እነ ኦሞት አግዋ ካቀረቡት አሰራ አንድ የከስ መቃወሚያ አስሩን ፍርደቤቱ ውድቅ አደረገው
ክሳቸው ከነሐሴ 29 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት አየታየ የሚገኛው የእነ ኦሞት አግዋ ሶስት ተከሳሾች ያሉበት(ኦሞት አጉዋ፣ አሽኔ አስቲን እና ጀማል ኡመር ) ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያ አቃቤህግ ከሰጠው ምላሽ ጋር መርምሮ ምላሽ ለመስጠት ለዛሬ ጥር 2 ቀን 2008 ዓ.ም የቀጠረው ፍርድ ቤቱ ተከሳሾች ያቀረቡትን የክስ መቃወሚያዎች ከአንዱ በሰተቀር ሁሉንም አለመቀበሉን እና ውድቅ ማድረጉን የመሃል ዳኛው ታረቀኝ አማረ በንባብ ለችሎቱ አሰምተዋል፡፡

እነ አቶ ኦሞት አግዋ አዲስ አበባ በሚገኘው የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ታስረው ሲቀርቡ
በፍርድ ቤቱ ከአንድ መቃወሚያ በሰተቀር መቃወሚያዎቹ ውድቅ እንዲሆኑ እና ተቀባይነት እንዳያገኙ ምክኒያት የሆነው አቃቤ ህግ በማስረጃ ማሰማት ሂደት ላይ በዝርዝር እንድንሰማቸው ያደረጋል የሚል ነው፡፡
ተከሳሾች ክሳችን በእያንዳዳችን በተናጠል ቀርቦብን ሳለ አቃቤ ህግ በጋራ የከሰሰን ክስ ተነጣጥሎ ለየብቻ እንድንከሰስ ይደረግ የሚለውን የተከሳሾች መቃወሚያ ፍርድ ቤቱ የወንጀል ህጉን አንቀፅ 211 ቁጥር 7/3 በመጥቀስ ወንጀሎቹ የተለያዩ ቢሆንም የጋምቤላ ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ጋሕነን) የጠራው ስብሰባ ላይ ኬንያ ፣ናይሮቢ ለመሳተፍ ሲሄዱ በቁጥጥር ስር የዋሉ መሆናቸውን ጠቅሶ ተከሳሾቹ በአንድ መዝገብ ሊከሰሱ ይችላሉ በማለት ፍርድ ቤቱ የተከሳሾቹን መቃወሚያ አልተቀበለም፡፡
ተከሳሾች አባል ሆነውበታል በሚል የተጠቀሰው የጋምቤላ ሕዝቦች ነፃነት ንቅናቄ (ጋሕነን) ቡድን ህልውና እንዳለው አቃቤ ህግ በክሱ እንዲያስርዳ በተቃውሞቸው የጠየቁት ተከሳሾች፣ ቡድኑ በፍርድ ቤትም ሽብርተኛ ተበሎ አለመሰየሙን ጠቅሰው ከክሱ ላይ እንዲሰረዘላቸው ላቀረቡት መቃወሚያ ፍርድቤቱ የቡድኑን ህልውና እና ዝርዝር ማሰረጃ በክሱ ሂደት የሚሰሙ ናቸው በማለት ተቃውሞውን አለተቀበለም፡፡
በኢሜል አና በስካይፒ የተለያዩ ግንኙነቶችን ፈጥረዋል ብሎ አቃቤ ህግ በክሱ ላይ ያሰቀመጠውን ተከሳሾች ከማን ጋር ግንኙነት እንዳደርጉ ሰላልጠቀሰ በክሱ ከማን ጋር ግንኙነት እንደነበራቸው በዝርዝር እንዲጠቀስ በክስ ተቃወሞው ላይ ያቀረቡትንም ተቃውሞ እንድሌሎቹ የክስ መቃወሚያዎች በተመሳሳይ ፍርድ ቤቱ የክሱ መሰረታዊ ስህተት አይደለም፣በማሰረጃ ማሰማት ሂደት ላይ እምንሰማቸው ዝርዝሮች ናቸው በማለት ተቃውሞውን ውድቅ አድርጓል፡፡
በመጨረሻም ተከሳሾች ካቀረቡት አስራ አንድ መቃወሚያዎች ፍርድቤቱ የተቀበለው በክሱ ላይ አንደኛ ተከሳሽ ኦሞት አግዋ አሰቀጠራቸው የተባሉት የፖሊስ አባላት ስም ዝርዝር በክሱ ተካቶ ይቅረብልን በለው ያቀርቡትን ተቃውሞ ሲሆን ፍርድቤቱ አቃቤህግ ለጥር 17 ቀን 2008 ዓ.ም. በክሱ ላይ የተጠቀሱትን የፖሊስ አባላት ስም ዝርዝር በክሱ አካቶ እንዲያቀርብ ትዕዛዝ ሰጥል፡፡
EHRP
ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ የይግባኙን ጉዳይ በተመለከተ ለሰበር ሰሚ ችሎት አቤቱታ አቀረበ
የቀድሞው የአውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በ2003ዓ.ም. ሰኔ ወር ላይ ከሌሎች 4 ሰዎች ጋር (ጋዜጠኛ ኤልያስ ክፍሌ፣ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ፣ አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሄር እና ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ) የፀረ ሽብርተኝነት ህጉን ተላልፈሃል ተብሎ ክስ ተመስርቶበት የነበረ ሲሆን፤በዚህም የ14 አመት የእስር ቅጣት እንደተወሰነበት የሚታወስ ነው።

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ
ቅጣቱ ከተላለፈበት በኋላ ጥፋተኛ መባሉን በመቃወም ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ ቢልም መዝገቡ በይቅርታ ጉዳይ እየታየ መሆኑ ተገልፆለት በወቅቱ ይግባኝ ማለት ሳይችል ቀርቷል። ከእርሱ ጋር የይቅርታ ጥያቄ ያቀረቡ የስዊድን ጋዜጠኞች እና በተመሳሳይ መዝገብ የምትገኘው ሂሩት ክፍሌ ከእስር የተለቀቁ ሲሆን፤ የጋዜጠኛ ውብሸት የይቅርታ ጉዳይ ግን እስካሁን ድረስ ተፈፃሚ አልሆነም።
በመሆኑም በቅርቡ በወንጀለኛ መቅጫ ስነስረዓት ህጉ አንቀፅ 191 ስር በተመለከተው መሰረት የይግባኝ ጊዜ ካለፈ በኋላ ይግባኝ ለማቅረብ ፈቃድ ለማግኘት የሚቀርብ ማመልከቻ በማስገባት ጠቅላይ ፍ/ቤት ይግባኙን አቅርቦ ነበር። የወንጀለኛ መቅጫ ስነስርአት ህጉ አንቀፅ 196 (1) እና (2)፤ የተፈረደባቸው ብዙ ሰዎች ሆነው አንዱ ብቻ ይግባኝ ያቀረበ እና የተጠቀመ [ከእርሱ ጋር አብራ የተከሰሰችው ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ ከጋዜጠኛ ውብሸት ጋር ተመሳሳይ የቀረበባት እነወዲሁም የስር ፍርድ ቤት 14 ዓመት ከፈረደባት በኋላ በይግባኝ ወደ 5 አመት እንደተቀነሰላት ይታወቃል።] እንደሆነ ሌሎቹም ይግባኝ እንዳሉ እንደሚቆጠር እንደሚደነግግ በመጥቀስ ነው ይግባኙን ያቀረበው። ይግባኙን የተመለከተው ይግባኝ ሰሚ ችሎት የይግባኙን አቤቱታ ሳይቀበለው ውድቅ አድርጎበታል። ጋዜጠኛ ውብሸትም ይግባኝ ሰሚ ችሎት መሰረታዊ የህግ ስህተት በመጣስ ይግባኙን እንዳልተቀበለው በመግለፅ ያቀረበው አቤቱታ ዛሬ ሰበር ሰሚ ችሎት ቀርቦ ነበር። ዳኞች ጉዳዩን መርምረው ብይኑን ሰኔ 12 ቀን 2009 ዓ ም ቀን እንደሚያደርሱ እና ውሳኔውን ከመዝገብ ቤት ከማግኘት እንደሚቻል ተናግረዋል።
ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በ2007 ዓ. ም. “የነፃነት ድምፆች” እና “ሞጋች እውነቶች” የተሰኙ መፅሐፍት ለንባብ ያበቃ ሲሆን በመጪው ሰኞ ሰኔ 12/2009 ቀን ከታሰረ 6ዓመት ይሞላዋል።
EHRP