የእነ ኦሞት አግዋ ላይ ዛሬም የአቃቤ ህግ ምስክር ሳይሰማ ተቀጠረ
ከመጋቢት 2007 ዓ.ም ጀምሮ የዋስ መብት በፍርድቤት ተከልክለው በእስር የሚገኙት እነ ኦሞት አግዋ ሐምሌ 12 ቀን 2008 ዓ.ም. የህግ አማካሪና ጠበቃቸው አመሃ መኮንን በህመም ምክንያት ችሎት ባለመገኘታቸው መዘገቡ የአቃቤ ህግ ምስክር ለመስማት ብቻ ለዘጠነኛ ጊዜ ተቀጥሯል፡፡
አንደኛ ተከሳሽ ኦሞት አግዋ ጠበቃችን አመሃ መኮንን ታመው ሆስፒታል የተኙ ስለሆነ ያለእርሳቸው ውክልና ምስክር እንዳይሰማብን ፍርድቤቱ አጭር ቀጠሮ ይስጠን ሲሉ ሶስቱንም ተከሳሾች ወክለው ፍርድቤቱን ጠይቀዋል፡፡
በዕለቱ ችሎት አቃቤ ህግ አሉኝ ካላቸው ሰባት ምስክሮች መካከል ሶስቱ በችሎቱ ምስክርነታቸውን ለመስጠት ቀርበው ነበር፡፡
ከምዕራብ ሸዋ ባኮ ከተማ ለአቃቤ ህግ ምስክር ለመሆን የመጡት ቄስ ሽብሩ ኦጅራ በተደጋጋሚ መጥተው ሳይመሰክሩ ተመልሰውብኛል ስለዚህ እንዲመሰክሩ ይደረግልኝ ብሎ ለተከራከረው አቃቤህግ፣ ዳኛ ታረቀኝ አማረ የስነስርዓት ህጉ ተከሳሾች ያለጠበቃቸው ውክልና እንዲከራከሩ አይፈቅድም በሚል ጥያቄውን ውድቅ አድርገውታል፡፡
የአቃቤ ህግ ምስክር ቄስ ሽብሩ ከምዕራብ ሸዋ ባኮ ከተማ ለምስክርነት ለመጡበት የሁለት ቀን ትራንስፖርት እና አበል እንዲከፈላቸው እንዲሁም ዛሬ የቀረቡ ምስክሮች ያለምንም የፍርድቤት መጥሪያ ሌሎች ተጨማሪ የአቃቤህግ ምስክሮች በጠቅላላ በቀጣይ ቀጠሮ ነሐሴ 9 ቀን 2008 ዓ.ም እንዲቀርቡ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ወንጀል ክስ ቀርቦባቸው ክሳቸው ከነሐሴ 29 ቀን 2007 ዓ. ም ጀምሮ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት አየታየ የሚገኛው የእነ ኦሞት አግዋ ሶስት ተከሳሾች ያሉበት(ኦሞት አጉዋ፣ አሽኔ አስቲን እና ጀማል ኡመር ) የክስ መዘገብ ላይ አቃቤ ህግ ምስክሮችን ማሰማት የጀመረው መጋቢት 6 ቀን 2008 ዓ.ም ነው፡፡
ምንጭ፡- EHRP
77 ቢሊዮን ብር የሚያንቀሳቅሰው ስኳር ኮርፖሬሽን የገጠመው ፈተና
‹‹ለስኳር ኮርፖሬሽን መውደቅ ሜቴክ ትልቅ ድርሻ አለው› ‹‹የስኳር ኮርፖሬሽን የቀድሞ አመራሮች መጠየቅ አለባቸው››
የኮርፖሬሽኑ ከፍተኛ አመራሮች
በዮሐንስ አንበርብር
በ2003 ዓ.ም. በተካሄደው የመጀመርያ የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ትልቅ ትኩረት ከተሰጣቸው ሜጋ ፕሮጀክቶች መካከል የስኳር ልማት አንደኛው ነው፡፡ አገሪቱ ለስኳር ልማት ያላትን ምቹ ሁኔታ በመጠቀም አሥር ግዙፍና አዳዲስ የስኳር ፋብሪካዎችን በመገንባት በዓመት 4.07 ሚሊዮን በላይ ስኳር በማምረትና ለውጭ ገበያ በማቅረብ፣ በ2007 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ 1.2 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት በዕቅድ ተይዞ ነበር፡፡
ይሁን እንጂ ይህ ዕቅድ በጣም የተለጠጠ መሆኑ በስተመጨረሻ ሲታወቅ፣ ሰባት ፋብሪካዎችን በመጀመርያው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን ዕቅድ ማጠናቀቅ ተብሎ እንዲከለስ ተደርጓል፡፡
እነዚህ አዳዲስና ግዙፍ ፕሮጀክቶች በደቡብ ኦሞ ዞን የሚገነቡት ኩራዝ አንድ፣ ኩራዝ ሁለት፣ ኩራዝ ሦስት፣ በለስ አንድ፣ በለስ ሁለት፣ ከሰም፣ ወልቃይት፣ አርጆ፣ ደዴሳና ተንዳሆ ናቸው፡፡
መንግሥት ፕሮጀክቶቹን አጠናቆ ስኳር ለውጭ ገበያ በማቅረብ በሚገኝ የውጭ ምንዛሪ ዕዳ መክፈል እንደሚችል በማሳመን ለስኳር ፋብሪካዎቹ መገንቢያ ከተለያዩ አበዳሪዎች ሁለት ቢሊዮን ዶላር ተበድሯል፡፡ ከአገር ውስጥ ባንኮችም ከፍተኛ ብድር አግኝቷል፡፡ በአጠቃላይ የስኳር ልማቱን የሚመራው የኢትዮጵያ ስኳር ልማት ኮርፖሬሽን 77 ቢሊዮን ብር በላይ እያንቀሳቀሰ የሚገኝ ቢሆንም፣ አንድም ፋብሪካ እስካሁን ተጠናቆ ወደ ሥራ አልገባም፡፡ በሌሎች አገሮች አንድ ስኳር ፋብሪካን ለማጠናቀቅ ግፋ ቢል አንድ ዓመት የሚፈጅ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ስኳር ልማት ኮርፖሬሽን ግን አንድ ዓመት ከስድስት ወራት (18 ወራት) አንድ ስኳር ፋብሪካን ለማጠናቀቅ አቅዶ የውል ስምምነቶችን ቢያደርግም፣ አንድ ፋብሪካ ሥራ ሳይጀምር ስድስተኛ ዓመት ላይ ተደርሷል፡፡
የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን የሥራ ኃላፊዎች በ2008 የበጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለማቅረብ ባለፈው ሰኞ ግንቦት 1 ቀን 2008 ዓ.ም. ተገኝተዋል፡፡
የኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ከተሾሙ የወራት ዕድሜን ያስቆጠሩት አቶ እንዳወቅ አብቴና ሌሎች ምክትል ሥራ አስፈጻሚዎች ያቀረቡት ሪፖርት ‹‹ተስፋ በመቁረጥና እያመመን ነው፤›› ብለዋል፡፡
ከሰባት ዓመት በፊት ግንባታው የተጀመረው ተንዳሆ ስኳር ፋብሪካ በኅዳር ወር 2008 ዓ.ም. ስኳር ማምረት ቢጀምርም ጥራቱ የተጓደለ የእንፋሎት አቅርቦት፣ የፋብሪካውን ፊልተር በቆሻሻ በመዝጋቱና በተርባይን ላይ ጉዳት በማድረሱ እንዲቆም መደረጉን ገልጸዋል፡፡ ጥገና ከተደረገ በኋላ በአገሪቱ በተከሰተው ድርቅ ለፋብሪካውና ለመስኖ የሚሆን የውኃ አቅርቦት ችግር ወደ ምርት እንዳይገባ እንዳደረገው ጠቁመዋል፡፡
የተንዳሆ ቁጥር ሁለት ፋብሪካ ግንባታም ገና 27 በመቶ ላይ ይገኛል፡፡ ኩራዝ አንድ የተባለው ፋብሪካ ኮንትራት ውል የተገባው በ2003 ዓ.ም. ሲሆን፣ የውል ማሻሻያ ሰኔ 2004 ዓ.ም. ላይ እንደተደረገ አቶ እንዳወቅ አስረድተዋል፡፡
በዚህ መሠረት ግንባታውን የሚያከናውነው አገር በቀሉ የኢትዮጵያ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ፕሮጀክቱን በመጋቢት ወር 2005 ዓ.ም. አጠናቆ ማስረከብ ይጠበቅበት ነበር፡፡
ፕሮጀክቱ በመጋቢት ወር 2008 ዓ.ም. ላይ የደረሰበት ደረጃ 83 በመቶ ሲሆን፣ ሜቴክ ግን 97 በመቶ ክፍያ እንደተፈጸመለት አቶ እንዳወቅ ተናግረዋል፡፡ ኩራዝ ሁለት የተባለውን ፋብሪካ ለማስገንበት ውል የተፈረመው እ.ኤ.አ. በሐምሌ ወር 2014 ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 58 በመቶ መድረሱን ይጠቅሳሉ፡፡ በውሉ መሠረት በመጪው ሐምሌ ወር ፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የነበረበት ቢሆንም መዘግየቱን አስታውቀዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ኮንትራክተር የፕሮጀክቱ ማጠናቀቂያ ጊዜ እንዲራዘምለት ጠይቆ እስከ መጪው ኅዳር ወር እንዲያጠናቅቅ መመርያ እንደተሰጠው አብራርተዋል፡፡
ኩራዝ ሦስት ግንባታው የተጀመረው እ.ኤ.አ. በፌብሯሪ 2015 ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 25 በመቶ ደርሷል፡፡ ይህም ቢሆን መሆን ከነበረበት ወደ ኋላ የቀረ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ኩራዝ አምስት ስኳር ፋብሪካን ለማስጀመር ከቻይና ኩባንያ ጋር ውል የተፈጸመ ሲሆን፣ ወደ ሥራ ለመግባት ኩባንያው ዝግጅት ላይ መሆኑን አቶ እንዳወቅ ይገልጻሉ፡፡ በለስ አንድ ስኳር ፕሮጀክት ወደ ሥራ የገባው በየካቲት 2003 ዓ.ም. ነው፡፡ በሰኔ ወር 2004 ዓ.ም. የውል ማሻሻያ መደረጉንና በመጋቢት ወር 2005 ዓ.ም. ኮንትራክተሩ ሜቴክ አጠናቆ ማስረከብ የነበረበት ቢሆንም፣ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም በአሁኑ ወቅት ገና 60 በመቶ ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ ኮንትራክተሩ ግን 94 በመቶ የሚሆነውን ክፍያ መቀበሉን ገልጸዋል፡፡
በለስ ሦስት ፋብሪካን ለመገንባት ውል የተፈጸመው በ2003 ዓ.ም. ሲሆን፣ መጠናቀቅ የሚገባው በ2005 መጋቢት ላይ እንደነበረ ያስረዳሉ፡፡ ይሁን እንጂ ፕሮጀክቱ ገና 23 በመቶ ሲሆን፣ ኮንትራክተሩ ሜቴክ ግን 94 በመቶ ክፍያ እንደተከፈለው ያስረዳሉ፡፡
የከሰም ስኳር ፋብሪካ አፈጻጸም 96 በመቶ መድረሱን ነገር ግን ገና ሙሉ ለሙሉ ወደ ሥራ እንዳልገባ አክለዋል፡፡ ወልቃይት ስኳር ፋብሪካም ግንባታው እንዳልተጀመረና በቅርቡ ግንባታው እንደሚጀመር ገልጸዋል፡፡ ኮርፖሬሽኑ ፋብሪካዎቹን ገንብቶና ምርት ኤክስፖርት በማድረግ ዕዳውን የመክፈል ኃላፊነት የተሰጠው ቢሆንም፣ ኤክስፖርት ማድረግ ይቅርና የአገሪቱን የስኳር ፍላጎት ማሟላት አለመቻሉን ገልጸዋል፡፡
ግንባታዎቹን ለማከናወን 77 ቢሊዮን ብር የውጭና የአገር ውስጥ ብድር የተበደረ በመሆኑ፣ አንድም ፋብሪካ ወደ ምርት ባልገባበት በአሁኑ ወቅት 13 ቢሊዮን ብር ዕዳ ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ የመክፈል ኃላፊነት ከፊቱ ተጋርጧል፡፡
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ተስፋዬ ይገዙና የኮሚቴው አባላት የኮርፖሬሽኑ ችግር ምን እንደሆነ፣ ሥራው ባልተሠራበት ሁኔታ ከ90 በመቶ በላይ ገንዘብ ለምን እንደተከፈለ ማብራሪያ ጠይቀዋል፡፡
የኮርፖሬሽኑ የኢንቨስትመንትና ልማት ዘርፍ ምክትል ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብርሃም ደምሴ በሰጡት አስተያየት፣ የአሥሩም አዳዲስ ፋብሪካዎች ኮንትራት የተሰጠው ለአገር በቀሉ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) መሆኑን አስታውሰው፣ ኮርፖሬሽኑ ፋብሪካዎቹን መገንባት እንዳልቻለ ገልጸዋል፡፡ ይህ ቢሆንም የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን አመራሮች ከሜቴክ ጋር የነበራቸው ግንኙነት በቢዝነስ ኮንትራት ሕግ የማይመራ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
‹‹አሥሩም ፋብሪካዎች በዚህ ኮንትራክተር እንዲሠሩ ነበር የተወሰነው፡፡ በኋላ ላይ የመፈጸም አቅሙ እየታየ ፕሮጀክቶቹ እየተነጠቁ አሁን እጁ ላይ ሦስት ፋብሪካዎች ናቸው የቀሩት፤›› ብለዋል፡፡
ከዚህ ኮንትራክተር (ሜቴክ) ተነጥቀው ፋይናንስ ተገኝቶላቸው ወደ ሥራ ከገቡት መካከል ከሰም ሥራ ለመጀመር ዝግጅት ላይ ሲሆን፣ ሌሎቹ ደግሞ እስከ ኅዳር ወር 2008 ዓ.ም. ይደርሳሉ ብለዋል፡፡ በሜቴክ እጅ የሚገኙት ግን መቼ እንደሚጠናቀቁ እንኳን ለማወቅ አስቸጋሪ እንደሆነባቸውና ከድርጅቱ ጋር ልቅ የሆነው ግንኙነት በውል ያልታሰረ በመሆኑ ዕርምጃ እንኳን ለመውሰድ እንዳልተቻለ ተናግረዋል፡፡
ሜቴክ በእጁ የሚገኙትን ሦስት ፋብሪካዎች በተለይም ኩራዝ አንድ ፋብሪካን በመጋቢት ወር 2007 ዓ.ም. ለማጠናቀቅ ገንዘብ እንደሚያስፈልገው ገልጾ፣ በልዩ ሁኔታ ስኳር ኮርፖሬሽን የአገር ውስጥ ብድር እንዲያገኝ ተደርጎ ሊከፈለው መቻሉን አቶ አብርሃም አስረድተዋል፡፡
‹‹ይሁን እንጂ ይህ ፋብሪካ እስካሁን አልተጠናቀቀም፡፡ እኛ ግን ዕዳ የመክፈል አደጋ ከፊታችን ተጋርጧል፤›› ብለዋል፡፡ ፋብሪካዎቹ ባለመድረሳቸው ምክንያት አጠቃላይ የስኳር ኮርፖሬሽን ወጪ እየናረ መሆኑን የሚገልጹት የሥራ ኃላፊው፣ የሸንኮራ አገዳው ቢደርስም አገዳውን ከማስወገድ ሌላ አማራጭ አለመገኘቱን ገልጸዋል፡፡
‹‹ኩራዝ ላይ 870 ሔክታር አገዳ ለማስወገድ ተቃርበናል፡፡ 300 ሺሕ ሔክታር የሸንኮራ አገዳ በለስ ላይ አስወግደናል፡፡ ይህንን ለማስወገድ በሔክታር 50 ሺሕ ብር እያወጣን ነው፤›› በማለት በምሬት ተናግረዋል፡፡
‹‹በዚህ ኮንትራክተር ላይ እንደ ማንኛውም ኩባንያ ቅጣት መጣል እንደማንችል ሁላችሁም ታውቃላችሁ፡፡ የሚያስጠይቅ ነገር ካለ ባለቤቱ ተለይቶ መጠየቅ ያስፈልጋል፤›› ብለዋል፡፡
ሌላው የኮርፖሬሽኑ አመራርም የሜቴክ ችግር በመገንባት ላይ ባሉት ፋብሪካዎች ላይ ብቻ አለመሆኑን ይጠቅሳሉ፡፡ በማምረት ላይ ለሚገኙ ፋብሪካዎች መለዋወጫ የሚያቀርበው ሜቴክ መሆኑን በመጥቀስ፣ መለዋወጫ ባለማቅረቡ ምክንያት ፋብሪካዎች ለበርካታ ቀናት ምርት እንደማያመርቱ ገልጸዋል፡፡
‹‹የማይችሉትን ሁሉ እንችላለን እያሉ አገርን ዋጋ እያስከፈሉ ነው፡፡ ምክንያቱም ነባሮቹ ፋብሪካዎች ያለ ችግር ቢሠሩ ቢያንስ በውጭ ምንዛሪ ስኳር አናስገባም ነበር፤›› ብለዋል፡፡ መለዋወጫ ከሜቴክ የመግዛት ግዴታ ለአገሪቱ አዋጭ አለመሆኑን፣ ምክንያቱ ደግሞ ሜቴክ ራሱ ከውጭ ከሚገባው በላይ እየሸጠ መሆኑን ይጠቁማሉ፡፡ ‹‹ለምሳሌ ሮለር ከውጭ ስንገዛ ከ200 ሺሕ ብር አይበልጥም፡፡ ሜቴክ ግን 600 ሺሕ ብር ነው የሚሸጥልን፤›› ብለዋል፡፡
‹‹እንቢ ብለን እንኳን እንዳንታገል አመራሮች ያሸማቅቁናል፤›› በማለት ተናግረዋል፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ከሌሎች አካላት ጋር የተያያዙ ችግሮችን ለብቻ በሌላ መድረክ እንደሚያይ አስታውቆ አሁንም የኪራይ ሰብሳቢነት ችግር በኮርፖሬሽኑ ውስጥ መኖሩን በመጥቀስ ፋብሪካዎች ኦዲት እንዲደረጉ አዟል፡፡
ምንጭ፡ ሪፖርተር ጋዜጣ
የመሬት ቅርምት እና ውጤቱ
ብስራት ወልደሚካኤል
በኢትዮጵያ መንግሥት በተደጋጋሚ ባለ ሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግቢያለሁ ሲል ይሰማል፡፡ በተለይ 11 በመቶ በተደጋጋሚ ዓመታዊ የኢኮኖሚ ዕድገት አስመዝግቢያለሁ ፣የምግብ ዋስትናን አረጋግጫለሁ ካለ ሰነባብቷል፡፡ ነገር ግን ተጨባጭ እውነታዎች እንደሚያሳዩት ከሆነ የተባለ ባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ ዕድገት በመን እና እንዴት እንደመጣ፣ የት ማን ተጠቃሚ ሆነ የሚሉ ጥያቄወች ግን መልስ አይሰጥባቸውም፡፡
በዚህ ሁኔታ ዛሬ ላይ አስቸኳይ የምግብ ዕርዳታ የሚፈልጉ ዜጎች ቁጥር ከ15 ሚሊዮን ወደ 18 ሚሊዮን ማሻቀቡን ዓለም አቀፍ መረጃዎች እያመለከቱ ነው፡፡ በተለይ የተባበሩት መንግሥታት ዓለም አቀፍ ተራድዖ ድርጅት በኢትዮጵያ የተከሰተው ርሃብ ሀገሪቱ በታሪኳ አይታው በማታውቀው መልኩ ከፍተኛ ህዝብ መራቡን እና አፋጣኝ ምላሽ ከዓለም አቀፍ ለጋሽ ሀገሮችና ተቋማት ካልተሰጠ ችግሩ ከዚህም ሊከፋ እንደሚችል በተደጋጋሚ የተማፅኖ እና ማስጠንቀቂያ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ይህም በተከታታይ ዓመታት ባለ ሁለት አሀዝ የኢኮሚ ዕድገት አስመዝግባለች በተባለችው ሀገር ባለሁለት አሀዝ 15 ሚሊዮን ህዝብ አስቸኳይ የምግብ ርዳታ አስፈላጊ መሆኑ አለ6 የተባለውን የቁጥር ዕድገት ገቢራዊ ሳይሆን ምናባዊ ያደርገዋል፡፡
በተለይ ሟቹ አቶ መለስ በስልጣን ላይ በነበሩበት እስከ 2002 ዓ.ም. ድረስ ከፍተኛ የሆነ የሀገሪቱን ለም መሬት በሊዝ/በኪራይ ሒሳብ ለውጭ ባለሃብቶች እንዲተላለፍ አድርገዋል፡፡ ከተላለፈው መሬት በተጨማሪ ለግብር እና ኢንዱስትሪ አገልግሎት በሚል ሰፋፊ መሬቶች ከዜጎች ተነጥቀው በመንግሥት የመሬት ባንክ ስር እንዲሆኑ ተደርገው ነበር፡፡
ለሽያጭ የተዘጋጀውና የተሸጠው መሬት መጠን
የማኀበራዊና ተፈጥሮ ሃብት ተመራማሪ ደሳለኝ ራህመቶ 2003 ዓ.ም. (እ.አ.አ. 2011)ጥናት፤ ከ1996 ዓ.ም. እስከ 2002 ዓ.ም. ባለው ጊዜ ውስጥ አጠቃላይ ለባለሃብቶች የተዘጋጀው ሰፋፊ ለም መሬት 3, 870, 280 ሄክታር መሬት ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥ ለባለሃብቶች የተላለፈው/የተሰጠው መሬት በከፊል 1, 342, 370 ሄክታር መሬት ነው፡፡ ይህም በሄክታር በየዓመቱ ከ14 ብር እስከ 135 ብር ዋጋ ከ30-50 ዓመት በሚፈጅ ኪራይ ውል የተላለፈ መሬት ነው፡፡ በመንግሥት እጅ ለሽያጭ/ኪራይ የተዘጋጀው መሬትና ተላልፎ የተሰጠውን መሬት በክልሎች ምን ያህል እንደነበር ያለውን በከፊል እንመልከት፤
ትግራይ ክልል 51, 544 ሄክታር መሬት ተዘጋጅቶ በዓመት በሄክታር ከ30-40 ብር ዋጋ በመንግሥት ቢተመንም፤ በሊዝ የመሬት ኪራይ ለባለሃብት የተላለፈ መሬት የለም፡፡
አፋር ክልል 409, 678 ሄክታር መሬት ተዘጋጅቶ እስካሁን ዋጋው ባልታወቀ ሒሳብ ለባለሃብት በሊዝ የተላለፈው መሬት 54, 000 ሄክታር መሬት ነው፡፡
አማራ ክልል 420, 000 ሄክታር መሬት ለባለሃብት በሚል ተዘጋጅቶ በዓመት በሄክታር ከ14-79 ብር ዋጋ ተተምኖ ከተዘጋጀው መሬት ላይ ለባለሃብት የተላለፈው 121, 370 ሄክታር መሬት ነው፡፡
ኦሮሚያ ክልል 1, 057, 866 ሄክታር መሬት ተዘጋጅቶ በዓመት በሄክታር ከ70-135 ብር ዋጋ ተተምኖ ከተዘጋጀው መሬት ላይ 380 000 ሄክታር መሬት በሊዝ ተላልፏል፡፡
ደቡብ ክልል 348, 009 ሄክታር መሬት ተዘጋጅቶ በዓመት በሄክታር በዓመት በሄክታር ከ30-117 ብር ዋጋ ተተምኖ 60, 500 ሄክታር መሬት ለባለሃብት ተላልፏል፡፡
ጋምቤላ ክልል 829, 199 ሄክታር መሬት ተዘጋጅቶ በዓመት በሄክታር ከ20-30 ብር ዋጋ ተመን 535, 000 ሄክታር መሬት ለባለሃብት ተላልፏል፡፡
በቤኒሻንጉል ክልል 691, 984 ሄክታር መሬት ተዘጋጅቶ በዓመት በሄክታር ከ15-25 ብር ዋጋ ተመን 191, 500 ሄክታር መሬት ለባለሃብት ተላልፏል፡፡
ኦጋዴን (ሶማሌ) ክልል 26, 000 ሄክታር መሬት ተዘጋጅቶ በዓመት በሄክታር ከ16-65 ብር ቢተመንም በሊዝ ለባለሃብት የተላለፈ መሬት የለም፡፡
*ከላይ የተጠቀሰው መረጃ የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች (አብዛኞቹ የህወሓት ሰዎች ናቸው) ከ2,000 ሄክታር መሬት በታች በእያንዳንዱ ባለሃብት የተወሰደውን ፣ ለአበባ እርሻ ልማት በየከተሞች አቅራቢያና ገጠር ከገበሬዎች ተነጥቆ የተሰጠውን መሬት ፣ መንግሥት ለስኳር ፕሮጀክት በሚል የወሰደውን 335, 000 ሄክታር መሬት አያጠቃልልም፡፡ መሬቱን ከወሰዱ ባለሃብቶች/ኩባንያዎች መካከል በአፋር ክልል የተሰጠው የግብፅ ብሔራዊ ባንክ እና በኦሮሚያ ክልል ለጥራጥሬ ምርት ከተሰጠው የጅቡቲ መንግሥት በስተቀር እስካሁን ምርታማና ውጤታማ የሆኑ የሉም፡፡ የግብፅ መንግሥት በብሔራዊ ባንኩ አማካኝነት እና የጅቡቲ መንግሥት በቀጥታ የሀገሮቻቸውን የምግብ ፍጆታ ለመደጎም የሚጠቀሙበት እርሻ ሲሆን፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ግን የዜጎቹን የምግብ ፍጆታ ለመሸፈን እና የሀገሪቱን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በመንግሥት ተቋማትም ሆነ በባለሃብቶች በኩል አንዳችም የግብርና መሬት ጥቅም ላይ አላዋለም፡፡ ሰፋፊ ለም መሬት ለሀገር ውስጥና ለውጭ ባለሃብቶች የተሰጡትም ቢሆኑ ዋጋቸው እጅግ እርካሽ ከመሆኑ የተነሳ ከውጭ ምግብ ነክ ምርቶችን ወደሀገር ውስጥ ለማስገባት እንኳ የሚበቁ አይደለም፡፡
የአካባቢና ማኀበራዊ ተፅዕኖው
ሁሉም ባለሃብቶች ማለት ይቻላል መሬቶቹን በወሰዱበት አካባቢ የነበሩ ነዋሪዎችን ያለ በቂ ካሳና ምክክር ከማፈናቀላቸው በተጨማሪ ለዘመናት ሲንከባከቡት የነበሩ የተፈጥሮ ደኖች ሙሉ ለሙሉ ተመንጥረው ከጥቅም ውጭ ሆነዋል፡፡ ይሄም ምናልባት በ10 እና 20 ዓመታት ውስጥ ከማኀበራዊ ተፅዕኖ በተጨማሪ ተፈጥሮን በማዛባት የሀገሪቱ የአየር ንብረትና አካባቢ ላይ ትልቅ ተፅዕኖ እንደሚኖረው ይታመናል፡፡ የአካባቢና አየር ንብረት መዛባት ተፅዕኖ ደግሞ እንደ ድርቅ ያሉ ሌላ ተጨማሪ ችግር ይዘው ከመምጣታቸው በተጨማሪ፣ ድርቅን ተከትሎ ምናልባትም ከአሁኑ መላ ካልተዘየደ ሀገሪቱ በታሪኳ አይታ ማታውቀው ርሃብ ሊከሰት እንደሚችል ይጠበቃል፡፡
አስገራሚው ነገር የሀገር ውስጥ ባለሃብቶችም ሆኑ ከውጭ የመጡ ባለሃብቶች ፕሮጀክታቸውን ለማሳካት ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና ንግድ ባንክ ከፍተኛ ብድር ወስደው ያልመለሱና በዛው የጠፉ በርካቶች ሲሆኑ፤ ምንም ሳይሰሩበት/ላይሰሩበት የተፈጥሮ ደኖችን (በተለይ በሰሜን ምዕራብ፣ በምዕራብ እና በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ አካባቢ) መንጥረው ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ ከጥቅም ውጭ አድርገው መሄዳቸው ነው፡፡ ከዚህ ጋ በተያያዘ ሻምፖርጂየተባለ የህንድ ኩባንያ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 50 ሺህ ሄክታር ለም መሬት ለግብርና ልማት በሚል ወስዶ የነበረውን ደን መንጥሮና አቃጥሎ እስከ አዲስ አበባ ድረስ ከሰል ይሸጥ እንደነበርና ከዛም ጥሎ ወደሀገሩ ጠቅልሎ እንደሄደ ይነገራል፡፡ በአካባቢውም ከሰል ነጋዴ ባለሃብቶች በሚል ይተቻሉ፡፡ ይሄ ደግሞ ተጨማሪ ሌላ ጉዳት ነው፡፡ ይህ ምንግሥት እሰራዋለሁ ላለው ስኳር ፕሮጀክት (ከሰም፣ ደቡብ ኦሞ እና ወልቃይት ) እና ኢሉባቦር ለማዳበሪያ ፋብሪካ ለማቋቋም በሚል ሙሉ ለሙሉ ከጥቅም ውጭ ያደረጋቸውን ደኖች ሳይካትት ነው፡፡ የስኳር ፕሮጀክቶቹም ሆኑ የማዳበሪያ ፋብሪካዎቹ የተፈጥሮ ደኖችን ከማውደም እና የአካባቢውን ነዋሪዎቸ ከማፈናቀል ባለፈ እስካሁን የታየ ምንም አዎንታዊ ውጤት የለም፡፡
ከላይ የተጠቀሱ እና ለባለሃብቶች በሊዝ መልክ የተላለፉ መሬቶች ውጤታማ ሆነው ቢታዩ ኖሮ የመንግሥት ዓላማና ግብ የሀገሪቱን የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ላይ ሳይሆን የውጭ ምንዛሪ ላይ ትኩረት ያደረገ ነበር፡፡ ይህ የሚያሳየው ሀገሪቱ ላይ እየተተገበረ ያለው የተፈጥሮ ሃብት አጠቃቀም እና የኢኮኖሚ ፖሊሲው ምን ያህል የተሳሳተ እንደሆነ እና መንግሥት እስካሁንም የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ በስሩ ካሉ የመገናኛ ብዙኃን ከሚነገረው ወሬ በስተቀር በተግባር ይሄ ነው የሚባል ጅማሮም ሆነ ውጤት የለም፡፡
በተለይ ከመሬት ቅርምቱ ጋ በተያያዘ ሶስት ተጨማሪ ጉዳዮችን እናንሳ፡፡
መንግሥት ሰፋፊና ለም የሆኑ የሀገሪቱን መሬት እጅግ ዝቅተኛ በሆኑ ዋጋ ለግማሽ ምዕተ ዓመት ድረስ ለመስጠቱ በዋናነት የሚሰጠው ምክንያት ፤
– ለዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር/የስራ አጥ ቁጥር ለመቀነስ
– በግብርናው ዘርፍ የቴክኖሎጂ ሽግግር ለማምጣት
– የግብርና ምርትን በማሳደግ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪን ማስገኘት የሚል ነበር፡፡
ነገር ግን ከተጠቀሱት ምክንያቶች ስኬታማ የሆኑ የሉም፡፡ በአንፃሩ በማኀበረሰቡ እና በአካባቢው ላያ ያደረሱት ጉዳት ግን አለ፡፡ በመሬት ቅርምቱ ከደረሱ ጉዳቶች መካከል ጥቂቶቹ፡
ነዋሪዎችን ያለበቂ ካሳና ምክር አገልግሎት ማፈናቀል ይገኝበታል፡፡ ከዚህ ጋ በተያያዘ በዋነኛነት በጋምቤላና ደቡብ ኦሞ ከፍተኛውን ቁጥር ይይዛሉ፡፡
በጋምቤላ ወደ 225, 000 የአካባቢው ነዋሪዎች ያለበቂ ካሳና፣ ምክክርና ስምምነት ተፈናቅለዋል፡፡ ይህንም ተከትሎ ከ 8 ሺህ እስከ 10 ሺህ ተፈናቃዮች ሀገር ለቀው ወደ ጎረቤት ሀገሮች በተለይም ወደ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን እና ኬንያ ተሰደዋል፡፡ የመሬት መፈናቀሉን ከተቃወሙ ከክልሉ ነዋሪዎች መካከል ፤ ከመንግሥት በተለይም ከወቅቱ ጠቅላ ሚኒስትር በነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ቀጥተኛ ትዕዛዝ በተወሰደ ወታደራዊ የኃይል እርምጃ 424 የአኝዋክ ማኀበረሰብ አባላት በተመሳሳይ ቀን በጅምላ ተገድለዋል፡፡ በርካታ ሰዎችም በጋምቤላና አዲስ አበባ በሚገኙ ወህኒ ቤቶች ታስረዋል፡፡ ይህ ድርጊት የተፈፀመው በአብዛኛው በዛው በጋምቤላ ክልል አኝዋክ ዞን ነዋሪዎች ነበሩ፡፡
በትውልድ ኢትዮጵ በዜግነት ሳውዲ ዓረቢያዊ የሆኑት መሐመድ አሊ አላሙዲ ንብረት የሆነው ሳውዲ ስታር ኩባንያ ከዚሁ ከጋምቤላ ብቻ 139 ሺህ ሄክታር መሬት ሩዝ እና አኩሪ አተር አምርተው የሰውዲ ዓረቢዎችን የምግብ ፍጆታ ለመሸፈን ታቅዶ ቢከናወንም ውጤታማ ሊሆን አልቻለም፡፡ የህንዱ ካራቱሪ ኩባንያ 10 ሺህ ሄክታር መሬት ጠይቆ በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በነበሩት በሟቹ አቶ መለስ ዜናዊ ቀጥተኛ ትዕዛዛና ፈቃድ ያለ ኩባንያው ፍላጎት 300 ሺህ ሄክታር መሬት ቢሰጣቸውም ውጤታማ አልሆኑም፡፡ ይህ ኩባንያ በቅርቡ 100 ሺህ ሄክታር መሬት መነጠቁን ተከትሎ በኩባንያው ባለቤት ካራቱሪና በመንግሥት በኩል አለመግባባት ተፈጥሯል፡፡ ሁለቱም ኩባንያዎች በርካታ ነዋሪዎችን አፈናቅለዋል፣ የተፈጥሮ ደኖችን ከጥቅም ውጭ አድርገዋል፡፡
በደቡብ ኦሞ ሸለቆ በተለይ በደቡብ ኦሞ ዞን ልክ እንደጋምቤላው ያለበቂ ካሳና ምክክር ከ200, 000 በላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ተፈናቅለዋል፡፡ ማፈናቀሉን ከተቃወሙት መካከል በተለይ ኩራዝ የስኳር ፕሮጀክት ግንባታ አካባቢ የነበሩ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁ ነዋሪዎች በተመሳሳይ ወታደራዊ እርምጃ ተገድለዋል፡፡ የመሬት ቅርምቱን የተቃወሙ ተፈናቃዮች መካከል በደቡብ ኦሞ እና ሐዋሳ በሚገኙ ወህኒ ቤቶች በርካቶች ሲታሰሩ፣ ከእስርና ግድያ ያመለጡ ደግሞ ወደጎረቤት ኬንያ ተሰደዋል፡፡
ሰፋፊ ለም መሬቶቹ ለባለሃብቶች ተሰጥተው፣ በመሬቱ ስም ከሀገሪቱ ከፍተኛ የባንክ ብድር እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ እስካሁን ባሉ መረጃዎች ከጅቡቲ መንግሥት እና ከግብፁ ብሔራዊ ባንክ መሬቶች በስተቀር በሌሎቹ መሬቶች ከባንክ ብድር ተወስዶባቸው በርካቶቹ ብድሮች አልተመለሱም፡፡ የባንክ ብድርንም ሆነ የመሬት ኪራይ ክፍያን ባለመፈፀም መሬት የተሰጣቸው የተለያዩ የህንድ ኩባንያዎችና የህወሓት ሰዎች ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ፡፡ ከዚሁ ሰፋፊ የመሬት ቅርምት ጋር በተያያዘ ዜጎች በግፍ ተፈናቅለዋል፣እየተፈናቀሉም ይገኛሉ፡፡ የባለሃብቶችን ድምፅ የሚሰማ አካል ቢኖርም የዜጎችን ድምፅና አቤቱታ እንዲሁም መብትና ጥቅም የሚያስጠብቅ አካል ግን አልተገኘም፡፡ የዚህ ሁሉ ችግር አብይ ምክንያት ከ”ህገ መንግሥት” እስከ ኢህአዴግ ፖሊሲ መሬት “የመንግሥትና የህዝብ ነው፣ መሬት አይሸጥም አይለወጥም” በሚል ፈሊጥ እያንዳንዱ ዜጋ የመሬቱ ባለቤትነቱ በአዋጅ እንዲነጠቅ መደረጉ ነው፡፡
በህወሓት/ኢህአዴግ ቋንቋ መሬት የመንግሥትና የህዝብ ነው፤ መንግሥትና ህዝብ ደግሞ ህወሓት ነው፡፡ ዜጋው እየኖረበት ያለበት መሬት ባለቤትነቱ በመነጠቁና በሱስ ስም “መንግሥት” እና “ህዝብ” የሚል ምናባዊ ተቋም አማካኝነት በላዩ ላይ ቤቱ ከነንብረቱ ያለማንም ከልካይ ይሸጣል፣ ይለወጣል፣ ይሄንን ተቃውሞ ጥያቄ የሚያቀርብ ደግሞ ይገደላል፣ አሊያም ይታሰራል፣ በለስ ቀንቶት ከነኚህ ርምጃዎች ካመለጠ ወደጎረቤት ሀገር ጥገኝነት ፍለጋ ይሰደዳል፡፡
ዜጎች ለምን የመሬታቸው ባለቤት አልሆኑም?
ዜጎች የመሬታቸው ባለቤቶች አለመሆናቸውና በመሬታቸው ላይ ማዘዝና መወሰን አለመቻላቸው ራሳቸውን እንደ ዜጋ የሚያዩበት አሊያም የሀገሪቱ ሉዓላዊ ግዛት ባለቤት ስለመሆናቸው የሚያስችል መብት ሙሉ ለሙሉ በህገ መንግሥቱ አዋጅ ተነጥቋል፡፡ በዚህም ከስነ ልቡና በተጨማሪ የገበሬዎች መሬት ምርታማነት ላይ ጥያቄን ያስነሳል፡፡ ምክንያቱም መሬቱን የራሱ አድርጎ መወሰንና ማዘዝ እንዲሁም ከባንክ ብድር ማግኘትም ሆነ መሸጥ የሚያስችል መብት በመነፈጉ ከእለት ጉርስ ባለፈ ስለ ምርታማነት የመጨነቅ ስሜት አይስተዋልበትም፡፡ ከባለፈው ህዳር ወር 2008 ዓ.ም. በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው ህዝባዊ አመፅ መነሻው የአዲስ አበባ እና የኦሮሚል ክልል ልዩ ዞን የተቀናጀ መስተር ፕላን ይደረግ እንጂ ዋናው ምክንያት ዜጎች የመሬት ባለቤትነታቸው ተነጥቆ በተደጋጋሚ በግፍ መፈናቀላቸው ነው፡፡ ይሄ ዛሬ በአንድ ክልል ተጀመረ እንጂ ብሶቱ ከልክ እያለፈ በሁሉም የሀገሪቱ አካባቢዎች ነገ መከሰቱ የማይቀር ነው፡፡ ለዚህ ሁሉ መፍትሄ ማስት ፕላኑን ማቆም ወይም የስርዓቱን ሰዎች ሰብስቦ የፕሮፖጋንዳ ድጋፍ ዜና እወጃ ሳይሆን መሰረታዊ የህገ መንግሥትና የፖሊሲ መሻሻል ነው፡፡
በኢትዮጵያ መሬት የእያንዳንዱ ባለ ይዞታ/ባለቤት ንብረት መሆኑን፣መሬትን የሚሸጥም ሆነ የሚሰጥ ራሱ ባለቡቱ እንደሆነ፣ መንግሥት ለከተማ መኖሪያና ማኀበራዊ አገልግሎት ተቋማት መገንባት ቢፈልግ ከባለይዞታቸው ተደራድሮ በገበያ ዋጋ እንዲገዛ ቢደረግ፣ ተቋማቱን ለመገንባት ዜጎች ተገቢውን ግብር እየከፈሉ ስለሆነ፣ በመሬታቸው ላይ የመወሰንና የማዘዝ ሙሉ ስልጣን ለእያንዳንዱ ዜጋ መሰጠት አለበት፡፡ አሁን ባለወ ነባራዊ ሁኔታ የሀገሪቱ መሬት ከፊውዳላዊ ስርዓት እጅግ የከፋ እንጂ የተሻለ ነገር የለውም፡፡ ምክንያቱም በፊውዳሉ ስርኣት ዜጎች የመሬታቸው ባለቤቶች አልነበሩም፣ ዛሬም አይደሉም፡፡ ይሄ ተለወጦ በደርግ ዘመን የካቲት 25 ቀን 1967 ዓ.ም. የታወጀው የመሬት ላራሹ አዋጅ እንደገና ተግባራዊ መደረግ አለበት፡፡ በግለሰቦችና በማኀበረሰቦች(ለግብርና እና ማኀበራዊ አገልግሎት) ያልተያዙ ቦታዎችን መንግሥት ለማኀበራዊ አግልግሎት ለማዋል ቢወስን ግልፅነትና ተጠያቂነት ባለበት መልኩ እንዲከናወን ግልፅ የሆነ ህጋዊ ማዕቀፍ ሊኖረው ይገባል፡፡ አሁን ያለው የጠባብ ፖለቲካዊ ቤተሰብ ግንኙነት ውርስ አሰራር መቆምና በግፍ የተወሰደው መሬት ለተፈናቃዮችና ባለቤቶች መመለስ እና አሰራሩ መከለስ ይኖርበታል፡፡
በሌላ በኩል የተለያዩ የሀገሪቱ ዩኒቨርስቲዎች በግብርና ሙያ በርካታ ተማሪዎችን እያስተማሩ ቢያስመርቁም፤ ባለሙያዎቹ የቀሰሙትን እውቀት አሟጠው እንዲጠቀሙ፣ ሀገሪቱንም እንዲጠቅሙ፣ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ረገድ የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ የመሬት አቅርቦትም ሆነ የባንክ ብድር በመንግሥት አልተመቻቸም ሳይሆን አልተፈቀደላቸውም፡፡ በሌላ በኩል ከግብርናው ጋርም ሆነ ከንግድ ጋ ምንም እውቀት የሌላቸው የህወሃት ሰዎች በፈለጉት ሰዓት የፈለጉትን መሬት ለሚፈልጉት ዓላማ በፈለጉት ቦታ ሲያገኙ፣ የባንክ ብድርም በፈለጉት ሰዓት ያገኛሉ፤ በተመሳሳይ የውጭ ባለሃብቶችም እንዲሁ፡፡ ነገር ግን ጊዜያቸውን እና ገንዘባቸውን መስዋዕት አድርገው ከ16 ዓመታት ያላነሰ በእውቀት ማዕድ ላይ የነበሩና ያሉ ዜጎች አብዛኞቹ ስራ አጥ ሆነው ስራ ለማግኘት መንግሥት እንዲጠብቁ ሲፈረድባቸው፣ በለስ የቀናቸውም ቢሆኑ አውቀታቸው በአግባቡ ስራ ላይ ለማዋዕል የሚያስችል መንግሥታዊ አገልግሎት ባለመኖሩ ቢሮ ገብቶ ወርሃዊ ደመወዝ በመጠበቅ ሙሉ ለሙሉ መንግሥት ላይ ጥገኛ እንዲሆኑ ይገደዳሉ፡፡
በሀገሪቱ የሀገሪቱን ነባራዊ ሁኔታ፣ የተፈጥሮ ሃብት አጠቃቀም፣ ኢኮኖሚውን በተመለከተ የዜጎችን መብትና ጥቅም ሊያስጠብቅ የሚያስችል ፖሊሲ ባለመኖሩ ከሌሎች ሀገረች ሲነፃፀር እንደ ኢትዮጵያ በእውቀትና በትምህርት ኪሳራ የደረሰባትም ሆነ የሚደርስባት ሀገር ስለመኖሯ አጠራጣሪ ነው፡፡ ቢያንስ በግብርና ሙያ የሚመረቁ ባለሙያዎች በየመስካቸው በቂ የመሬት አቅርቦት እና የባንክ ብድር ቢመቻችላቸው ከራሳቸው አልፈው ሀገሪቱን በብዙ መልኩ መጥቀም በቻሉ ነበር፡፡ ምናልባት የተሻለ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ሽግግር ቢያስፈልግ እንኳ እዛው በሚማሩበት የትምህርት ተቋም ማመቻቸት አሊያም ለተጨማሪ አጫጭር የሙያ ስልጠናዎቹን ሊሰጡ የሚችሉ በዘርፉ ውጤታማና ከእኛ ልቀው ካሉ ሀገሮች ባለሙያዎችን አምጥቶ አሰልጥኖ ወደስራ እንዲገቡ ቢደረግ የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ፣ የስራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ፣ የዜጎችን መብትና ጥቀምን ለማስጠበቅና ለመጠበቅ እጅግ የተሸሉ ቢሆኑ እንጂ የሚያንሱ አይደሉም፡፡ የአካባቢና የተፈጥሮ ሃብት አጠቃቀም ላይም ቢሆን በተገቢው መንገድ እንዲከናወን በማድረግም ሆነ ጥራት ያለው ምርት አምርቶ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ለማስገኘትም ቢሆኑ ከውጭ ባለሃብቶችም ሆነ በፖለቲካ ወገንተኝነት ከሚደረግ የጥቅም ትስስር በእጅግ የዘርፉ ተማሪዎች ውጤታማ ስለመሆናቸው ጥርጥር የለውም፡፡
በርግጥ ዜጎች ሁሉ በፖለቲካው፣ በኢኪኖሚውም ሆነ በማኀበራዊ አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ ስርዓቱ ላይ ጥገኛ እንዲሆኑ ከሚሰራ እና ራሱን የአናሳ ብሔር ተወካይ አድርጎ በዘረኝነት ፖለቲካዊ ወገንተኝነት በተጠመደ ህወሓት/ኢህአዴግ ቡድን ከላይ የተጠቀሰውን ቀና አስተሰሰብ መጠበቅ የዋህነት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ነገር ግን ጥቅሙ ለባለሙያዎቹ፣ ለሀገሪቱም፣ ለህዝቡም ሆነ ለራሳቸው የተሻለ ጥቅም ያለውና አዋጭ መፍትሄ ነው፡፡ መፍትሄዎቹ ላለፉት 25 ዓመታት ባለመወሰዳቸው የመሬት ቅርምቱ በሀገሪቱ ሰላምና መረጋጋት፣ ፖለቲካ፣ ኢኮኖሚና ማኀበራዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ ችግር አስከትሏል፣ የተለመደው የኪሳራ አካሄድ አሁንም በተጠናከረ መንገድ ቀጥሏል፡፡ የዚህ ሁሉ መዘዝ ግን አንዱን አካባቢ ብቻ ነጥሎ ጉዳት የሚያደርስ ሳይሆን አጠቃላይ በሀገሪቱ ኢኮኖሚና ፖለቲካ ማኀበራዊ ጉዳይ ላይ የራሱን አሉታዊ ጫና ማሳረፉ አልቀረም፡፡ የመሬት ባለቤትነት የህግ ማሻሻያ እና የፖሊሲ ለውጥ ካልተደረገ ዜጎች ከመሬታቸው በግፍ የመፈናቀል እና የመሬት ቅርምቱ ተጠናክሮ መቀጠሉ የሚያጠያይቅ አይደለም፡፡
Ethiopian Pastor, Translator and two others Charged With Terrorism
By Felix Horne
The charging of Pastor Omot Agwa, World Bank Inspection Panel translator and two others under Ethiopia’s anti-terrorism Law. The charges focus around their attendance at a food security workshop in Nairobi put on by several well-known organizations. The charges are absurd, even by Ethiopian standards. The second man was charged largely based on producing a research paper that was intended to be presented at the workshop. It was entitled “Deforestation, Dis-Possession and Displacement of Gambela in General and Majang People in particular.”

Pastor Omot Agwa was charged by Ethiopian authorities under the anti-terrorism law after being detained for nearly six months.
Here is detail press release as follow;
Ethiopia: World Bank Translator, Activists Face Trial
Activists Heading for Food Workshop Charged With Terrorism
Ethiopian authorities should immediately drop all charges and release a former World Bank translator and two other local activists charged under Ethiopia’s repressive counterterrorism law after trying to attend a workshop on food security in Nairobi, six international development and human rights groups said today.
On September 7, 2015, the authorities charged Pastor Omot Agwa, Ashinie Astin, and Jamal Oumar Hojele under the counterterrorism law after detaining them for nearly six months. The charge sheet refers to the food security workshop, which was organized by an indigenous rights group and two international organizations, as a “terrorist group meeting.” The three were arrested on March 15 with four others while end route to the workshop in Nairobi, Kenya. Three were released without charge on April 24, and a fourth on June 26.
“Ethiopia should be encouraging debate about its development and food security challenges, not charging people with terrorism for attending a workshop organized by respected international organizations,” said Miges Baumann, deputy director at Bread for All. “These absurd charges should be dropped immediately.”
Omot, of the evangelical Mekane Yesus church in Ethiopia’s Gambella region, was an interpreter for the World Bank Inspection Panel’s 2014 investigation of a complaint by the Anuak indigenous people alleging widespread forced displacement and other serious human rights violations in relation to a World Bank project in Gambella. He had raised concerns with workshop organizers about increasing threats from Ethiopian security officials in the weeks before his arrest.
The food security workshop in Nairobi was organized by Bread for All, with the support of the Anywaa Survival Organisation (ASO) and GRAIN. Bread for All is the Development Service of the Protestant Churches in Switzerland. ASO is a London-based registered charity that seeks to support the rights of indigenous peoples in southwest Ethiopia. GRAIN is a small international nonprofit organization based in Barcelona, Spain that received the 2011 Right Livelihood Award at the Swedish Parliament for its “worldwide work to protect the livelihoods and rights of farming communities.”
The objective of the Nairobi workshop was to exchange “experience and information among different indigenous communities from Ethiopia and experts from international groups around food security challenges.” Participants from Ethiopia were selected by ASO based on their experience in supporting local communities to ensure their food security and access to land.
The charge sheet accuses Omot of being the co-founder and leader of the Gambella People’s Liberation Movement (GPLM) and communicating with its leaders abroad, including ASO Director Nyikaw Ochalla, who is described in the charge sheet as GPLM’s London-based “senior group terrorist leader.” Omot faces between 20 years and life in prison. Ashinie is accused of participating in the GPLM, including communicating with Nyikaw and preparing a research document entitled “Deforestation, dispossession and displacement of Gambela in general and Majang people in particular.” Jamal Oumar is accused of being a participant of a “terrorist group” and of organizing recruits to attend the Nairobi workshop.
The GPLM is not among the five organizations that the Ethiopian parliament has designated terrorist groups. It is an ethnic Anuak organization that fought alongside the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) to oust the repressive Derg regime in the 1990s, and was folded into the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) power structure in 1998. Currently the GPLM has no public profile, no known leadership structure, and has not made any public statement of its goals.
“For the government to make criminal allegations against me because I assisted in coordinating a workshop about land and food issues in Ethiopia is simply incredible,” said Nyikaw Ochalla, ASO executive director. “Trying to give indigenous people a voice about their most precious resources – their land and their food – is not terrorism, it’s a critical part of any sustainable development strategy.”
All three detainees were recently moved to Kalinto prison, on the outskirts of the capital, Addis Ababa, after spending more than five months in Maekelawi, the Federal Police Crime Investigation Sector in the city. Human Rights Watch and other organizations have documented torture and other ill-treatment at Maekelawi. Omot, and possibly the other two, were held in solitary confinement for three weeks upon their arrest, and all have had limited access to family members. Jamal and Omot have reportedly been in poor health.
The detainees were held 161 days without charge, well beyond the four months allowed under Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation, a period in violation of international human rights standards and among the longest permitted by law in the world. The next hearing in the case is scheduled for October 22, 2015.
Since 2011, Ethiopia’s counter-terrorism law has been used to prosecute journalists, bloggers, opposition politicians, and peaceful protesters. Many have been accused without compelling evidence of association with banned opposition groups.
In August 2015, 18 leaders of protests by the country’s Muslim community were convicted and sentenced to between 7 and 22 years in prison. The ongoing trial of the members of a group called Zone 9 bloggers has been adjourned 36 times.
Human Rights Watch and other organizations have documented numerous incidents in which individuals critical of Ethiopia’s development programs have been detained and harassed, and often mistreated in detention. Journalists have been harassed for writing articles critical of the country’s development policy.
“These three men are the latest victims of the Ethiopian government’s crackdown on independent activists,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director at Human Rights Watch. “The arrests, lengthy detentions, and spurious terrorism charges bear all the hallmarks of Ethiopia’s effort to silence critical voices.”
Case of Pastor Omot Agwa
In February 2014, Omot acted as interpreter and facilitator for the World Bank Inspection Panel during its visit to Gambella to investigate a complaint brought by former Gambella residents concerning the bank’s Protection of Basic Services (PBS) program. The program funded block grants to regional governments, including paying salaries of government officials.
The former residents alleged that the program was harming them by contributing to the government’s abusive “villagization” program. The program forcibly evicted indigenous and other marginalized peoples from their traditional lands and relocated them to new villages. In its report to the World Bank board of directors, which was leaked to the media in December 2014, the Inspection Panel concluded that the bank had violated some of its own policies in Ethiopia.
In February 2015, the World Bank board considered the Inspection Panel’s recommendations. Shortly thereafter, Omot reported that he was under increasing pressure from Ethiopian security personnel. While the Inspection Panel had not disclosed Omot’s identity in its report, it included a photograph of him with other community members, which was removed from subsequent versions. The week before his arrest, several people told Omot that a well-known federal security official from Gambella was looking for him.
On March 15, Omot texted an emergency contact that security officials at Addis Ababa’s international airport had detained him and the six others as they were heading for the workshop in Nairobi. Several days later, a witness saw four armed federal police officers and four plainclothes security officials take Omot, in chains, to his house in Addis Ababa, where they removed computers, cameras, and other documents.
The seizure of Omot’s computers and other materials raises concerns about the security of other Gambella community members the Inspection Panel interviewed. Given the severe restrictions on human rights investigation and reporting in Ethiopia, it is virtually impossible for rights groups to learn about reprisals in the villages the Inspection Panel visited.
Within days of Omot’s arrest, Human Rights Watch and other organizations alerted the World Bank Group president, Jim Yong Kim, and the European Union, United States, and Swiss missions in Addis Ababa. But on March 31, the World Bank board approved a new US$350 million agriculture project in Ethiopia. On September 15, the World Bank approved a $600 million Enhancing Shared Prosperity through Equitable Services project, which is replacing one of the subprograms of the PBS program.
World Bank staff assert that they have privately raised the case with Ethiopian government officials, but the nature of any communications is unclear. In a May meeting with nongovernmental organizations in Washington, DC, World Bank staff said that the government had informed them that Omot’s arrest was in accordance with Ethiopian law and unrelated to the bank’s accountability process.
The organizations seeking this press release of Omot, Ashine, and Jamal are:
Human Rights Watch
Bread for All
GRAIN
Anywaa Survival Organization
Oakland Institute
Inclusive Development International
Source: https://www.hrw.org/news/2015/09/21/ethiopia-world-bank-translator-activists-face-trial
Local Ethiopians miss out as big agriculture firms struggle in Gambella
William Davison in Gambella
As dusk envelops the grasslands of Gambella in western Ethiopia, a weary Jakob Pouch sits on a jerry can, resting his chest against a wooden staff. The 45-year-old evangelical preacher from the Nuer community has just made the three-hour walk from the banks of the Baro river, where he tends to his large family’s small plot of corn. His daughters are preparing cabbage and cobs to be cooked on an open fire.
In the opposite direction, across the asphalt road that leads to South Sudan, lies the farm of BHO Bioproducts, an Anglo-Indian company growing rice and cotton on the 27,000 hectares (67,000 acres) it has leased.
Pouch says the company doesn’t care about the people of his village, Wath-Gach. Grazing land has been lost, and BHO has built a wooden cage around a water pump to prevent locals using it. “From the beginning we did not have a good relationship,” he says. “It was given without consultation. There has been lots of negative impact.” The company didn’t respond to a request for comment.
BHO’s operation, which began in 2010, is one of many concessions Ethiopia’s government has granted in Gambella, including one plot leased to the Indian company Karuturi Global of 100,000 hectares. Commercial farmers are expected to bring knowhow, technology and jobs to one of the country’s poorest and most remote regions. By converting uncultivated bush into productive farms, officials believed food security and export revenues would improve in a country dominated by subsistence agriculture.
But despite those worthy ambitions, progress has been hampered by Gambella’s logistical difficulties, and a failure to ensure local communities benefit.
The village of Ilea is home to people from Gambella’s other main indigenous group, the Anuak. It’s also been the headquarters of Karuturi’s operation for the past five years. In the village, a group of men shelter from the afternoon heat, passing round a tobacco waterpipe. Behind them, women draw water from a well built by the government.
Karuturi’s project has stalled after managers discovered that four-fifths of the land is in a floodplain. The firm also failed to build relations with residents, according to the elders. Complaints include reduced land for farming and hunting, no promised health clinic, cattle dying from ingesting pesticides, the burning of unwanted maize, and only a handful of jobs for villagers. “The government benefits from the tax but the community does not benefit,” says Obang Wudo, one of the elders.
The gripes of Ilea’s residents about Karuturi are compounded by their concerns about nearby land parcelled out to Ethiopian investors from outside Gambella. They say they frequently lobby the regional government to act, but nothing has been done.
That region’s president, Gatluak Tut Khot, expresses support for investors engaged in “very difficult work”. The regional government can’t force companies to pay more, he explains, but his administration has held meetings to improve relations. “They have to respect the interests of the community and those who need jobs from them,” he says.
Gambella has been the focus of a political fallout between the central government and advocacy groups such as Human Rights Watch and the Oakland Institute – with donors uncomfortably positioned in the middle. The critics claim that aresettlement programme to move scattered rural populations to larger settlements was coercive and designed to clear the way for investors. Ethiopia says rights groups from the global north are ideologically opposed to its state-heavy development model and that the voluntary resettlement programme was to make public service delivery more cost-efficient. The UK’s Department for International Development and the World Bank are facing legal inquiries for funding the salaries of civil servants who staffed the enlarged villages.
Bikrum Gill is studying the impact of Indian investors on Gambella’s people for his doctorate, with a specific focus on Karuturi. He found that locals had hoped to access more food and better farming technologies, but were often disappointed. Instead, communities lost land and flooding worsened. Speaking specifically about the Karuturi investment, Gill says: “It’s difficult to ascertain, what, if any, benefits this project has brought to affected local people.”
Karuture farm managers at the site referred inquires to the company’s head office, which didn’t respond to attempts to contact it.
One farmer from Ethiopia’s highlands, who did not want to be named, tells a different story. He thinks the wave of commercial farming will transform an economic backwater. “They were sitting on the side of the riverbank,” he says about locals. “If investors are coming, their life has changed, they are operators, technicians.” He pays 50 birr (about £1.60) a day – above the average for manual labour in Ethiopia – and provides transport for his workers. Eight houses have been built for teachers, he says, and 25 hectares cleared for the community to plough.
Some larger enterprises are also reaching out. At the request of the regional administration, Saudi Star Agricultural Development’s four-year-old rice farm in another part of the region has hired 40 local professionals, while district governments will each get two tractors for young people to use.
“We know we’re creating job opportunities, transforming skills, training locals,” says the firm’s chief executive, Jemal Ahmed. “The community has to profit from the project and we have social responsibility.” He is fully aware of local sensitivities about the company’s work. The farm, bankrolled by Ethiopian-born Saudi billionaire Mohammed al-Amoudi, was attacked by gunmen two years ago and has been criticised as a land-grab.
Ahmed says no one was displaced from Saudi Star’s 10,000 hectares, which were earmarked in the late 1980s by the previous government for large-scale agriculture. “It’s not part of any villagisation, it’s not been grabbed – that’s a fact,” he says. “But people who have their own agenda, – Oakland Institute and Human Rights Watch – fabricated stories and campaigned against this project.”
Gill says part of the problem is that investors are “not seeing the people on the land … It precludes the possibility of engaging with locals. To succeed you have to build out of local diversity and knowledge.”
Source: http://www.theguardian.com/global-development/2015/jan/01