አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ በርካታ የኦፌኮ/መድረክ አመራሮች ከእስር ተለቀቁ

በኦሮሚያ ክልል ከሰኞ የካቲት 5 እስከ 7 ቀን 2010 ዓ ም በመላው ኦሮሚያ ክልል የተጠራውን ከቤት ያለመውጣትና የንግድ እቀባ ተከትሎ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ /መድረክ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ፥ እና ሌሎች የፓርቲው አመራሮች በተለይም የፓርቲው ምክትል ዋና ፀሐፊ አቶ ደጀኔ ጣፋ፥ የወጣቶች ክንፍ ሥራ አሥፈፃሚ አባል አቶ አዲሱ ቡላላ እና የወጣቶች ክንፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ጉርሜሳ አያኖን ጨምሮ 7 የፖለቲካ እስረኞች ተለቀዋል። እነ አቶ በቀለ ገርባ የካቲት 6 ቀን 2010 ዓ ም ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር መለቀቃቸው ታውቋል።

Bekele_Adama Public speech.jpg
አቶ በቀለ ገርባ በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ህዝባዊ አቀባበል ላይ ንግግር ሲያደርጉ

እነ አቶ በቀለ ገርባ ከእስር መፈታታቸውን ተከትሎ በርካታ ደጋፊዎቻቸው ከአዲስ አበኣ ጀምሮ ከፍተኛ ህዝባዊ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በተለይም በመኖሪያ ከተሞቻቸው ህዝባዊ አቀባበሉ እስከምሽት እንደነበር ማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
Bekele Gerba_Adama
በአዳማ/ናዝሬት አቶ በቀለ ገርባ የተደረገ ህዝባዊ አቀባበል

አቶ በቀለ ገርባ ከእስር መፈታታቸውን ተከትሎ ረቡዕ የካቲት 7 ቀን 2010 ዓ. ም. አዳማ/ናዝሬት በሚገኘው አበበ ቢቂላ ስታዲየም በርካታ ህዝብ አቀባበል ያደረገላቸው ሲሆን፤ እርሳቸውም ለህዝቡ ንግግር አድርገዋል። አሁንም በርካታ የፖለቲካ እስረኞች በውህኒ ቤት እንደሚገኙና ሁሉም መፈታት እንዳለባቸው ያስታወሱት አቶ በቀለ፤ ከእስር እንዲፈቱ በመንግሥት ላይ ጫና በመፍጠር ድጋፍ ላደረገው ለመላው ህዝብ ምሥጋናችውን አቅርብዋል።

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out /  Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out /  Change )

Connecting to %s

%d bloggers like this: