የነ አቶ አንዱዓለም አራጌና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ክስ ውሳኔ በድጋሚ ተቀጠረ
በእነ አንዱዓለም አራጌ የክስ መዝገብ ለፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ የጠየቁት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አቶ አንዱዓለም አራጌ እንዲሁም እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ ናትናኤል መኮንን፣ አቶ አንዱዓለም አያሌው፣ ሻምበል የሺዋስ ይሁንዓለም፣አቶ ዮሐንስ ተረፈ፣አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ እና አቶ ምትኩ ዳምጤ ውሳኔ ለዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2005 ዓ.ም. ተቀጥሮ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ 6 ኪሎ የሚገኘው የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የይግባኙን የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ቢጠበቅም ውሳኔውን ሳይሰጥ ለአምስተኛ ጊዜ ለሚያዚያ 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ተቀጠረ፡፡
ፍርድ ቤቱም ውሳኔውን ሊሰጥ ያልቻለበትን ምክንያት ሲገልፅ የክሱን ሂደት ገና መርምሬ አልጨረስኩም በሚል ተጨማሪ ቀነ ቀጠሮ መስጠቱን አስታውቋል፡፡ በወቅቱ የፍርድ ቤቱ ዳኞች ሽመክት አሰፋ፣ በላቸው አንሺሶ እና ዳኜ መላኩ ተሰይመው ሲሆን ከከሳሽ በኩል አቃቤ ህግ ብርሃኑ ወንድማገኝ እንዲሁም ከተከላካይ ጠበቆች አቶ አበበ ጉታ፣ አቶ ደርበው ተመስገን እና አቶ ሳሙኤል አሰፋ ተገኝተዋል፡፡ ተከሳሾችም በሰዓቱ የቀረቡ ቢሆንም የነበረው በበርካታ ያልተለመደ የጦር መሳሪያ አጀብ አዲስ ያልተለመደ ክስተት ቢሆንም በተለይ የአቶ አንዱዓለም አራጌ በከፍተኛ ደረጃ መጎሳቆል የችሎት ታዳሚዎችን ሐዘን ውስጥ ከቶ ተከሳሾቹ የውሳኔ ፍርዱ ሳይሰጥ ከቀኑ 6፡30 ሰዓት ወደ የመጡበት እስር ቤት ተመልሰዋል፡፡
ማፈናቀሉ እስከመቼ?
ብስራት ወልደሚካኤል
ህወሓት/ኢህአዴግ በህይወቱ ከሚፈራውና ከሚጠላው ነገር አንዱ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ዜጋ ማየትና መስማት ነው፡፡ ምክንያቱም የድርጅቱ አባላት በባህሪያቸው በውሸት፣ በተንኮልና በዕውቀት አስተሳሰብ አድማስ ደካማ ስለሆኑ የዜጎችን አንድነትና ብሔራዊነት ስሜትን አጥብቀው ይጠላሉ፤ ይህንንም በማሰራጨት የማሃይሞችን ርካሽ ፖለቲካ አራምደውበታል፣እያራመዱም ይገኛሉ፡፡ የዚህ ዋነኛ ተባባሪ ደግሞ በህወሓት የሚነዱት ብአዴን፣ ኦህዴድ እና ደኢህዴን ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት የሀገሪቱን አንድነትና ደህንነት አደጋ ላይ በመጣላቸው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዝምታ ሊያልፍ ስለማይገባ እስካሁን ለፈፀሙት ሁሉ አስፈላጊውን ሰነድ በእጃችን ማስገባት፣ ድርጊቱን የፈፀሙትንና ተባባሪዎቹን ስም ዝርዝር ከነ ሙሉ አድራሻቸው መያዝ፣ ጉዳት የደረሰባቸውና ሚደርስባቸው ዜጎችን መርዳትና መንከባከብ እንዲሁም ወንጀለኞችን በተለያዩ ማኀበራዊ ሚዲያዎች(Facebook, blog, twitter,….) ጨምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በማጋለጥ ለህግ እንዲቀርቡና ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ የሁላችንም ኢትዮጵያዊያን የውዴታ ግዴታ መሆን ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ዛሬ በሰፊው የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ላይ በህወሓት/ኢህአዴግ እየደረሰ ያለው ግፍ በተመሳሳይ መልኩ ነገ በሌሎችም ላይ ይደርሳል፤ ከዚህ በፊትም ደርሷልና፡፡
ስለዚህ በቅርቡ በደቡብ ክልል ቤንች ማጂ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ለረጅም ጊዜ ሀብት ንብረት አፍርተውና ተዋልደው የኖሩ የአማርኛ ተናጋሪዎችን የማፈናቀል ስራ የተሰራውን መረጃ በሚመለከት ፣
አሁን ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያሶ ወረዳ እንዲፈናቀሉ የተደረጉት የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ለሞት.ለስቃይና ለመከራ እንዲደረጉ የተደረገበትን ምክንያት በዝርዝር በማጣርት መረጃውን ይፋ በማድረግ ሁሉም ዜጋ በጋራ ሊያወግዝና የተፈናቀሉትም ወደነበሩበት ስፍራ በክብር እንዲመለሱ ለማድረግ በሀግር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን በጋራ መስራት ይጠበቅብናል ብዬ አስባለሁ፡፡ ለዚህም በሀገር ውስጥ ያሉ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ ፖለቲከኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ወደስፍራው በመሄድ አስፈላጊውን ጥናት በማድረግ መረጃውን ለህዝብ ይፋ ማድረግና የድርጊቱ ፈፃሚዎችም በአስቸኳይ ለህግ እንዲቀርቡ አስፈላጊውን ሁሉ ማድረግ፣
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ይህን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለዓለም አቀፉ ማኀበረሰብ በማጋለጥ ለኢህአዴግ የሚደረገው የለጋሾች ድጋፍ ለሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሚውል ማረጋገጥና ድጋፉ እንዲቋረጥ ከማድረግ በተጨማሪ መረጃውን ለሚሰበስቡ ሀገር ውስጥ ላሉ ሀገር ወዳድ ሰባዓዊ ባለሙያዎች የገንዘብ፣ የቁሳቁስና የሙያ ድጋፍ ማድረግ፣
በተለይ ወንጀሉ የሚፈፀምባቸው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ወገኖቻችን ወኪል ነኝ የሚለውን ብአዴን/ኢህአዴግ አባላት ጉዳዩን አጥብቀው በመጠየቅ ለድርጅቱ የሚያደርጉትን ድጋፍ ሙሉ ለሙሉ በማቋረጥ ለህዝብ እና ለሀገር ያላቸውን ወገንተኝነት ማረጋገጥ፣ ከፓርቲውም በይፋ በመልቀቅ ህዝባዊ ዓላማ ያለውን ትግል መቀላቀልና የወንጀል ተባባሪ አለመሆናቸውን በተግባር በማሳየት ከነገ ተጠያቂነት እራሳቸውን ነፃ ማድረግ፣
የሌላው ማኀበረሰብ ኢትዮጵያዊያን ድርጊቱን በጋራ በማውገዝ አሁን እየተፈፀመ ያለው ዘግናኝና አሰቃቂ ወንጀል ወደ ሌሎችም መዛመቱ ስለማይቀር “ማፈናቀሉ እስከመቼ?” በሚል ሁሉም በጋራ በመንቀሳቀስ በራሱ ተስፋ የቆረጠውን ዘረኝነት አገዛዝ እርቃኑን በማስቀረት ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን በማፅናት የዜጎች ሰብዓዊ መብት በሙሉ መከበሩን ለማረጋገጥ የዜጎች ከሀገራቸው መፈናቀል፣ መሰደድ፣ በግፍ መታሰርና መገደል ማብቃት አለበት እላለሁ፡፡ አለበለዚያ ነገ ሁላችንም ከሀገራችን መፈናቀላችን አይቀሬ ስለሆነ ዛሬውኑ ቆም ብለን በማሰብ ማድረግ ያለብንን መወሰን ያለብን ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ማንም ኢትዮጵያዊነታችንን ሲፈልግ ወስዶ እንካችሁ፤ ሳይፈልግ ዜግነታችሁን እኔ የምሰጣችሁ ስፍር ብቻ ነው ሲሉ መፍቀድ ባርነትን ከመምረጥ ውጭ ምን ትርጉም ልንሰጠው እንችላለን? እኔ በበኩሌ ባርነትን በፍፁም አልመርጥም፣ አልደግፍምም፡፡
! …. የኢህኣዴግ ኣጀንዳና የኣማራ ተወላጆች መፈናቀል …..!
አብርሃ ደስታ
(ከመቀሌ)
በዚ መሰረትም ‘የሌላ’ ክልል ተወላጆች በ’ሌላ ክልል’ መሬት የማግኘት መብታቸው ሲነፈጉ ይታያል። የኣማራ ተወላጆች ብዙ ግዜ ኑሮኣቸው ከመሰረቱበት ቀያቸው በኃልና በግፍ ሲፈናቀሉ እያየን ነው። በቡድን መብት መሰረት የኢትዮዽያ ሕጋዊ ዜጎች በገዛ ሀገራቸው መኖርያ መሬት ሲከለከሉ ማየት እጅግ ያሳዝናል። በሌላ በኩል በስልጣን ያለ ድርጅት (የራሱን ዜጎች እያፈናቀለ) መሬ ታችን ተቀባይነት በሌለው መንገድ ለዉጭ ዜጎች ሲቸረችር ይታያል። ዜጎቻችን በገዛ መሬታቸው ባዕድ ሁነዋል ።
የሚገርመው ደግሞ ‘መሬት ኣይሸጥም ኣይለወጥም’ ከሚል ግራ የተጋባ ፍልስፍና መሬታችን ለውጭ ዜጎች የሚሰጠው በነፃ ሊባል በሚችል ሁኔታ መሆኑ ነው። (በነፃ የሚሰጥበት ምክንያት መሬት ተሸጠ እንዳይባል ነው)። የኣማራ ተወላጆች ከቀያቸው መፈናቀል የገዢው ፓርቲ የተሳሳተ ፖሊሲና ለህዝብ ያለው ንቀት የሚያሳይ ነው። ዜጎችን በማባረር (‘ሕጋዊ ያልሆኑ ኗሪዎች’ በሚል ስም) መሬት ለውጭ ዜጎች ሲሰጥ እነዚህ የሌላ ሀገር ዜጎች እንዴት ‘ሕጋዊ’ ሆኑ???
ሰዎች ከቀያቸው በሃይል (በግፍ በዘርሓረጋቸው እየተለዩ) ሲፈናቀሉ (ሲባረሩ) የከፋ የሰብኣዊ መብት ጥሰት ነው። ዜጎቻችን (ወገኖቻችን) ሲፈናቀሉ የሚደርሳቸው ኢኮኖሚያዊ፣ ማሕበራዊና ስነልቦናዊ ቀውስ (Helplessness) መገመት ኣይከብድም። ሁሉም ኢትዮዽያ ሊተባበራቸው ይገባል፤ መንግስት ይህን ተግባሩ እንዲያቆም ተፅዕኖ ማድረግ ኣለብን።
እኛም እየተፈናቀሉ ካሉ ሰዎች ጎን መሰለፍ ያለብን ይመስለኛል። ምክንያቱም (1) ወገኖቻችን ናቸው። እኛ ኢትዮዽያውያን ያልደረስንላቸው ማን መጥቶ ይረዳቸዋል? (2) ዛሬ በኣማራ ተወላጆች እየተፈፀመ ያለው ግፍ (ኣሁንኑ ካልቆመ) ነገ በእያንዳንዳችን እንደሚፈፀም ማወቅ ይኖርብናል። (3) የማፈናቀል ተግባሩ የብሄር ፖለቲካ ችግር ኣባብሶ የጥላቻ ፖለቲካ ስር ሰዶ የኢትዮዽያ ሀገራችን ኣንድነት የሚፈታተን ይሆናል።
የስርዓቱ ደጋፊዎች ይህንን ችግር ተረድታቹ በገዢው ፓርቲ Pressure ፍጠሩ ፤ ኣለበለዝያ ግን ችግሩ ሁሉም ዜጋ ይነካል። በተለይ የትግራይ ተወላጆች በግልፅ ተቃውሞኣችንን ማሰማት ኣለብን። ህወሓት /ኢህኣዴግ ከተግባሩ እንዲቆጠብ ማድረግ ወይ ተግባሩ እንዲያቆም በመቃወም ከነዚህ ተፈናቃዮች ጎን መሰለፍ ኣለብን። ምክንያቱም እነዚህ ተፈናቃዮች ብዙ ችግር እንደሚደርስባቸው የታወቀ ነው። ቂም መያዛቸው (በገዢው ፓርቲ ቅር መሰኘታቸው) ኣይቀርም። ገዢው ፓርቲ (ኢህኣዴግ) የህወሓት ስራ መሆኑ ይታወቃል። ህወሓት ስልጣን መያዝ የቻለው በትግራይ ህዝብ ትግል ነው (ህወሓት ህዝቦች ማፈናቀል ወይ መጨቆን እንዲችል ለማብቃት ባይሆንም)።
ስለዚ የኣማራ ተፈናቃዮች በህወሓት ተግባር ምክንያት በትግራይ ህዝብ ቅር ሊሰኙ ይችላሉ። እንዲህ ከሆነ ደግሞ ዛሬ በኣማራ ህዝብ እየተፈፀመ ያለው ግፍ ነገ በትግራይ ህዝብ መደረጉ ኣይቀርም። ግለሰዎች በስልጣን ለማቆየት ሲባል በሰለማዊና ንፁህ ዜጎች ግፍ እየተፈፀመ ዝም ብሎ መመልከት ተገቢ ኣይደለም።
ስለዚ ተቃውማችን ማሰማት ኣለብን። ደሞ የትግራይ ተወላጆች በኣማራ ክልል የሉም? የደቡብ ክልል ወይ ኦሮምያ ወይ ሌላ ክልል ተወላጆች በኣማራ ክልል የሚኖሩ የሉም ? የማፈናቀሉ ተግባር ካልቆመ መጨረሻው ምን ሊሆን ነው? ስለ ሌሎች ስናስብ ስለራሳችን እያሰብን ነው፤ ሌሎችን ስንተባበር ራሳችን እየተባበርን ነው። ተግባራችን ስንቃችን ነው።
ለዜጎች ቅድምያ እንስጥ!
It is so!!!
Ethiopia’s Human Rights Crisis Worsened
By Betre Yacob.
The human rights situation in Ethiopia, the most important strategic and security ally of the Western powers, has worsened drastically, according to the 2013 Human Rights Watch’s World Report, which summarizes the human rights situation of more than 90 countries worldwide—drawing on events from the end of 2011 through November 2012.
The 665 page report says that Ethiopia’s dictatorial regime has deliberately continued to severely restrict fundamental rights of freedom of expression, association, and assembly. In addition, the report indicates that intimidation, arbitrary arrest, torture, forced displacement, and killing remain routine throughout the country.
The report, which reflects extensive investigative work that Human Rights Watch undertook in collaboration with local human rights activists, was released in the beginning of February 2013. Providing heartbreaking examples, cases, and photographs, the report explains enough how dramatically the human rights crisis in Ethiopia has been worsening.
“Freedom of Expression, Association, and Assembly”
According to the report, the Anti-Terrorism Law and the Charities and Societies Proclamation (CSO Law), which criminalize independent reporting on opposition and human rights activities, have severely restricted freedom of expression, assembly, and association in Ethiopia. The report says that as a result of these two draconian laws—independent journalists, opposition politicians, human rights activists have been subjected to persistent harassment, threats, intimidation and persecution by the government authorities.
The report explains: “Ethiopia’s most important human rights groups have been compelled to dramatically scale-down operations or remove human rights activities from their man-dates, and an unknown number of organizations have closed entirely. Several of the country’s most experienced and reputable human rights activists have fled the country due to threats.”
Mentioning the Committee to Protect Journalists (CPJ), the report says that Ethiopia has now become a very dangerous country for independent journalists. This is why, the report says, “more journalists have fled Ethiopia than any other country in the world due to threats and intimidation in the last decade.”
The report, which says the Anti-Terrorism Law is misused by the government to silence opponents and repress dissent, states that only in 2012 30 journalists, political activists, and opposition party members were convicted miserably on unclear terrorism offenses under the Law. According to the report, 11 journalists in total have been convicted under the same law— since 2011.
The report explains: “On January 26, 2012, a court in Addis Ababa sentenced both deputy editor Woubshet Taye and columnist Reeyot Alemu of the now-defunct weekly Awramaba Times to 14 years in prison. On July 13, veteran journalist and blogger Eskinder Nega, who won the prestigious PEN America Freedom to Write Award in April, was sentenced to 18 years in prison along with other journalists, opposition party members, and political activists. Exiled journalists Abiye Teklemariam and Mesfin Negash were sentenced to eight years each in absentia under a provision of the Anti-Terrorism Law that has so far only been used against journalists.”
It further says: “On July 20, after the government claimed that reports by the newspaper Feteh on Muslim protests and the prime minister’s health would endanger national security, it seized the entire print run of the paper. On August 24, Feteh’s editor, Temesghen Desalegn was arrested and denied bail. He was released on August 28, and all the charges were withdrawn pending further investigation.”
The report also reveals that the government of Ethiopia is committing human rights violations in response to the ongoing Muslim protest movement in the country. It says federal police use excessive force, including beatings, to disperse peaceful protesters.
With regard to this, the report, for instance, says: “On July 13, police forcibly entered the Awalia Mosque in Addis Ababa, smashing windows and firing tear gas inside the mosque. On July 21, they forcibly broke up a sit-in at the mosque. From July 19 to 21, dozens of people were rounded up and 17 prominent leaders were held without charge for over a week. Many of the detainees complained of mistreatment in detention.”
“Extrajudicial Executions, Torture and other Abuses in Detention”
The 665 page report says that there have been so far widespread extrajudicial executions, torture and other brutal abuses in different detention centers and military barracks of the tyrannical regime in Ethiopia. It notes that Human Rights Watch has continued to document such executions and abuses.
The report explains: “An Ethiopian government-backed paramilitary force known as the “Liyu Police”, for instance, executed at least 10 men who were in their custody and killed 9 other villagers in Somali Region on March 16 and 17 in Raqda village, Gashaamo district.”
It further says: “In April, unknown gunmen attacked a commercial farm owned by the Saudi Star company in Gambella that was close to areas that had suffered a high proportion of abuses during the villagization process. In responding to the attack, Ethiopian soldiers went house to house looking for suspected perpetrators and threatening villagers to disclose the whereabouts of the ‘rebels’. The military arbitrarily arrested many young men and committed torture, rape, and other abuses against scores of villagers while attempting to extract information.”
Additionally, the report states that there is what it says “erratic access” to legal counsel and insufficient respect for other due process during custody, pre-trial detention, and even during trial phases, when the cases are politically related. “This places detainees at risk of abuse”, the report says.
“Forced Displacement”
The report notes that although the government maintain that “villagization” is a voluntary program designed to improve access to basic services by bringing scattered people all together in new villages, the reality is that the program is involuntary and mainly designed to make way for huge agriculture investments.
The report explains: “In Gambella and in the South Omo Valley, forced displacement is taking place without adequate consultation and compensation. In Gambella, Human Rights Watch found that relocations were often forced and that villagers were being moved from fertile to unfertile areas. People sent to the new villages frequently have to clear the land and build their own huts under military supervision, while the promised services (schools, clinics, water pumps) often have not been put in place.”
According to the report, indigenous peoples, amount about 200,000, are being relocated in South Omo and their land expropriated to make way for sugar plantations. It says: “Residents reported being moved by force, seeing their grazing lands flooded or ploughed up, and their access to the Omo River, essential for their survival and way of life, curtailed.”
“Key International Actors”
The report, which finally examines the response of international actors to the human rights crisis in Ethiopia, strongly criticizes donors. It says that donor countries and development agencies are failed to take into account the deteriorating human right situation and the brutality of the regime, and act responsibly.
The report explains: “The World Bank, for instance, approved a new Country Partnership Strategy in September that takes little account of the human rights or good governance principles that it and other development agencies say are essential for sustainable development. It also approved a third phase of the Protection of Basic Services program (PBS III) without triggering safeguards on involuntary resettlement and indigenous peoples.”
! …….. የኢትዮዽያ ፖለቲከኞች ………!
አብርሃ ደስታ (ከመቀሌ)
በኢትዮዽያ የፖለቲካ ድርጅቶች (ፓርቲዎች) ኣመሰራረት ርእዮተ ዓለም (Ideology) ወይ ሳይንሳዊ መርህ መሰረት (Principle based) ያደረገ ሳይሆን በዘረኝነት ወይ ጎሰኝነትና ጎጠኝነት የተቃኘ በመሆኑ ነው። የዚ ሁሉ ምክንያት ምንድነው?
1) የማህበረሰቡ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ማነስ ነው። በኢትዮዽያ መርህ መሰረት ያደረገ ፖለቲካ ማራመድ የህዝብ ድጋፍ ኣያስገኝም። የፖለቲካ rationality የለም። ድጋፍ ለማግኘት የጎሰኝነትና ጎጠኝነት ቅስቀሳዎች ጠቃሚ ናቸው። ‘እንደዚህ ተበደልን፣ እንዲህ ኣረጉን …’ ስትል የህዝቡን ስሜት (ወይ ቀልብ) መግዛት ትችላለህ። የተለያየ ጎሳና ጎጥ የተለያየ ፓርቲ ያመርታል። ለምሳሌ ህወሓት ድጋፍ የሚሰበስበውና ስልጣን የያዘው በዚ መንገድ ነው።
2) የኣብዛኞቹ ፖለቲከኞች ዋና ዓላማ ስልጣን መሆኑ ነው (ስልጣን መያዝና መሪ ሁኖ መከበር በቃ)። ለዚህም ጥሩ ኣማራጭ የየራሳቸው ፓርቲ በመመስረት የፓርቲው ሊቀመንበር (ፕረዚደንት) መሆን ያምራቸዋል። ለዚህም ነው በሀገራችን እነዚህ “33 የተቃዋሚ ፓርቲዎች “ የሚባሉ ጨምሮ ከ60 በላይ ፓርቲዎች ኣሉ የሚባለው።
3) የገዢው ፓርቲ ሴራዎች:: ህወሓት/ኢህኣዴግ ጥሩ ነገር በመስራት ተቃዋሚዎችን ለማሸነፍ ከመሞከር ይልቅ የመንግስትን ሃብትና መዋቅር በመጠቀም ተቃናቃኞችን በማፍረስና ማዳከም ሴራ መጠመዱ ሌላው ምክንያት ነው። በሚያደርገው በስለላ የተደገፈ conspiracy የተቃዋሚ መሪዎች (የገዢው ፓርቲ የጥፋት ስራ መሆኑ ስለማይገነዘቡ) እርስበርሳቸው እንዳይተማመኑና ኣንድነት እንዳይፈጥሩ ስለሚያደርግ ነው።
4) የፖለቲካ ፓርቲዎች የተሳሳተ የትግል ኣቅጣጫ (Game Theory)። ኣንዳንድ ፖለቲከኞች (እንዳውም ኣብዛኞቹ) የህዝብን ስሜት ለመግዛት ሲባል ዘረኝነትን የሚቃወሙ እየመሰሉ በተግባር ግን ራሳቸው ዘረኝነትን (ጎሰኝነትን) ያጠቃቸዋል። እንደውጤትም ሁሉም ዘረኛ ሁነው ይገኛሉ። ሌሎች ከነሱ ጋ ከመቀላቀል ይልቅ ከነሱ ራሳቸው ለመከላከል ሲሉ ሌላ ድርጅት መመስረት ይፈልጋሉ። ፓርቲዎችም ይበዛሉ።
ለምሳሌ
(ሀ) ኣንዳንድ ዘረኝነት ወይ ጎሰኝነትን እንቃወማለን፣ በዘር መከፋፈል ይቅር እያሉ የሚሰብኩ ኋይሎች ግንቦት -7 ከዴምህት (ዴሞክራሲያዊ ምንቅስቃስ ህዝቢ ትግራይ ወይ የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ) ኣብሮ እየተንቀሳቀሰ ነው ብለው ይከሳሉ (ይወቅሳሉ)። ይሄ ፓርቲዎች በዘር ተከፋፍለው እንዲቀሩ ያደርጋል።
(ለ) ህወሓት/ኢህኣዴግ በራሱ ጎጠኝነትን እቃወማለሁ እያለ “ዓረና ትግራይ ፓርቲ ከጠላቶቻችን ሸዋ ፖለቲከኞች በማበር የትግራይን ህዝብ ለመግደል እየተንቀሳቀሰ ነው “ በሚል ስም ያጠፋል። ታድያ ዓረና ፓርቲ ኮ ትግራይ የመገንጠል ዓላማ የለውም፤ ከሌሎች የኢትዮዽያ እህት ፓርቲዎች ይሰራል እንጂ ለብቻው መሆንኮ ኣይደገፍም። ኣብሮነት ጥሩ ነው። ዙሮዙሮ ግን ይሄም ፓርቲዎች እንዳያብሩ ምክንያት ይፈጥራል።
(ሐ) ሰመያዊ ፓርቲ የመሰረቱ ፖለቲከኞች (እንደሚባለው) የኢትዮዽያ ኣንድነት ይሰብካሉ። ዘር ወይ ጎሳ መሰረት ያደረገ ፓርቲ እንደማይደግፉም ይነገራል። እነዚህ ሰዎች ታድያ (የሰማሁት ትክክል ከሆነ ምክንያቱም እንደዚህ ዓይነት ኣስተሳሰብ ከፖለቲከኛ ኣይጠበቅም) የኣንድነት ፓርቲ ኣባላት የነበሩ ሲሆን ፓርቲው (ኣንድነት) እነሱ የማይፈልጉዋቸውን ሰዎች (እነ ስየ ኣብርሃ የትግራይ ተወላጆችን በኣባልነት ስለያዘ) ከፓርቲው ለቀው በመውጣት “ኣዲሱ”ን ሰማያዊ ፓርቲ መሰረቱ። (የፓርቲዎች ቁጥር ጨመረ)።
ይህንን መረጃ (ምሳሌ ‘ሐ’) ትክክል ከሆነ ማለትም ሰመያዊ ፓርቲ ከሌሎች ብሄሮች (ለምሳሌ ትግራይ) በኣባልነት ካልተቀበለ መጨረሻው ምን ሊሆን ነው? እንበልና ሰማያዊ ፓርቲ ስልጣን ያዘ (የኣንድ ፓርቲ ዓላማ ስልጣን መያዝ ስለሆነ) ከዛ እንዴት ኣድርጎ ሀገርን ያስተዳድራል? ወይስ ኣማራ ክልልና ኣዲስ ኣባባ ብቻ ገንጥሎ ሀገር ሊመሰርት ነው?
ጎሰኝነት ወይ ዘረኝነት ኣንቀበልም ስንል ከተለያዩ ብሄሮች በኣባልነት ኣንቀበልም ማለት ሊሆን ኣይገባውም። በኣጭሩ በኢትዮዽያ ፓርቲዎች እንደ ኣሸን የሚፈሉ ገዢ የሆነ ርእዮተ ዓለም መሰረት ያደረገ የፓርቲ ስርዓት ስለሌለ ነው።
በመጨረሻም
በኢትዮዽያ ፓርቲዎች የሚመሰረቱ በርእዮተ ዓለም ልዩነት ምክንያት ኣይደለም ካልን ታድያ የጋራ ነጥባቸው ምንድነው? በኢህኣዴግ ሙስና መሰረት ያደረጉ ጥቅማጥቅሞች ያገናኛቸዋል። የተቃዋሚ ፓርቲዎች ኣንድ የሚያደርጋቸው ነጥብ ደግሞ ገ ዢውን ፓርቲ መጥላታቸው ነው።
የመጨረሻ መጨረሻ
በመርህ የሚንቀሳቀሱ ፖለቲከኞች የሉም ማለት ግን ኣይደለም። ይኖራሉ ግን የህዝብ ተቀባይነት በቀላሉ ለማግኘት ይቸገራሉ። ስለዚ ኣናያቸውም።
የኢትዮዽያ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ሆይ፡ እባካቹ ኣንድ ጠንካራ ድርጅት ፍጠሩ። 33፣65 እየተባላቹ ኣታሳፍሩን።
It is so!!!