Monthly Archives: April, 2013

ህዝበ ሙስሊሙ “313 ሚሊዮን ብር ለልማት” በሚል ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ አደረገ

ብስራት ወ/ሚካኤል

ህዝበ ሙስሊሙ አርብ ሚያዝያ 18 ቀን 2005 ዓ.ም በአንዋር መስጂድ “313 ሚሊዮን ብር ለልማት” የሚል
መፈክር እያስተጋባ ተቃውሞውን አሰማ፡፡ ለጁምዓ ስግደት የወጣው የሙስሊሙ ህብረተሰብ ከስግደት በኋላ “313
ሚሊዮን ብር ለልማት” የሚል መፈክር አሰምቶ በሰላም ወደ የቤቱ ተበትኗል፡፡

የዕለቱ መፈክር ምን ማለት ነው? ለምን አስፈለገ? ምን መልዕክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ ነው በማለት በሥፍራው
ለነበሩ አንድ የሙስሊየም ሃይማኖት ተከታይ ፍኖተ ነፃነት ጥያቄ አቅርቦ   “መንግስት አህባሽ የተባለ ባዕድ
አስተምሮ አስመጥቶ ለማስፋት 313 ሚሊዮን ብር በጀት ለመጅሊሱ መመደቡን የሚያሳይ ሰነድ አግኝተናል፡፡ ይህ
በጣም ያሳዝናል፡፡ መንግስት በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ አልገባም እያለ ይክዳል፡፡ በተግባር ግን በጀት መድቦ
ሙስሊሙን ህብረተሰብ ለማተራመስ ይሠራል፡፡ ወታደርና ደህንነት አሰልፎም የእምነት ነጻነታችንን አፍኗል፡፡
በነጻነት እንዳናመልክ የእምነት ሥፍራችንን ይዳፈራል፡፡ ስለዚህ ሃይማኖታችንን ለመበከል ሙስሊሙን ለመከፋፈል
የመደበውን በጀት ለልማት እንዲያውለው ለማሳሰብ ነው” በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡  አያይዘውም “ለልማት እያለ
ህዝብን ከማስጨነቅ በእጁ ያለውን ገንዘብ በመጀመሪያ ለልማት እንዲያውለው ለመጠየቅ መጥተነል” ሲሉ የተቃውሞ
ሰልፉን አላማ አስረድተዋል፡፡

ከሀሙስ ዕለት ጀምሮ በተለያዩ መስጂዶች ሁለት ገጽ ያለው በራሪ ወረቀት የተበተነ ሲሆን፤ “68ኛ የተቃውሞ
ሳምንት ድምጽ፤ ቁጥር 42” የሚለው ይኸው በራሪ ወረቀት ስድስት አብይ ርዕሶችን በመያዝ ይዘረዝራል፡፡ እነሱም
ሰላማዊነታችን ከሌሎች እምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ድጋፍ አስገኝቶልናል፣ ሰላማዊነታችን ዓለም አቀፍ ዲፖሎማሲያዊ
ድጋፍ አስገኝቶልናል፣ ሰላማዊነታችን ትግላችን ዕድሜና ክብር እንዲጎናፀፍ አስችሎናል፣ ሠላማዊ ትግል ለእርማት
ሁል ጊዜ ክፍት ነው፣ ሠላማዊነታችን ከአስከፊ እርምጃዎች እንድንጠበቅ ሰበብ ሆኖናል የሚልና ሠላማዊ ትግል
ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ማሰለፍ ይችላል የሚሉት ነጥቦች ናቸው፡፡
ህዝበ ሙስሊሙ አርብ ሚያዝያ 18 ቀን 2005 ዓ.ም በአንዋር መስጂድ “313 ሚሊዮን ብር ለልማት” የሚል
መፈክር እያስተጋባ ተቃውሞውን አሰማ፡፡ ለጁምዓ ስግደት የወጣው የሙስሊሙ ህብረተሰብ ከስግደት በኋላ “313
ሚሊዮን ብር ለልማት” የሚል መፈክር አሰምቶ በሰላም ወደ የቤቱ ተበትኗል፡፡

የዕለቱ መፈክር ምን ማለት ነው? ለምን አስፈለገ? ምን መልዕክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ ነው በማለት በሥፍራው
ለነበሩ አንድ የሙስሊየም ሃይማኖት ተከታይ ፍኖተ ነፃነት ጥያቄ አቅርቦ   “መንግስት አህባሽ የተባለ ባዕድ
አስተምሮ አስመጥቶ ለማስፋት 313 ሚሊዮን ብር በጀት ለመጅሊሱ መመደቡን የሚያሳይ ሰነድ አግኝተናል፡፡ ይህ
በጣም ያሳዝናል፡፡ መንግስት በሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ አልገባም እያለ ይክዳል፡፡ በተግባር ግን በጀት መድቦ
ሙስሊሙን ህብረተሰብ ለማተራመስ ይሠራል፡፡ ወታደርና ደህንነት አሰልፎም የእምነት ነጻነታችንን አፍኗል፡፡
በነጻነት እንዳናመልክ የእምነት ሥፍራችንን ይዳፈራል፡፡ ስለዚህ ሃይማኖታችንን ለመበከል ሙስሊሙን ለመከፋፈል
የመደበውን በጀት ለልማት እንዲያውለው ለማሳሰብ ነው” በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡  አያይዘውም “ለልማት እያለ
ህዝብን ከማስጨነቅ በእጁ ያለውን ገንዘብ በመጀመሪያ ለልማት እንዲያውለው ለመጠየቅ መጥተነል” ሲሉ የተቃውሞ
ሰልፉን አላማ አስረድተዋል፡፡

ከሀሙስ ዕለት ጀምሮ በተለያዩ መስጂዶች ሁለት ገጽ ያለው በራሪ ወረቀት የተበተነ ሲሆን፤ “68ኛ የተቃውሞ
ሳምንት ድምጽ፤ ቁጥር 42” የሚለው ይኸው በራሪ ወረቀት ስድስት አብይ ርዕሶችን በመያዝ ይዘረዝራል፡፡ እነሱም
ሰላማዊነታችን ከሌሎች እምነት ተከታይ ወንድሞቻችን ድጋፍ አስገኝቶልናል፣ ሰላማዊነታችን ዓለም አቀፍ ዲፖሎማሲያዊ
ድጋፍ አስገኝቶልናል፣ ሰላማዊነታችን ትግላችን ዕድሜና ክብር እንዲጎናፀፍ አስችሎናል፣ ሠላማዊ ትግል ለእርማት
ሁል ጊዜ ክፍት ነው፣ ሠላማዊነታችን ከአስከፊ እርምጃዎች እንድንጠበቅ ሰበብ ሆኖናል የሚልና ሠላማዊ ትግል
ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል ማሰለፍ ይችላል የሚሉት ነጥቦች ናቸው፡፡

ምንጭ ፡- ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ

አንድነት ፓርቲ በሀገር አቀፍና በዓለም አቀፍ ደረጃ ፔቲሽን ሊያስፈርም ነው

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በመላ ኢትዮጵያ የሚካሄደውን የዜጎች ማፈናቀል እንዲቆም፣ ተዘዋውሮ የመኖር ዋስትና እንዲረጋገጥ፣ የመስራትና ሀብት የማፍራት መብት እንዲከበር እንዲሁም በሀገሪቱ ያለውን ለከት ያጣ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብት ጥሰት በመቃወም የኢትዮጵያ ህዝብ የሚተባበርበትን ዘመቻ ጀመረ፡፡
ይህንን አስመልክቶ የህዝብ ግንኙነት ክፍል እንደገለፀው ይህንን ሀገራዊ ዘመቻ በበላይነት የሚመራው የፓርቲው የፖለቲካ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሲሆን ዕቅድ በመንደፍ ተግባራዊ ለማድረግ የተግባር ኮሚቴ አቋቁሟል፡፡
በዕቅዱም መሰረት ኢትዮጵያውያን ሁሉ ሀገራዊ ዋስትና እንዲኖራቸውና መብታቸውን ማስጠበቅ የሚችሉባቸውን ዕቅዶች አውጥቷል፡፡ በዚህም መሰረት በቅድሚያ ሀገራዊ ይዘት ያለውን ማፈናቀል ለመጨረሻ ጊዜ ለማስቆም፤ የተፈናቀሉትም ወደነበሩበት ስፍራ እንዲመለሱና ካሳ የሚገባቸውም ተገቢ ካሳ እንዲፈፀምላቸው፤ ወንጀለኞች ለፍርድ እንዲቀርቡ ለማድረግ ፔቲሽን በማስፈረም ወደሚመለከተው አካል ማስገባት ቀዳሚው ነው፡፡ በተጨማሪም በሀገራቀፍ ደረጃ ምሁራን የተሳተፉበት የፓናል ውይይት በማካሄድ ከሙህራኑ የመፍትሄ አቅጣጫ የሚጠበቅ ሲሆን በሀገራቸው ጉዳይ ተሳታፊ ማድረግ ሌላው ዓላማ እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡
ከዚህም ባሻገር ህዝቡ መብቱን ለማስከበር እንዲችል ህዝባዊ ውይይቶችና ሰላማዊ ሰልፎች የሚደረጉበትን ሁኔታ ለማመቻቸት በቁርጠኝነት እየሰራ መሆኑን ከህዝብ ግንኙነት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ምንጭ ፡- ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ

Imprisoned Ethiopian Journalist Wins the 2013 UNESCO-World Press Freedom Prize

By Betre YacobImprisoned-Ethiopian-journalist-Reeyot-Alemu-

Imprisoned Ethiopian journalist Reeyot Alemu has won the 2013 UNESCO-Guillermo Cano World Press Freedom Prize. She is given the prize in recognition of her “exceptional courage, resistance and commitment” to freedom of expression. According to UNESCO’s news report, she was recommended by an independent international jury of 12 most outstanding media professionals.

Reeyot Alemu is one of the very rare outspoken Ethiopian women journalists. She bravely fought falsehoods, brutality, and oppression in Ethiopia, with pen — a power of words. She is currently serving a five-year jail sentence in Kality, a notoriously brutal prison of the authoritarian regime in Ethiopia. She was charged with ‘terrorism offences’ on June 2012, under the vaguely worded and broad-reaching Anti-Terrorism law, passed by the regime in 2009.

According to the Committee to Protect Journalists (CPJ), all of the charges against Reeyot Alemu were only based on her journalistic activities–emails she had received from pro-opposition discussion groups and reports and photographs she had sent to opposition news sites.

Reeyot Alemu is among a number of journalists who have been prosecuted under the anti-terrorism law in Ethiopia. According to Amnesty International, only during 2011 and 2012, over 100 journalists and political activists were arrested and prosecuted on charges of terrorism and other offenses in the country, for exercising their rights to freedom of expression. The actions that were the basis for such charges and prosecutions included writing articles critical of the government, calling for peaceful protest, and reporting on peaceful protests.

A Woman Born to Stand for the Truth

Born in 1980, Reeyot Alemu studied in Addis Ababa, the capital of Ethiopia. She received her BA in English Language and Theatrical Art from Addis Ababa University in 2005. Willing to risk her freedom and peace of mind, she began writing articles for independent newspapers in 2009, as a freelance writer.

Reeyot Alemu joined the now-defunct most prominent weekly newspaper called Awramba Times in 2010, where she worked as a columnist and wrote critically about the social and political crisis of her country. In 2011, she worked, among other roles, as a columnist for the weekly independent paper Feteh, which was later shuttered by the regime.

In 2010, Reeyot Alemu was able to found her own publishing house and a monthly magazine called “Change” that covered a wide range of political and social issues. However, after operating for a while, both of them were subsequently closed.

On June 21, 2011, Reeyot Alemu was taken from the school she taught, and arrested in Ma-ekelawi, an interrogation center, where dis-speakable torture is a normal practice of police and security officials in attempts to elicit confessions before cases go to trial. It was without charge. Four days before her arrest, she had written a sharp critique against the regime’s illegitimate fundraising methods for a dam project, and had apparently compared the late Libyan dictator Muammar Gaddafi with Ethiopia’s then-Prime Minister Meles Zenawi, who ruled the country for 21 years with a rod of iron.

Judged a “terrorist” by the tyrannical regime’s court, Reeyot Alemu was sentenced to 18 years in prison in January 2012. An appeals court, however, subsequently reduced the sentence to five years and dropped some of the charges.

Reeyot Alemu was offered clemency if she agreed to testify against journalist colleagues, who were arrested with her and accused by the regime of abetting terrorist groups. She, however, refused to do so and was consequently sent to solitary confinement as a punishment.

According to different sources, since her imprisonment in June 2011, the health of Reeyot Alemu has deteriorated. Recently, she has underwent surgery to remove a tumor from her breast. Her families reported that after the surgery she was forced to return to jail with no recovery time, and two days later she was, therefore, bleeding.

In 2012, Reeyot Alemu was the recipient of the prestigious 2012 Courage in Journalism Award that recognizes courageous actions of journalists around the world. She was given the prize for her “refusal to self-censor in a place where that practice is standard, and her unwillingness to apologize for truth-telling, even though contrition could win her freedom.”

በሚዛን 2ኛ ደረጃ እና መሰናዶ ትምህርት ቤት ተዘጋ

 

በደቡብ ክልል በቤንች ማጂ ዞን በሚገኘው ሚዛን 2ኛ ደረጃ እና መሰናዶ ትምህርት ቤት ከሚያዚያ 10 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ መዘጋቱ  ታውቋል፡፡ እንደፍኖተ ነፃነት ምንጮች ገለፃ ከሆነ ከሚያዚያ 7 ቀን 2005ዓ.ም. ጀምሮ በትምህርት ቤቱ ተማሪዎችና አስተዳደር አካላት በተነሳ አለመግባባት ከፍተኛ እረብሻ በመፈጠሩ እንደሆነ ተገለፀ፡፡ ለረብሻው መንስኤው የትምህርት ቤቱ  ከአሜሪካ በተሰጠው የትምህርት ዕድል የ12ኛ ክፍል የመሰናዶ ተማሪዎች መካከል  በተደረገው ውድድር  ከሴቶች ተማሪ መድኃኒት ስታሸንፍ  ከወንዶች ደግሞ በጀመሪያ ተማሪ ጌታመሳይ ማሸነፉ ከተጠቆመ በኋዋላ በተደረገ የውጤት ማጣራት ሂደት ተማሪ ዮሐንስ ማለፉ ተጠቁሟል ፡፡ ይህንንም ተከትሎ በተለይ የውድድሩ አዘጋጅ ኮሚቴ በወንዶች ተማሪ ዮሐንስና ተማሪ ጌታመሳይ ውድድር  ላይ የውጤት አሰራር  ስህተት በመኖሩን  በተማሪዎችና  በትምህርት ቤቱ መምህራንና አስተዳደር አካላት መካከል  በተፈጠረ አለመግባባት መማር ማስተማሩ ሂደት መቋረጡ ተጠቁሟል፡፡ በመጨረሻም በተደረገው የውጤት ማጣራት መሰረት በውድድሩ ያለፈው ተማሪ ዮሐንስ መሆኑንም ምንጮቻችን አስታውሰዋል፡፡

ከረብሻው ጋር በተያያዘ ሚያዚያ 11 ቀን 2005ዓ.ም. በትምህርት ቤቱ አካባቢ ተኩስ መከፈቱና  በተፈጠረ ግጭትም 3 ተማሪዎች ቆስለው ወደህክምና ጣቢያ መወሰዳቸው ተገልፁዓል፡፡ ይህን ዜና  እስከዘገብንበት ድረስም ትምህርት ቤቱ በፌደራል ፖሊስ መከበቡ ተጠቁሟል፡፡ ይህንንም በሚመለከት የትምህርት ቤቱ ዋና ርዕሰ መምህር የሆኑት አቶ አብዱ ካሣ ስለጉዳዩ ስናነሳላቸው አሁን ስለማልችል ከ30 ደቂቃ በኋላ መልሳችሁ ደውሉ ካሉ በኋዋላ ሽልካቻን በመዝጋታቸው  ምላሻቸውን  ማካተት አልቻልንም፡፡ ምክትላቸው አቶ አበራ ጉልማንም ለማናገር ጥረት ብናደርግም ስልካቸውን ጆሯችን ላይ ዘግተዋል፡፡

 

 

የነ አቶ በቀለ ገርባ ይግባኝ ክስ ለሌላ ጊዜ ተቀጠረ

 

የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ(ኦፌኮ) ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር፣ የመድረክ ከፍተኛ አመራርና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ፣ የኦፌኮ አመራር አባል የሆኑት አቶ ኦልባና ሌሊሳን ጨምሮ ወጣት ወልቤካ ለሚ፣ አደም ቡላ፣ ደረጀ ከተማ፣አዲሱ ምክሬ፣ገልገሎ ጉፉ፣ መሐመድ መሉ እና ወይዘሪት ሐዋ ዋቆ  በፌደራሉ አቃቤ ህግ በሽብርተኝነት ክስ ተመስርቶባቸው በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ወንጀል ችሎት የጥፋተኝነት ውሳኔ የተወሰነባቸውን ክስ በመቃወም ይግባኝ ቢጠይቁም እስካሁን ውሳኔ አላገኙም፡፡ በዚህም ምክንያት ይግባኝ የጠየቁት ክስ 6 ኪሎ በሚገኘው በፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት  አቶ በቀለ ገርባ ለሚያዚያ 14 ቀን 2005ዓ.ም. የተቀጠረ ሲሆን የአቶ ኦልባና ሌሊሳ ደግሞ ለሚያዚያ 16 ቀን 2005ዓ.ም. ክርክር ለማድረግ ተቀጥሯል፡፡ በዚህ የክስ መዝገብ ያሉ ሌሎች ስድስት ተከሳሾች ይግባኝ ቢጠይቁም እስካሁን የተሰጠ ቀነ ቀጠሮ አለመኖሩ ታውቋል፡፡ አቶ በቀለ ገርባ ቀደም ሲል በከፍተኛው ፍርድ ቤት የተወሰነባቸው ቅጣት 8 ዓመት ሲሆን አቶ ኦልባና ሌሊሳ ደግሞ 13 ዓመት ፅኑ እስራት መሆኑ ይታወቃል፡፡

በተያያዘ ዜና በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ ወንጀል ችሎት በፌደራሉ አቃቤ ህግ በሽብርተኝነት ክስ ተጠርጥረው በተሸለ በከሺ  የክስ መዝገብ ክስ የተመሰረተባቸው አቶ ተሸለ በከሺ፣ሐሰን መሐመድ፣ አለማየሁ ጋሮምሳ፣ ልጅዓለም ታደሰ፣ ቶሎሳ በቾ እና ወጣት ሙላታ አብዲሳን ጨምሮ 69 ተከሳሾች  ሚያዚያ 11 ቀን 2005ዓ.ም. የመከላከያ ምስክር ለመስማት ቀነ ቀጠሮ የተሰጠ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ለሰኔ 27 ቀን 2005ዓ.ም. ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ በዚህ የክስ መዝገብ የኦፌኮ አባላትን ጨምሮ  የቀድሞ የፓርላማ አባል የሆኑት የተከበሩ አቶ ጉቱ ሙሊሳ ይገኙበታል፡፡  ተከሳሾቹ የፍርድ ውሳኔ ሳያገኙ ከሚያዚያ 19 ቀን 2003ዓ.ም. ጀምሮ በፍርድ ቤት እየተመላለሱ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡

%d bloggers like this: