ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖት በፀጥታ ኃይሎች ቁጥጥር ስር ዋለ
በየመን ሰንዓ የሚገኘው ኢትዮጵያዊው ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖትበየመን ሁቲ አማጽያን ቁጥጥር ስር መዋሉ ተገለፀ፡፡ ጋዜጠኛው እንዲታሰር ጠቁሞ ያስያዘው ለጊዜው ማንነቱ ያልታወቀ ኢትዮጵያዊ ጥቆማ ሲሆን፤ ለእስር ሲዳረግ የተገለፀለት ምክንያት በየመን የሚገኘውን መረጃ ከየመን ወደ ውጭ ታወጣለህ እና በተደረጂ ስደተኞች ስም ገንዘብ ትቀበላለህ የሚል እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡
ጋዜጠኛው በመካከለኛው ምስራቅ በተለይም በየመን ያሉ ወቅታዊ ጉዳዮችን ለህዝብ በማሳወቅ የሚታወቅ ሲሆን፤ በየመን ኢትዮጵያውን ስደተኞች የደረሰባቸውን ችግርናወቅታዊ ሁኔታም ለህዝብ በማድረስ ይታወቃል፡፡ ጋዜጠኛ ግሩም ከመታሰሩ በስተቀር እስካሁን ፍርድ ቤት ይቅረብ አይቅረብ የተገለፀ ነገር የለም፡፡ በአሁን ሰዓት በየመን የተረጋጋ መንግሥትም ሆነ ሁኔታ እንደሌለ ይታወቃል፡፡
ምንጭ፡፤ ነብዩ ሲራክ