የወልቃይት የአማራ ማንነት መብት ጥያቄ ተቃውሞ አድማሱን እያሰፋ ቀጥሏል

ትናንት ቅዳሜ ነሐሴ 7 ቀን 2008 ዓ.ም. በምስራቅ ጎጃም ደብረማርቆስ ከተማ እና ዛሬ እሁድ ነሐሴ 8 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰሜን ወሎ መቄት ከተማ ህዝባዊ የፀረ አገዛዝ ተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፎች ተካሂደዋል፡፡ ህዝቡም በነበረው የተቃውሞ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ወልቃይት ጠገዴ የአማራ ነው፣ የወልቃይት የአማራ ማንነት መብት ጥያቄ መንግሥት ምላሽ እንዲሰጥ፣ ወልቃይት ጠገዴ ወደነበረበት አማር መመለስ አለበት፣ የህወሓት የበላይነት ይቁም፣ የታሰሩ የፖለቲካና የህሊና እስረኞች ይፈቱ፣ መብትን መጠየቅ አሸባሪነት አይደለም፣በኦሮሚያ የሚፈሰው ደም የእኛም ደም ነው፣ ፍትህ ለወገኖቻችን፣ ጭቆና በቃን፣…..የሚሉ መፈክሮች በስፋት ተደምጠዋል፡፡

Debre-MarkosAnit-gov-protest

የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፉ እንዳይደረግ መንግሥት ቀደም ሲል በደህንነቱ እና የፀጥታ ኃይሉ አማካኝነት ከፍተኛ ጥበቃና ማስፈራሪያ ቢያደርግም፤ በተለይ የደብረ ማርቆስ እና አካባቢው ነዋሪ መነሻውን ከከከተማዋ የተለያየ አካባቢ በማድረግ መዳረሻው ወደ ንጉስ ተክለኃይማኖት አደባባይ ሲያደርግ ተስተውሏል፡፡ ይሁን እንጂ መንግሥት የተቃውሞ ሰልፉ መዳረሻ ጋ ከመድረሱ በፊት በህዝቡ ላይ በወሰደው ወታደረዊ ርምጃ 4 ሰዎችን በፅኑ መቁሰላቸው ታውቋል፡፡ መንግሥት ሰልፉን ለመበተን በወሰደው የኃይል ርምጃ የተበሳጩ ሰዎች በሁለት የፀጥታ ኃይሉ ላይ የአፀፋ ርምጃ መውሰዳቸውን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡

እሁድ ነሐሴ 8 ቀን በወሎ እና ሰሜን ሸዋ ከተሞች አጠቃላይ የአማራ ተጋድሎ ተቃውሞ ጥሪ መተላለፉን ተከትሎ በሰሜን ወሎ መቄት ከተማ ተመሳሳይ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ተደርጓል፡፡ በሌሎች ከተሞችም በተለይ በደሴ፣ ወልዲያ፣ ከሚሴ፣ ኮምቦልቻ፣ ላሊበላ፣ ደብረ ብርሃን፣ ሸዋ ሮቢትን ጨምሮ በሌሎችም የወሎና ሴመን ሸዋ ከተሞች ተመሳሳይ የተቃውሞ ሰልፍ ጥሪ የነበረ ቢሆንም ፤መንግሥት በወሰደው ጥብቅ ወታደራዊ ቁጥጥርና አፈና ምክንያት ህዝቡ መውጣት እንዳልቻለ ተጠቁሟል፡፡ ህዝባዊ ተቃውሞውችን ከተክትሎም በአማራ ክልል ባሉ የተለያዩ ከተሞች በርካታ ወጣቶች ከቤታቸውና ከስራ ገበታቸው ላይ እየታፈኑ በመታሰር ላይ መሆናቸውን የአዲስ ሚዲያ ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡

የተቃውሞ አድማሱን እያሰፋ የመጣው የአማራ ተጋድሎ ህዝባዊ ተቃውሞ ባለፈው ሐምሌ 5 ቀን 2008 ዓ.ም. መነሻውን በሰሜን ጎንደር ያደረገው የወልቃይት የአማራ ማንነት መብት ጥያቄ፣ ወደ ደቡብ ጎንደር ደብረ ታቦር እና ጋይንት ከዚያም ወደ ምዕራብ ጎጃምና የአማራ ክልል መዲና ወደሆነችው ባህርዳር ከተማ መደረጉ አይዘነጋም፡፡ ዘጠነኛ ወሩን ያስቆጠረው የኦሮሚያም ህዝባዊ የፀረ አገዛዝ ተቃውሞ በተለያዩ የክልሉ ከተሞች እንደቀጠለ ሲሆን፤ በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች እየጠወሰደ ባለው ወታደራዊ የኃይል ርምጃ የሚገደሉ፣ የሚቆስሉ እና የሚታሰሩ ዜጎች ቁጥርም እየጨመረ መሄዱ ታውቋል፡፡

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: