Daily Archives: February 15th, 2018

ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የሥራ መልቀቂያ አስገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትር እቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2010 ዓ. ም. በፅህፈት ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥራ መልቀቂያቸውን በቅድሚያ በስልጣን ላይ ያለው የገዥው ፓርቲ አባል ለሆነውና ተወክለው ለመጡበት ለደኢህዴን እና ኢህአዴግ ከሊቅመንበርነት ለመልቀቅ ያስገቡት ጥያቄ ተቀባይነቱን ማግኘቱን አስታውቀዋል። ይህንንም ተከትሎ ከጠቅላይ ሚኒስትርነት ኃላፊነት ለመነሳት ለገዥው ኢህአዴግ ምክር ቤት ጥያቄ ማስገባታቸውንና ውሳኔያቸው ተቀባይነት አግኝቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲፀድቅላቸው እንደሚንሱ ይጠበቃል።
Hailemariam Desalegn
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ

ለረጅም ጊዜ በሥላጥን ላይ ቆይተው በሞት የተለዩት አቶ መለስ ዜናዊን በመተካት ከነሐሴ 2004 ዓ. ም. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ያሉት አቶ ኃይለማርያም፤ ዛሬ በፅህፈት ቤታቸው በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በሰጡት ይፋዊ የሥራ መልቀቂያ መግለጫ እንዳስታወቁት ከሆነ በእርሳቸው ምትክ በፓርላማው ሌላ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር እስኪሾም ድረስ ሥራቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቅዋል። የሥልጣን መልቀቃቸውም በሀገሪቱ ያለውን ችግር ለመፍታት የመፍትሄ አካል አድርገው እንዳሰቡትም አስታውቀዋል።

አቶ አንዱዓለም አራጌን ጨምሮ የፖለቲካ እስረኞች ተለቀቁ

ከመስከረም 3 ቀን 2004 ዓ ም ጀምሮ በእስር ላይ የነበሩት የቀድሞ የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ (አንድነት) ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር እና የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አንዱዓለም አራጌ ፥ የፓርቲያቸው አመራር አባላት የነበሩት አቶ ናትናኤል መኮንን፥ የቀድሞ የፓርላማ አባል አቶ አንዱዓለም አያሌው የካቲት 7 ቀን 2010 ዓ ም ከእስር ተለቅዋል።
Andualem Arage
አቶ አንዱዓለም አራጌ

በተመሳሳም የቀድሞ የጋምቤላ ፕሬዘዳንት የነበሩት አቶ ኦኬሎ አኳይ፥ የመብት ተሟጋቿ ወ/ሮ እማዋይሽ አለሙ፥ የኦፌኮ/መድረክ አመራር የነበሩት አቶ ኦልባና ሌሊሳ፥ የቀድሞ መኢአድ ፕሬዘዳንት አቶ ማሙሸት አማረ፥ የመኢዴፓ አመራር የነበሩት አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ (አበበ ቀስቶ)፥ የኢብአፓ ፕሬዘዳንት የነበሩት አቶ ዘሪሁን ገብረእግዚአብሔር፥ የቀድሞ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር የነበረው ወጣት ብርሃኑ ተክለያሬድ፥የመብት ተሟጋቿ ጫልቱ ታከለ እና ደርቤ ኢተና፤ የሙስሊሙ መፍትህ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትና የመብት ተሟጋቾች አህመዲን ጀበልና አህመድ ሙስጠፋ እና አርቲስት ሴና ሰለሞን ከእስር ተለቅዋል።

በተለይ አቶ አንዱዓለም አራጌ እና ወ/ሮ እማዋይሽ አለሙ ተይዘው ከታሰሩ ጀምሮ በተለያየ ክስ መዝገብ ዕድሜ ልክ እስር ተፈርዶባቸው እንደነበር ይታወቃል።

ከላይ የተጠቀሱትን ጨምሮ በተመሳሳይ ቀን ከ746 ያላንሱ የፖለቲካ እስረኞች እንደሚፈቱ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ለመግንግሥት መገናኛ ብዙኃን ማሳወቁ ይታወሳል። ይሁን እንጂ አሁንም በርካታ የፖለቲካ እስረኞች በተለያዩ የሀገሪቱ ወህኒ ቤቶች እንደሚገኙ መረጃዎች ይጠቁሟሉ።

የነ አቶ አንዱዓለም አራጌን መፈታት ተከትሎ በርካታ ህዝብ በአዲስ አበባ ቃሊቲ ወህኒ ቤት እና በየመሮሪያ ቤታቸው በመገኘት ደስታውን ሲገልፅና እና ድጋፉን ሲያደርግ ተስተውሏል። እነ አንዱዓለምም ለመላው ህዝብ ምሥጋናችውን አቅርበዋል።

አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ በርካታ የኦፌኮ/መድረክ አመራሮች ከእስር ተለቀቁ

በኦሮሚያ ክልል ከሰኞ የካቲት 5 እስከ 7 ቀን 2010 ዓ ም በመላው ኦሮሚያ ክልል የተጠራውን ከቤት ያለመውጣትና የንግድ እቀባ ተከትሎ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረንስ /መድረክ ተቀዳሚ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት አቶ በቀለ ገርባ፥ እና ሌሎች የፓርቲው አመራሮች በተለይም የፓርቲው ምክትል ዋና ፀሐፊ አቶ ደጀኔ ጣፋ፥ የወጣቶች ክንፍ ሥራ አሥፈፃሚ አባል አቶ አዲሱ ቡላላ እና የወጣቶች ክንፍ ምክትል ኃላፊ አቶ ጉርሜሳ አያኖን ጨምሮ 7 የፖለቲካ እስረኞች ተለቀዋል። እነ አቶ በቀለ ገርባ የካቲት 6 ቀን 2010 ዓ ም ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር መለቀቃቸው ታውቋል።

Bekele_Adama Public speech.jpg
አቶ በቀለ ገርባ በአዳማ አበበ ቢቂላ ስታዲየም ህዝባዊ አቀባበል ላይ ንግግር ሲያደርጉ

እነ አቶ በቀለ ገርባ ከእስር መፈታታቸውን ተከትሎ በርካታ ደጋፊዎቻቸው ከአዲስ አበኣ ጀምሮ ከፍተኛ ህዝባዊ አቀባበል የተደረገላቸው ሲሆን በተለይም በመኖሪያ ከተሞቻቸው ህዝባዊ አቀባበሉ እስከምሽት እንደነበር ማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
Bekele Gerba_Adama
በአዳማ/ናዝሬት አቶ በቀለ ገርባ የተደረገ ህዝባዊ አቀባበል

አቶ በቀለ ገርባ ከእስር መፈታታቸውን ተከትሎ ረቡዕ የካቲት 7 ቀን 2010 ዓ. ም. አዳማ/ናዝሬት በሚገኘው አበበ ቢቂላ ስታዲየም በርካታ ህዝብ አቀባበል ያደረገላቸው ሲሆን፤ እርሳቸውም ለህዝቡ ንግግር አድርገዋል። አሁንም በርካታ የፖለቲካ እስረኞች በውህኒ ቤት እንደሚገኙና ሁሉም መፈታት እንዳለባቸው ያስታወሱት አቶ በቀለ፤ ከእስር እንዲፈቱ በመንግሥት ላይ ጫና በመፍጠር ድጋፍ ላደረገው ለመላው ህዝብ ምሥጋናችውን አቅርብዋል።

ዶ/ር መረራ ጊዱናን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች ተፈቱ

በአውሮፓ ቤልጅየም በተደረገላቸው ግብዣ መሰረት በኢትዮጵያ ጉዳይ ውይይት አድርገው ሲአመለሱ ከአዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ታስረው የነበሩት ዶ።ር መረራ ጉዲና ከእስር ተለቀዋል። ዶ/ር መረራ የኦፌኮ /መድረክ ሊቀመንበር ሲሆኑ፤ በአቃቤ ህግ ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው በፍርድ ቤት እየታየ እንዳለ ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጎ ጥር 9 ቀን 2010 ዓ ም ከእስር ተለቀዋል።
Dr. Merera _Ambo .jpg
ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር ሲለቀቁ በአምቦ የተደረገላቸው ህዝባዊ አቀባበል ላይ

ዶ/ር መረራ ከእስር ሲለቀቁ በርካታ ቤተሰቦቻቸው፥ የትግል አጋሮቻቸውና ደጋፊዎቻቸው ደማቅ አቀባበል ያደርጉላቸው ሲሆን፤ በተለይም በቡራዩ መኖሪያ ቤታቸው፥ እና በትውልድ አካባቢያቸው አምቦ በርካታ ህዝብ በተገኘበት ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

Dr. Merera _Ambo 1
ዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር ሲለቀቁ በአምቦ የተደረገላቸው ህዝባዊ አቀባበል ላይ

ከዶ/ር መረራ ፥ የወለጋ ዩኒቨርስቲ መምህር ሩፋኤል ዲሳሳን ጨምሮ በደቡብ ክልል ኮንሶ እና ጌዲዮ ዞን የታሰሩ በርካታ የፖለቲካ እስረኞች መለቀቃችው ታውቋል።

ቀደም ሲል መንግሥት በተለይ በኦሮሚያ እና በአማራ ክልል እየተደረገ ያለውን ህዝባዊ አመፅና ጫና ተከትሎ የፖለቲካ እስረኞችን እንደሚፈታ ቃል መግባቱ ይታወሳል።

%d bloggers like this: