Monthly Archives: June, 2015

Obama’s visit diplomatic triumph or misplaced priority?

Kirubel's Blog

The upcoming official visit by United States President Barack Obama has sparked fierce debate between thrilled diplomats and concerned activists in the US.
Former diplomats say that Obama’s visit, a first for a sitting American president, is welcome news that recognizes the two countries’ ever-increasing ties. Meanwhile, human rights activists say the visit could be seen as an endorsement of the Ethiopian government’s alleged restriction of press and political freedoms.
The US State Department, in its annual Human Rights Report issued on June 25, grouped Ethiopia together with a small list of countries including China and Eritrea, accused of contravening human rights. Rights groups say that despite such reports, the US priorities its security cooperation with Ethiopia while turning a blind eye to rights abuse.
Ahistoric visit
Former presidents Jimmy Carter, Bill Clinton and George Bush have all visited Ethiopia, but only after leaving office. The 44th US President…

View original post 657 more words

“ለውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ” ከአንዳርጋቸው ጽጌ እህት

የግንቦት 7 ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ የሆኑት የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እህት ወ/ሮ ብዙአየሁ ፅጌ ለኢትዮጵያ ህዝብ መልዕክት አስተላልፈዋል! መልዕክታቸውም እነሆ፤…
“ለውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ” ከአንዳርጋቸው ጽጌ እህት (ወ/ሮ ብዙአየሁ ፅጌ)

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ

ይድረስ ለኢትዮጵያ ሕዝብ በኢትዮጵያ ውስጥም ሆነ ከኢትዮጵያ ውጭ እንዳሸዋ ተበትናችሁ የምትገኙ ወገኖቼ እኔ የተጎዳሁትን ያህል እናንተም የተጎዳችሁ መሆናችሁን በተለያዩ ሀገሮች በተደረጉ ሰልፎች ፤ የዉይይት መድረኮች ላይ በንዴት፤ በቁጭት እና በእልኸኝነት በእንባ ስትራጩ በመሃላችሁ ተገኝቼ ያየኻችሁ ሲሆን፤ ይህም በጣም በኢትዮጵያዊነቴ እንድኮራ አድርጎኛል። አንዳርጋቸውም በወያኔ የጨለማ እስር ቤት እየከፈለ ያለውን መከራና መስዋትነት የትም እንዳልወደቀና እንዳልቀረ በማሰብ እጽናናለሁ።
ዛሬ አንዳርጋቸው ፅጌ በመላው ኢትዮጵያዊያን ዘንድ “የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ“፤ “የኢትዮጵያ ልዩ አፈር“፤ “የኢትዮጵያ የበኩር ልጅ ” ወዘተ…. የሚሉ መገለጫዎችን እና መጠሪያዎችን የተጎናፅፈው ታናሽ ወንድሜ አንዳርጋቸው ፅጌ በእኔ እይታ ደግሞ የቤተሰባችን ልዩ ልጅ ነው።
አንዳርጋቸው የቤተሰባችን የመጀመረያ ወንድ ልጅ ስለነበረ ብርቅዬ መሆን የጀመረው የካቲት 1 ቀን 1947 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው በቀድሞው ቀዳማዊ ኃይለ ስላሴ ሆስፒታል ከእናታችን ከወ/ሮ አልታዬ ተሰማ ሮቢ እና ከአባታችን ከአቶ ፅጌ ሀብተማርያም ጨሜሳ ከተወለደ ቀን ጀምሮ ነው።
አንዳርጋቸው ለወላጅ አባታችን እና እናታችን፤ ለአያቶቻችን እና ለቅድመ አያቶቶቻችን ፤ ለእህቶቻን እና ለወንድሞቻችን ፤ ለዘመድ አዝማድ፤ ለአብሮ አደግ ጓደኞቹ በአጠቃላይ በአካባቢው ለነበሩት ዘመድ እና ወዳጅ ሁሉ ትልቅ እና ትንሽ ፤ ሐብታም እና ደሃ ፤ ወንድ እና ሴት ሳይል እንዲሁም በትምህርት ቤት አክብሮት እና ትህትና ሲያሳይ የኖረ ነው። የአንዳርጋቸው ሌላው ትልቁ እና አስገራሚው ስጦታዉ ወደር የማይገኝለት ትዕግስቱ ነው።
በቅርበት ከነበርው አካባቢው ሰፋ ባለው ክልል ወስጥም ቢሆን አንዳርጋቸው ስለ ሀገሩ እና ስለኢትዮጵያ ህዝብ ክብር እና ደህንነት የነበርው የተቆርቋሪነት ስሜት ገና የአንደኛ ደርጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ከነበረበት ዘመን የጀመረ ነበር። ለዚህም ነው ዛሬ “ለአንቺነው ነው ሀገሬ ” የሚል ግጥም ለገጠመላት የልጅነት ፍቅረኛው “ኢትዮጵያ” ሲል ልጆቹን ቤተሰቡን እና ጓደኞቹን ጥሎ የሀገርን ጥቅም እየነገደ የቡድን ምቾትን እና ሀብትን በማካበት ላይ የሚገኘውን የዘረኛ ባንዳ ወያኔ መንግስት በቁርጠኝነት ለመታገል የተነሳው።
አንዳርጋቸው አገሩን በበጎውም በክፉም ዘመን የሚያውቃት የ1960ቹ ትውልድ አካል በመሆኑ ነው፡ በዚህም በዚያም የተነሳ ይችን አገር ለማዳን የመጨርሻው ትውልድ እንደመሆኑ ይህንን አደራ ለመሸከም ታሪክ የጣለበትን ሀላፌነት ከዚህ የመነጨ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ስለሆነም አንዳርጋቸው ቁጭ ብሎ ከመፀፀት በላይ እራሱን ለዚች አገር የመስዋት ጠቦት አድርጎ ማቅረቡና ታፍኖ ያለው ነጻነት ናፋቂው የኢትዮጵያ ህዝብም ይህንን ተረድቶ በልቡ ማሀደር ላይ በክብር የጻፈው በመሆኑ ማንም ምድራዊ ሀይል ምንም አይነት ጥላሸት በመቀባት ሊቀይርው እንደማይችል ባለፉት 10 ወራት የታየው አብሮነት ትልቅ ምስክር ነው።
እነሆ! ይህ ጉዞው ዛሬ በወረበላው የየመን መንግስት ሹማምንት ተባባሪነት በጠላቶቹ እጅ እንዲወድቅ አድርጎታል። አንዳርጋቸው በጠላቶቹ እጅ ከወደቀ አስርኛ ወራቶች በላይ ቢቆጠሩም እስከ ዛሬ ድርስ ከአረመኔዉ ወያኔ አፋኞች ውጭ እና ከፈጣረው በስተቀር የት ስፍራ በምን ሁኔታ እንደሚገኝ የሚያውቅ ሰው የለም።
አንዳርጋቸው በዚህ አይነት አሰቃቂ ሁኔታ ውስጥ መዉደቁ ልቤ ውስጥ የተቀመጠ የእሳት ረመጥ ሆኖ በየቀኑ እያቃጠለኝ ቢገኝም፤ በሀገሬ ኢትዮጵያ ፤ ከአሜረካ እስከ ካንዳ ፤ከጃፓን እስክ ደቡብ ኮረያ፤ ከአዎሮፓ እስከ ደቡብ አፍሪካ፤ ከአውስትራሊያ እሰከ እስራኤል እንዲሁም በተለያዩ የአርብ አገራት ባለው የአለማችን ስፋት ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያን ወገኖቼ ” እኔም አንዳርጋቸው ፅጌ ነኝ !” ፡ “ሁላችንም አንዳርጋቸው ፅጌ ነን” ብለው በመነሳት የወያኔን እና የተባባሪዎቹን እብሪት፤ትዕቢት እና ህገወጥነትን ለማጋለጥ እያደረጉ ያለው ትግል ታላቅ መፅናናትን ይሰጠኛል።
አንዳርጋቸው የትናንሽ ልጆች አባት ከመሆኑ በላይ በተጨማሪ የ 85 ዓመት እድሜ ባለፅጋ የሆኑ አባታችን እዚያው ታፍኖ በተቀመጠበት ኢትዮጵያ ውስጥ ይኖራል። ከዚህ በተረፈ በጣም ከሚወዱት እና ከሚያፈቅሩት ከቅርብ ቤተሰቦቹ አልፎ አሁን ግን በአንዳርጋቸው የሀገር ፍቅር ፤ ለነጻነት ፤ ለፍትህ ፤ ለእኩልነት እና ለዴሞክራሲ የሚታገሉ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አባት እና እናቶች ፤ ወድም እና እህቶች ፤ ልጆች አፍርቶ ይገኛል።
ይችን አጭር ፅሁፍ ለመፃፍ ያነሳሳኝ ዋናው ምክንያት ለዚህ በሚሊዮን ለሚቆጠሩ ቤተሰቤ ልባዊ ምስጋናዬን በአንዳርጋቸው ስም ለማቅረብ ነው። በዚህ ክፉ ጊዜ የታየው ቆራጥነት በወያኔ ታፍኖ የተወሰደው ወንድማችንን ሙሉ ነጻነቱን እንዲሁም በወያኔ እስር ቤት እየማቀቁ ላሉት የነጻነት ታጋዮች እንዲሁም መብትና ነጻነቱን ተገፎ በሰፊዉ እስርቤት እየማቀቀ ላለው መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግሉን እንደሚቀጥል እና ከግቡ እንደሚያደርስ ባለ ሙሉ ተስፋ ነኝ።
በመጨርሻም ውድ ኢትዮጵያን ወገኖቼ አንዳርጋቸው እና እሱን የመሰሉ የነጻነት ታጋዮች እና የፖለቲካ መሬዎች ካለፍርድ በየስር ቤቱ በግፍ ታጉረው ላሉ ሁሉ እና ለቤተሰቦቻቸው ጭምር ፈጣሪ አምላካችን ብርታቱን ይስጥልኝ። የመጨርሻውም ፍርድ የሚመጣው ከሱ ከእግዛብሄር ስለሆነ ይችን የምንወዳትን የጋራ ሀገራችንን ለመታደግ በጋራ የጀመርነውን በጋራ እንውጣው ስል በወያኔ ጭለማ እስር ቤት ውስጥ በሚሰቃዩት ወገኖች ስም እማፀናለሁ።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!!
ወ/ሮ ብዙአየሁ ፅጌ

የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ወደ ሳሙኤል አወቀ መኖሪያ ቤት ለቅሶ እንዳይደርሱ ታገዱ

• ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም ለሌላ ለቅሶ በመሄድ ላይ የነበሩ ዜጎች ተደብድበው ተመልሰዋል

ተደብድቦ የተገደለው ወጣት ሳሙኤል አወቀ

ተደብድቦ የተገደለው ወጣት ሳሙኤል አወቀ

የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ሰኔ 8/2007 ዓ.ም ደብረማርቆስ ከተማ የተገደለው የሳሙኤል አወቀ ለቅሶ እንዳይደርሱ ታገዱ፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ዛሬ ሰኔ 13/2007 ዓ.ም በጠዋት ከአዲስ አበባ ተነስተው የሳሙኤል አወቀ ቤተሰቦች ወደሚገኙበት ምስራቅ ጎጃም ዞን ግንደወይን እያቀኑ በነበረበት ወቅት አባይ ድልድይ ላይ በፌደራል ፖሊስ ታፍነው ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ጎሃ ፂዮን ከተማ ውስጥ እስከ ምሽቱ 2 ተኩል ድረስ ታግተው ውለዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ወደ ለቅሶ እንዳይሄዱ ያገዱት ከአዲስ አበባ የሄዱና ከቦታው ተዘጋጅተው ሲጠብቁ የነበሩ የፌደራል ፖሊሶች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡
አመራሮቹና አባላቱ ለፖሊስ ቃል ሲሰጡ ከሳሙኤል አወቀ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት፣ በፓርቲው ውስጥ ያላቸውን ኃላፊነት፣ ሳሙኤልን ማን እንደገደለው የሚመለከቱ ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል፡፡ ለቅሶ እንዳይደርሱ ከተከለከሉትና ታተው የዋሉት
1. ኢ/ር ይልቃል ጌትነት/ የፓርቲው ሊቀመንበር
2. ይድነቃቸው ከበደ/ የፓርቲው የህግ ጉዳይ ኃላፊ
3. ወሮታው ዋሴ /የፓርቲው የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ
4. ሀብታሙ ደመቀ/ የኦዲትና ኢንስፔክሺን አባል
5. ጌታቸው ሺፈራው/ የነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ
6. ጋሻው መርሻ/ የብሄራዊ ምክር ቤት አባል
7. እምላሉ ፍስሃ/ የብሄራዊ ምክር ቤት አባል
8. ሜሮን አለማየሁ/ አባል
9. ጥላሁን አበጀ/ አባል
10. ጠና ይታየው/ አባል
11. እስጢፋኖስ በኩረጽዮን /አባል
12. ኃይለማሪያም ተክለ ጊዮርጊስ/ አባል
13. ጋሻነህ ላቀ/ አባል
14. ግርማ ቢተው አባልና
15. የመኪናው ሾፌር ናቸው

ከምሽቱ 2 ሰዓት ተኩል ከአዲስ አበባ በመንገድ ትራንስፖርት ሰራተኞችና ትራፊክ ፖሊሶች ህጋዊ መሆኑ ተረጋግጦ ያለፈው እንዲሁም ለአራት ቀን ከፓርቲው ጋር ውል የያዘው መኪና እንዳይንቀሳቀስ ተከልክሎ ከፍተኛ አመራሮቹና አባላቱ ከእስር ተለቀዋል፡፡ በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ ልዑካን ይዘዋቸው የነነበሩ ቁሳቁሶች ለምርመራ በሚል በፖሊስ ተይዘዋል፡፡
በተያያዘ ዜና ከአዲስ አበባ ተነስተው ምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወደ ሌላ ለቅሶ ሲሄዱ የነበሩ ዜጎች የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ከታፈኑ በኋላ ደጀን ላይ ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ ተፈፅሞባቸው በግዳጅ ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርገዋል፡፡ ተመልሰው ወደ ለቅሶው ቢሄዱ እስከ 10 ሺህ ብር ሊቀጡ እንደሚችሉ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ እነዚህ ዜጎች በተያዙበት ወቅት ሰማያዊ ፓርቲ ደብረማርቆስና ባህርዳር ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያደርግ እንደሆነ እንደተገለጸላቸው፤ እነሱም የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ ላይ ትገኛላችሁ ተብለው ተጠርጥረው እንደሆነ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ከምርጫው ጋር በተያያዘ 4ኛ ሌላ የመድረክ አባል ተገደሉ

ባለፈው ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. ምርጫን ተክትሎ የሚገደሉ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ነው፡፡ ባለፈው ሰኔ 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ከምሽቱ 2፡00 ሰኣት ላይ የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ግንባር (መድረክ) አመራር አካል የነበሩት አቶ ብርሃኑ ኤረቦ መገደላቸውን መድረክ አስታውቋል፡፡ አቶ ብርሃኑ በደቡብ ክልል ሀዲያ ዞን በሚገኘው ሶሮ ወረዳ በዳና ቶራ ቀበሌ የፓርቲው የኮሚቴ አመራር አባልና በምርጫው ቅስቀሳም ላይ ንቁ ተሳትፎ እንደነበራቸውም ፓርቲው በመግለጫው አስታውቋል፡፡

Medrek 2
በወቅቱ ግድያውን የፈፀሙት ብርሃኑ ደቦጭ እና ታዲዮስ ጡምቦ የተባሉ ፖሊሶች እንደሀኑ እና ከዛ በፊትም እነኚህ ፖሊሶች የመድረክ አመራሮች እና አባላቱን ሲያስፈራሩና ሲዝቱባቸው እንደነበርም ተጠቁሟል፡፡ በተለይ አቶ ብርሃኑ ኤረቦ በሁለቱ ፖሊሶች መኖሪያ ቤታቸው ደጅ ተይዘው ከተደበደቡና ከተገደሉ በኋላ አስከሬናቸው ባካባቢው ባለ ወንዝ ተጥሎ እንደተገኘ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ አቶ ብርሃኑ ኤረቦ የተገደሉበት ሶሮ ወረዳ በምርጫ ዋዜማ መምህር ጌታቸው የተባሉ የመድረክ ዕጩ በኢህአዴግ በደረሰባቸው ጫና እና አስተዳደራዊ በደል በወረዳው አስተዳደር ፊት ራሳቸውን አቃጥለው ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን፤ ወረዳው የኢህአዴግ ተወካይ እና የፌደራል ጉዳዮች ሚኒስቴር የሆኑት ዶ/ር ሽፈራው ተክለማርያም የተወዳደሩበት ወረዳ መሆኑ ታውቋል፡፡
መድረክ ከግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ይህ እስከተዘገበበት ድረስ አቶ ብርሃኑ ኤረቦን ጨምሮ የተገደሉት የክልል አመራሮቹ ቁጥር አራት የደረሰ ሲሆን፤ እነኚህም በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ሚዳ ቀኝ ወረዳ አቶ ጊዲሳ ጨመዳ፣ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን ቆራ ወረዳ አቶ ገቢ ጥቤ፣ ከትግራይ ክልል ምዕራብ ትግራይ ዞን ማይካድራ ከተማ አቶ ታደሰ አብርሃ እንደሚገኙበት ለማወቅ ተችሏል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በምርጫው ወቅት ከፍተኛ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ የነበሩ የመድረክ አባላትና ደጋፊዎች በተለይም በደቡብ፣ በኦሮሚያ እና በትግራይ በርካታ ሰዎች እንደታሰሩ፣በጥይት ተደብድበው እንደቆሰሉ እና ቤቶቻቸው እንደተቃጠለ ከፓርቲው የተገኘ መረጃ አመልክቷል፡፡ በተመሳሳይም በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረማርቆስ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ አመራርና የህዝብ ተወካዮች ዕጩ የነበረው ወጣት ሳሙኤል አወቀም ተደብድቦ መገደሉ ይታወቃል፡፡ መድረክ እና ሰማያዊ ፓርቲ አባሎቻቸው የተገደሉት በኢህአዴግ መሆኑን እንደሚያምኑ ገልፀዋል፡፡

በደብረማርቆስ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ እና በትግራይ ሑመራ የዓረና/መድረክ አባል ተገደሉ

በምስራቅ ጎጃም የሰማያዊ ፓርቲ ፀሐፊ እና ግንቦት 16 ቀን 2007 ዓ.ም. በተደረገው ምርጫ በደብረማርቆስ ከተማ የሰማያዊ ፓርቲ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ የነበረው ወጣት ሳሙኤል አወቀ ዓለም ሰኔ 8 ቀን 2007 ዓ.ም. ማታ ላይ በሁለት ግለሰቦች በተፈፀመበት ከፍተኛ ድብደባ ሆስፒታል ቢገባም ህይወቱ ሊትርፍ አልቻለም፡፡ ወጣቱ ቀደም ሲል ሚያዝያ 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በመንግሥት ደህንነቶችና ፖሊስ አባላት ድብደባ እንደደረሰበት ከነጉዳቱ ለህዝብ ይፋ አድርጎ ነበር፡፡

ወጣት ሳሙኤል አወቀ ሚያዝያ 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በተደበደበበት ወቅት

ወጣት ሳሙኤል አወቀ ሚያዝያ 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በተደበደበበት ወቅት

ከሚያዝያው ድብበደባ በኋላም በተደጋጋሚ የደብረማርቆስ ደህንነት አባላት፣ የከተማው የፖሊስ አዛዥን ጨምሮ የብአዴን/ኢህአዴግ ካድሬዎች ዛቻና ማስፈራሪያ ይፈፅሙበት እንደነበርና ከፖለቲካው እንቅስቃሴ እንዲወጣ አሊያም ሀገር ለቆ እንዲሄድ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ እንደሰጡት በራሱ የማኀበራዊ ሚዲያ ገፆቹ ላይ ይገልፅ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ ወጣቱ ይሰጠው የነበረውን ማስፈራሪያና ዛቻም እንደማይቀበልና ሰላማዊ የፖለቲካ ትግሉንም እንደሚቀጥል በተደጋጋሚ መግለፁን ከራሱ የማኀበራዊ ገፅ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በተለይ በግንቦት 24 ቀን 2007 ዓ.ም. የሚደርስበት ዛቻና ማስፈራሪያ ተጠናክሮ መቀጠሉን እና ከሐሰት ክስ እስከ ግድያ የሚደርስ እርምጃ ሊወስዱበት እንደታሰበ ራሱ በፌስ ቡክ ገፁ የሚከተለውን ገልፆ ነበር፡-
ውድ የደብረማርቆስ ከተማ ኗሪዎች ፤ ሰማያዊ ፓርቲን የመረጣችሁ ከ25,0000 በላይ መራጮች(ኮረጆውን) እርሱት እና በተጨማሪም በ31 ዩኒቨርስቲ የምትገኙ ከ14,000 በላይ ሰማያዊ ፓርቲን የመረጣችሁ ሌሎች ደጋፊዎች እና የኢሕአዴግ አባላትም የማያፍረው ብአዴን / ኢሕአዴግ ድምፅ መቀማቱ ሳያንስ በ21/08/2007 ዓም አፍነው ደብድበው ከሞት መትረፌ ቆጭቷቸው እሰር ቤት ለመወርወር ያለመከሰስ መብቴን እንኳን ተዳፍረው የሀሰት ክሰ እየፈጠሩ ነው!!!” በስልኬ እደተደወለም ያለፍላጎቴ ደሕንነት እያስገደደኝ ይገኛል!!!!! ተገደልሁም ታሠርሁም ፤ ታፈንኩም ነፃነት አይቀርም እና ለማሰረጃነት የደሕንነቶችን ስም፤ ፎቶግራፍ ፤ እና አድራሻ እንዲሁም በሐሠት ምሰክርነት እና ከሳሽነት የተደራጁ አካላት እና ዋና ተወካዮች የደብረማርቆስ ከተማ 04 ቀበሌ አመራሮች እና ፖሊስ ለታሪክ አሰመዘግባለሁ፡፡ ማንኛውም የምከፍለው ዋጋ ለሀገሬ እና ለነፃነት ነው ከታሠርሁም ሕሊናዬ አይታሰርም ከገደሉኝም ትግሌን አደራ በተለይ የኔ ትውልድ አደራ !!!!” አገራችን የወያኔ ዘረኞች ብቻ መፈንጫ መሆን የለባትም፡፡ ትግላችን የነፃነት ጉዟችን ጎርባጣ መድረሻችን ነፃነት ታሪካችን ዘላለማዊ ነው!!!! (ከሳሙኤል አወቀ ዓለም – የሰማያዊ ፓርቲ የደብረ ማርቆስ የሕዝብ ተወካዮች እጩ ተወዳዳሪ)

ወጣት ሳሙኤል አወቀ

ወጣት ሳሙኤል አወቀ

የ27 ዓመቱ የህግ ባለሙያና የሰማያዊ ፓርቲ አመራር የነበረው ወጣት ሳሙኤል የቀብር ስነ ስርዓት ሰኔ 9 ቀን 2007 ዓ.ም የትግል አጋሮቹ፣ ጓደኞቹና ዘመዶቹ በተገኙበት በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎንቻ ሲሶነሴ ወረዳ ሰቀላ ቀበሌ ግንደወይን አርባይቱ እንሰሳ ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ 11፡30 ላይ ተፈፅሟል፡፡ በዕለቱ ማታ ከቀብር መልስ ወደ ደብረማርቆስ ይመለሱ የነበሩ ወዳጆቹና ዘመዶቹ ታግተው እንደነበር የነገር ኢትዮጵያ ዘገባ አመልክቷል፡፡ የወጣት ሳሜኤል አወቀ አሟሟትን በተመለከተ እስካሁን ከመንግሥት በኩል የተሰጠ ምንም ዓይነት ምላሽ የለም፡፡
በተያያዘ ዜና የዓረና መድረክ አባል አቶ ታደሰ አብርሃ በትግራይ ክልል በቃፍታ ሑመራ ማይካድራ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ ሰኔ 9 ቀን 2007 ዓ.ም. ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት አካባቢ ሶስት ሰዎች አንቀዋቸው ሞተዋል ብለው ቢሄዱም ህይወታቸው እስከ ሌሊቱ 9፡15 ድረስ እንደነበርና ከዛ በኋላ ህይወታቸው እንዳለፈ የዓረና ፓርቲ መረጃ አመልክቷል፡፡ከዚህ በፊት አቶ ታደሰ ከዓረና/መድረክ ፓርቲ አባልነትና ተሳትፎ እንዲያቆሙ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያና ማስፈራሪያ ከደህነነቶችና ከህወሓት/ኢህአዴግ አመራሮች ይደርሳቸው እንደነበርና ለዚህም አማላጅ ይላክባቸው እንደነበር ተጠቁሟል፡፡

አቶ ታደሰ አብርሃ

አቶ ታደሰ አብርሃ

የ48 ዓመቱ አቶ ታደሰ አብርሃ በፖለቲካው ንቁ ተሳትፎ ያላቸው መሆኑን እና እስካሁን ይህ እስከተዘገበበት ድረስ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ታንቀው በተገደሉበት ወቅት በኪሳቸው የነበረው 300 ብር እንዳልተወሰደና ግድያው ፖለቲካዊ ይዘት እንዳለው ተጠቁሟል፡፡ የአቶ ታደሰ አብርሃን ገዳዮችና አሟሟታቸውን በተመለከተ አስከሬናቸው በሑመራ ሆስፒታል ምርመራ እንዲደረግ ቢሞከርም የአካባቢው ፖሊሶችና የኢህአዴግ አመራሮች መከልከላቸውም ታውቋል፡፡ በሶስት ቀናት ልዩነት የሰማያዊ እና የዐረና/መድረክ አመራሮች ተገድለዋል፡፡
ክምርጫ 2007 ዓ.ም. ጋር በተያያዘ በታህሳስ 2007 ዓ.ም. የዓረና/መድረክ አመራር የነበሩት ልጅዓለም ኻልዓዩ ማንነታቸው እስካሁን ባልታወቁ ሰዎች አዲስ አበባ ላይ ሲገደሉ በምርጫው ወቅት የኦፌኮ/መድረክ አባል በአርሲ ኮፈሌ ና በደቡብ እንዲሁ አንድ መገደላቸውን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ከምርጫ 2007 ዓ.ም. ጋር በተያያዘ የተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና አባላት ግድያ እስካሁን ባይቆምም፤እስካሁን በጉዳዩ ዙሪያ ከመንግሥት የተሰጠ ምንም ምላሽ የለም፡፡

%d bloggers like this: