱት አቶ ገበየሁ ሁለተኛው ምስክር በበኩሉ እስማኤል፣ መስቀል አደባባይ ተገኝቶ ድንጋይ ወርውሯል፣ እጁን በማነባበር ተቃውሞውን ገልጿል በማለት ምስክርነት መስጠቱን የተከሳሹ ጠበቃ አስረድተዋል፡፡ ጠበቃው የተለያዩ መስቀለኛ ጥያቄዎችን ለሁለቱም ምስክሮች ማቅረባቸውን አያይዘው ገልፀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ በዚሁ ጉዳይ ላይ ብይን ለመስጠት ተለዋጭ ቀጠሮ ለሐምሌ 14 ቀን 2007 ዓ.ም ሰጥቷል፡፡

 አለነ ማህፀንቱ

አለነ ማህፀንቱ

በተያያዘ ዜና የአንድነት ፓርቲ ማህበራዊ ጉዳዮች ኃላፊ የነበረው አቶ አለነ ማህፀንቱ፣ ከጠዋቱ 3፡00 ሰባራ ባቡር የሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት የዋስትናውን ጉዳይ በሚመለከት ብይን ለመስጠት ፍርድ ቤቱ ተሰይሞ እንደነበር የገለፁት አቶ ገበየሁ፣ ፍርድ ቤቱ የደምበኛቸውን ዋስትና ጥያቄ ውድቅ ማድረጉን ገልፀዋል፡፡ አቃቤ ህግ ‹‹ተከሳሹ ተመሳሳይ ወንጀል ሊፈፅም ስለሚችል›› የዋስትናው ጥያቄ ውድቅ እንዲደረግ ለፍርድ ቤቱ ያመለከት ሲሆን የተከሳሹ ጠበቃ በበኩላቸው ‹‹የአቃቤ ህግ መከራከሪያ በስር ፍርድ ቤት ያልተነሳ በመሆኑ፣ አቃቤ ህግም ካስያዘው ጭብጥ ውጪ የሆነ መከራከሪያ ነጥብ በማቅረቡ እንዲሁም ፍርድ ቤቱ የይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤት እንደመሆኑ መጠን አቃቤ ህግን ይህን መከራከሪያ ሊያቀርብ የሚችልበት የህግ አግባብ›› እንደሌለ ገልፀው የደምበኛቸው የዋስትና ጥያቄ ውድቅ መደረጉ ከህግ አንጻር ተቀባይነት እንደሌለውና በድጋሚ ይግባኝ እንደሚጠይቁ አስረድተዋል፡፡ አቶ አለነ ማህፀንቱ፣ ባቀረበው የክስ መቃወሚያ ላይ አቃቤ ህግ መልስ እንዲሰጥ እንዲሁም ምስክሮቹን እንዲያስደምጥ የአራዳ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ተለዋጭ ቀጠሮ ለሐምሌ 20 ቀን 2007 ዓ.ም መስጠቱ ይታወሳል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: