Category Archives: Social and Culture

አዳማ የኤድስ ተጠቂዎች ማደርያን ወደ መቅዲ ባርና ሬስቶራንት ቀየረች?!

የትነበርክ ታደለ
ይህ የምስራች እንዳይመስላችሁ! እጅግ ዘግናኝ አሳፋሪና አሳዛኝ የሀገራችን እውነታ ነው። ከአመታት በፊት ሀገር በኤች አይቪ የደረሰባትን የጭለማ ድባብ አንረሳውም! እርግጥ አሁንም ገና ከሀዘኑ ሙሉ በሙሉ አልተላቀቅንም። በዝያ የጭለማ ዘመን፣ መፍትሄ ከሀገር ውስጥም ከውጭም ሲፈለግ፣ ወጣቱ በየቦታው ሲረግፍ፣ ቤተሰብ ሲበተን አዳማ ውስጥ አንድ ሰው ተገኘ።

መስፍን ፈይሳ (የመስፍነ ፈይሳ ኢኒሼቲቭ በጎ አድራጎት መስራች)

መስፍን ፈይሳ (የመስፍነ ፈይሳ ኢኒሼቲቭ በጎ አድራጎት መስራች)

ይህ ሰው መስፍን ፈይሳ ይባላል። መስፍን ራሱም የቫይረሱ ተጠቂ መሆኑን ይፋ አውጥቶ በመናገር የሱ ቢጤ ወገኖቹን ለመርዳት ቆርጦ ተነሳ። እሱ እንደሚናገረው ማዳበርያ ከረጢት አንገቱ ላይ አስሮ በየደጃፉ እየዞረ ምግብ እየለመነ የሰበሰባቸውን ወገኖቹን መመገብ ያዘ።

እየቆየ ጥረቱ ፍሬ አፍርቶ በሀገር አቀፍ ደረጃ እውቅና የተሰጠውና ከ5000 ሰዎች በላይ የተረዱበት “መስፍን ፈይሳ ኢኒሼቲቭ በጎ አድራጎት” ተቋቋመ።

ይህ ተቋም አሁን “መቅዲ ባርና ሬስሮራንት ተብሎ ወጣቶች ቀንና ለሊት የሚጨፍሩበት፣ በሺሻ ጢስ የሚታጠኑበትና ህልማቸውን የሚነጠቁበት ቦታ ሆኗል።

ከሰአታት በፊት ግለሰቡ በፌስ ቡክ ገጹ ላይ በለቀቀው ቪዲዮ እንዳስታወቀው በጉልበት ከሀገር እንድወጣ ካደረጉኝ በኋላ ተቋሙን አፈራርሰው አራት ሚሊየን የሚገመት ንብረት ዘርፈው ጉዳተኞቹን በትነው ህንጻውን ከኤች አይቪ መከላከያነት ወደ ማሳራጫነት አዙረውታል ብሏል።

እጅግ የሚደንቀው ደግሞ ይህ ተቋም (አሁን መቅዲ ባር) የሚገኘው ከአዳማ ዩኒቨርስቲ አጠገብ መሆኑ ነው። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የተለያዩ አለማቀፍ ሚዲያዎች እንደሚዘግቡት ሀገራችን ውስጥ ዝሙት በርካሽ የሚሸጥባቸው ስፍራዎች ዩኒቨርስቲዎች ባሉበት አካባቢ ነው።

በተለይ ደግሞ አዳማ ናዝሬት በዚህ ግምባር ቀደም ተጠቃሿ ናት። አንድ የቅርብ ጊዜ መረጃ እንደሚያሳየው አዳማ 230.000 ነዋሪዎች ያላት ስትሆን ከዚህም ውስጥ ካሉት ሴቶች 5000 ዝሙት አዳሪዎች ናቸው። ይህም ማለት ከመቶ አምስት ፐርሰንቱ በዚሁ ስራ የሚተዳደሩ ናቸው። ልብ በሉ ይህ ቁጥር የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችን አይጨምርም።

እንግዲህ ይህንን አይነት ጉድ የተሸከመች ከተማ እንዴት ባለ አስተዳደር እጅ ብትወድቅ ነው የህዝብን ሁለንተናዊ ጤንነት ከመጠበቅ ሀላፊነቱ እየሸሸ በግለሰብ የተቋቋመ ተቋም ለማፈረስ የተደፈረው?

እጅግ በጣም የሚገርመው ደግሞ ይህ ተቋም ሲጀመር የመሰረት ድንጋይ የጣሉት በአሁን ሰአት የክልሉ ፕሬዚዳንት የሆኑት ኦቦ ሙክታር ከድር መሆናቸው ነው። (አቡነ ጳውሎስም በቦታው ነበሩ)

Mesfin Feyisa Initiative adama-nazereth

እና ምነው? ኦቦ ሙክታር አዳማ ውስጥ ምን እየተካሄደ ማወቅ አይችሉም ማለት ነው? ለአንድ ትልቅ አላማ ራሳቸው በቦታው ድረስ ሄደው መሰረት የጣሉለት ተቋም እጅግ በሚያሳፍርና በሚያዋርድ ሁኔታ ተሽቆልቁሎ ሲጠፋ ምንም አልሰሙም ማለት ነው? አዳማ የኦሮሚያ ዋና ከተማ ነች! ይህንን ሳይስሙና ሳያዩ ወለጋ ጫፍ ወይም አርሲ ቦረና ስላለው እንዴት ሊሰሙ ይችላሉ? ነው ወይስ በዚህ ጉዳይ ላይ የሳቸው ይሁንታ አለበት? እውነት ለመናገር መልስ ሊሰጡበት የሚገባ ጥያቄ ነው።

የአዳማ ህዝብስ ቢሆን በራሱ ጉዳይ ላይ ከሱ የተሻለ ማን ሊጠይቅለት ይችላል? ግለሰቡ እንደተናገሩት ወደዚህ ባርና ሬስቶራንት ልጆቻችሁ እየሄዱ እያያችሁ ዝም ብትሉ በልጆቻችሁ ህይወት ላይ ፈርዳችኋል።

መንግስትም ቢሆን እነ መቄዶኒያን የመሳሰሉ ወገንን ከጎዳና የሚሰበስቡ ተቋማት ነገ በተመሳሳይ መንገድ እንደማይፈርሱና ወደ ሺሻ ቤትነት እንደማይቀየሩ ምን ማስተማመኛ ይሰጠናል? ትውልድ እየጠፋ ነው! ህግ እየተጣሰ ነው! የምንፈልገውን እያጣን የማንፈልገው እየተጫነብን በዚህ ላይ ለጩሀታችን ዝምታ እየተመለሰልን ነው! ነገ አጣብቂኙ ለሀገር ነውና መቅዲ ባር በአስቸኳይ ወገኖቻችን ወደ ሚረዱበት ተቋምነት ይመለስልን! ወገን በጭፈራ ቤት አይታከምም!

በሳውዲ በተከሰው አደጋ ከ13 በላይ ኢትዮጵያውያን መሞታቸው ተገለፀ

ነብዩ ሲራክ
(ከሳውዲ ዓረቢያ)

መስከረም 13 ቀን 2008 ዓ.ም. የሐጅ ሥነ ሥርዓት ተከትሎ ሰይጣንን በድንጋይ በሚመታበት ክንዋኔ ምሳሌ፤በጀማራት ድልድይ በሚወስደው መንገድ በሀጅ ተጓዦች መካከል በመጨረሻው ሰዓት በተፈጠረ ግፊያና መጨናነቅ በተከሰተ አደጋ የሟ ቾች ቁጥር ወደ 1,100 ከፍ ያለ ሲሆን የቆሰሉት ቁጥርም ከፍተኛ መሆኑ ታውቋል፡፡ ከደረሰው አደጋ ውስጥ እስካሁን ከ13 በላይ ኢትዮጵያውያን ሲሞቱ ከ26 በላይ መቁሰላቸውን እና ከ204 በላይ መጥፋታቸውን መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡ ለሒጅ ፀሎት ስነስርዓት የተጓዙ ኢትዮጵያውያንም 8 ሺህ ያህል እንደነበሩ ተጠቁሟል፡፡

Saudi Hajaj

ባለፈው ጳጉሜ 5 ቀን 2007 ዓ.ም. በመካ ሳውዲ ዓረቢያ በደረሰው የክሬን መውደቅ አደጋ ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በርካታ ለሐጂና ፀሎት ስነስርዓት ወደስፍራው ባቀኑ ሀጃጆች ላይ ከህይወት መጥፋት እስከ አካል ማጉደል አደጋ ማድረሱ አይዘነጋም፡፡ በተለይ የመስከረም 13 ቱን አደጋ በተመለከተ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እንደሚከተለው አቅርቦታል፡፡

ኢትዮጵያ…

* ኢትዮጵያ 13 በላይ ሞተውባታል ፣ 26 ቆስለውባታል
ከ204 በላይ ጠፍተውባታል ፣ ፍለጋው ቀጥሏል
* ጅዳ ከተላለፉት ቁስለኞች ኢትዮጵያዊ የለም
* ጅዳ ማህጀር የተላለፈው ሬሳ ማንነት ገና አልተጣራም
* ከማህጀሩ ሬሳ የአፍሪካውያን አለበት ተብሏል
* ኢትዮጵያውያን መካ ላይ ለፍለጋው በግል ተደራጅተዋል
* ማፈላለጉን በሁሉም ሆስፒታሎች መከዎን ገዷቸዋል
* ቤተሰብ ወይም የኢንባሲ ውክልና አምጡ ተብለዋል
* በመካው ክሬን የተጎዳች ኢትዮጵያዊት ሀጃጅ ተገኘች
* ኢትዮጵያቷ ሀጃጅ እስከዛሬ አልታወቀችም ነበር
* ልክ የዛሬ ሳምንት መሞቷ ተጠቁሟል

ህንድና ፖኪስታን …

* በማፈላልጉ የሳውዲ መንግስት አፋጣኝ እርዳታ ተጠየቀ
* የህንድን ፖኪስታን ቆንስሎች መግለጫ ሰጥተዋል
* ህንድ 46 ሞቶባታል 62 ቆስለዋል 82 ጠፍተውባታል
* ፖኪስታን 46 ሞተውባታል ፣ 8 ቆስለዋል 42 ጠፍተውባታል

የጠፉትን ፍለጋና ጭንቅ ድካሙ

ተቀማጭነታቸውን ሳውዲ ያደረጉ ፣ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ፣ በሀጅ ጸሎት ከአደጋው የተረፉ ሀጃጆችና ቤተሰቦቻቸው በሚና ጀማራት አደጋ የጠፉና የሞቱትን ሰዎች ለማፈላለግ ሌት ከቀን ወደ ሚና ፣ ጀማራትና መካ በመመላለስ አድካሚ የጭንቅ ሳምንት መግፋታቸውን በመግለጽ ላይ ናቸው። የጠፉ ሃጅ ቤተሰቦች በግሩኘና በተናጠል ቢያፈላልጉም በርካታዎች እንዳልተሳካላቸው ይናገራሉ ። በአደጋው የሞቱ ኢትዮጵያውያን ቁጠር ገና ከአደጋ ቀን አንስቶ ከአምስት በላይ መሆኑ ግልጽ እያለ በኢትዮጵያ ኢንባሲ ፣ ቆንስልና የሀጅ ኮሚቴ የሚደረገው ፍለጋ የተቀናጀ ባለመሆኑ ዝርዝር መረጃው ቀርቶ የሞቱና የቆሰሉትን ዙሪያ ትክክለኛ መረጃ አልቀረበም ነበር ። ከብዙ ጉትጎታ በኋላም ትክክለኛውን መረጃ ለህዝብ ለማድረስ በርካታ ቀናት ወስዷል።
አሁንም በኢትዮጵያ ተወካዮች በኩል ቀናት የወሰደው የሞቱና የቆሰሉትን የማሳወቅ መረጃ ቅበላ ከቀናት በፊት ይፋ ቢደረግም አሁንም ቁጥሩ እየጨመረ ከመጣው የሟቾቸ ብዛት አንጻር የመረጃ ክምችቱን የማሻሻል ስራ እየተሰራ አይደለም በሚል ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ የመካና ጅዳ ነዋሪዎች ገልጸውልኛል፡፡

ኢትዮጵያን ወጣቶች በመካ ሚናው ፍለጋ

የሀጅ ኮሚቴ አካሄድ አዝጋሚ መሆን ያሳሰባቸው በመካ ዙሪያ የሚገኙ ወጣቶች ራሳቸውን በማደራጀት መካ ላይ በሚገኙ በ13 ሆስፒታሎች በአደጋው የተጎዱትን ለማግኘት ፍለጋ ጀምረዋል ። በትናንሽ ሆስፒታሎች ችግር ባይገጣማቸውም መሊክ ፈይሰል ፣ ሄራ ፣ ጀበለር ኑርና መሊክ አብደላ በተባሉ ትላልቅ ሆስፒታሎች እንዳይገቡ ተከልክለዋል ። ያም ቢሆን በቀሩት አንዳንድ ሆስፒታሎች ማፈላለጉን በተወሰነ መልኩ በማሳለጥ 15 ያህል ቁስለኞችን ማግኘታቸውን ጠቁመውኛል። መሊክ ፈይሰል ፣ ሄራ ፣ ጀበለር ኑርና መሊክ አብደላ በተባሉ ትላልቅ ሆስፒታል ሃላፊዎች “የቤተሰብ ወይም የኢንባሲ ውክልና አምጡ !” በማለት አንደከለከሏቸው ወጣቶች አጫውተ ኛል። ይህንን ችግር እንዳጋጠኛቸው ያጋጠማቸውን ለሀጅ ኮሚቴ በመጠቆም ተቀራርበው ለመስራት መሞከራቸው የገለጹልኝ የአፈላላጊ ቡድኑ አባላት አብሮ የመስራት ሙከራውም አለመሳካቱን ገልጸውልኛል! “ከጅዳ ለመጡ ኮሚቴ ነን ” ላሉን ሰዎች በሀጅ ኮሚቴ ወይም በጅዳ ቆንስሉ በኩል ውክልናውን ወይም መታወቂያ ቢሰጠን ብለን ጠይቀን ነበር ያሉኝ አንድ ወጣት በበኩላቸው ” መጣዎቂያ ይሰጣቹሃል!” የሚል ቃል ቢገባላቸውም እስካሁን ከኮሚቴውም ሆነ ከሌላ ወገን መልስ ባለ መሰጠቱ ጥረታቸው መሰናክል እንደገጠመው ገልጸውልኛል፡፡

በአንጻሩ የተመሳሳይ ችግር ያለባቸው የአንዳንድ ሀገራት የመንግስት ተወካዮችና ዲፕሎማቶች እንኳንስ ነዋሪው ተደራጅቶ መጥቶ ነዋሪዉን ለበጎ ስራና በማቀናጀትና በማቀዳጀት በሽዎች የሚቆጠሩ ልዩ የጠፉ ሃጃጆችን አፈላላ ግብረ ሃይል አቋቁመው በመካ ፣ ሚናና ጀናራት ማሰማራታቸው ይጠቀሳል ። የነዋሪውንና የሀጃጆችን ጭንቀት በመረዳትም የቆሰሉትንና የሞቱትን ፎቶ መረጃዎች ከሳውዲ መንግስት በመውሰድ ለዜጎቻቸው አቅርበዋል።

የመካ ወጣቶች በፍለጋው እንደ “አሳ ጎርጓሪ …”

አበው ” አሳ ጎርጓሪ…” የእኒሁ በመካ ዙሪያ ያሉ ወጣቶች በሚና ጀማራት የተጎዱ ሰዎችን ሲያፈላልጉ በመካው ክሬን ተጎድታ የሞተች ኢትዮጵያቷ ሀጃጅ ማግኘታቸው ታውቋል። እስከ ዛሬ የሀጅ ኮሚቴም ሆን የጅዳ ቆንስል ምንም መረጃ ስለሌላቸው ማንም ሳይደርስባት መሞታን ገልጸውልኛል። ይህችው ኢትዮጵያዊት ሃጃጅ በጉዳቱ በከባድ ቆስላ በህክምና ስትረዳ ከቆየች በኋላ ባሳለፍነው ሳምንት በተከበረው የኢድ አል አድሃ እለት ህይዎቷ ማለፉን ከዶክተሮች እንደተገለጸላቸው ሬሳውን አየሁ ያለ ጎልማሳ አስረድቶኛል። እኔም ጉዳዩን በተዘዋዋሪ መንገድ ለማጣራት ባደረግኩት ሙከራ የተባለችው እህት ሬሳ በሆስፒታሉ የሬሳ ክፍል እንደሚገኝ ማረጋገጥ ችያለሁ! በዚህች ሟች ሀጃጅ ዙሪያ የደረሰኝ መረጃ ለሃጅ ኮሚቴና ለጅዳ ቆንስል በተመሳሳይ ሁኔታ መቅረቡን አረጋግጫለሁ፡፡

ሀጃጆችን ፍለጋ በጅዳ ሆስፒታሎች

አደጋው ከደረሰ በኋላ ባሉት ቀናት የተጎጅዎች ቁጥር ከፍ እያለ በመምጣጡ ወደ 200 የሚጠጉ ቁስለኞች ወደ ጅዳ መተላለፋቸው ይታወሳል ። ይህንኑ ተከትሎ የጅዳ ቆንስል በሳምንቱ መጀመሪያ ዲፕሎማቶችን ከተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ጋር በቡድን በማሰማራት ፍለጋ ጀምረው ነበር ። በዚሁ ፍለጋ ከተጋበዙት መካከል የሴቶች ማህበርና የጅዳ ኮሚኒቲ የሚገኙበት ሲሆን የሴቶች ማህበር አባላት ሲሳተፉ የጅዳ ኮሚኒቲ ግን በፍለጋው አልተሳተፈም ። ለሁለት ቀናት በተደረገው ፍለጋ አንድም ኡትዮጵያዊ አልተገኘም።

የተደረገው ፍለጋ ጅዳ ማህጀር የሚገኘውን የሬሳ ማቆያ ያካተተ ቢሆንም ወደ ማቆያው የተላለፈው ሬሳ ማንነት ገና ባለመጣራቱ መረጃ ማግኘት እንዳልተቻለ የጅዳ ቆንሰል ባወጣው መረጃ ጠቁሟል ። እስከ ዛሬ ረፋድ በዚሁ ሬሳ ማቆያ ተጨማሪ ሬሳዎች መግባታቸው ሲረጋገት ወደ ማህጀሩ ማቆያ አፍሪካውያን ሬሳ እንደሚኖርበት ተገምታል።

ሞተው መለየት ያልቻሉትን የማጣራቱ ስራ

በሳምንት የአደጋው አድሜ በዋናነት አሳሳቢ የሆነው ቁርጡ የታወቀው የሞቱትና የቆሰሉት ዜጎች አልሆነም። ሞተው ፎቷቸውና ቆሰለውም ከሆነ ዝርዝራቸው ያልተገኙት ጉዳይ ብዙ ዜጎችን በመንፈስ እያስጨነቀና እያንገላታ ይገኛል። መዳረሻቸው ” ጠፋ” ከሚባሉት መካከል በደረሰው አደጋ ፊታቸው መለየት ያስቸገረ ይገኙበታል የሚል ጥርጣሬ ቢኖርም የሟቾችን ሬሳ ለመለየት የተለያዩ እርንጃዎች ቀርበዋል። ሀጃጆች በገቡበት አሻራ ለመለየት እየተወሰደ ያለው ማጣራት ረዠም ጊዜ መውሰዱ ተቃውሞ እየቀረበበት መሆኑ ይጠቀሳል ። የሳውዲ መንግስት የየጤና ጥበቃና የፖስፖርት ክፍል ኃላፊዎች ስለመለየቱ ስራ ሲናገሩ በሶስት መንገድ እንደሚከወን ያስረዳሉ ። እስካሁን መለየት ያልተቻለውን ሬሳ ለመለየት የቀረቡት ዘዴዎችም 1ኛ / በገቡበት አሻራ 2ኛ / በገቡበት ፎቶ መለየት እና 3ኛው / የስጋ ዘመድ ቤተሰቦቻቸው እየቀረቡ DNA በመስጠት መለየቱ እንደሚከወን ይናገራሉ ! አሻራቸው የተነሱ ሬሳዎች ውጤት በከነገ ጀምሮ ይፋ ይደረጋል ተብሎ ቢጠበቅም የተረጋገጠ መረጃ እስካሁን አላገኘሁም፡፡

የሟቾች ቁጥር ማሻቀብ

የሚና አረፋት አደጋ ከተከሰተ ሰባተኛ ቀኑን የደፈነ ቢሆንም በመቶዎች የሚቆጠሩ የተለያዩ ዜጎች መዳረሻ እስካሁን ሊታወቅ አልቻለም ። ካሳለፍነው ሳምንት ጀምሮ በማህበራዊ መገናኛ መረቦች እስከ ታዋቂ መገናኛ ብዙሀን የዜና አውታሮች የጠፉና ያልተገኙት ዜጎች ጉዳይ አሳሳቢ እንደሂነ ቀጥሏል! ምንም እንኳን የሳውዲ መንግስት የሚቱትን ቁጥር ከ 769 ፈቀቅ ባያደርገውም ሞተየ ተብለው ፎቷቸው የተለጠፉት ቁጥር ከ1500 በላይ እየሆነ መጥቷል። የመንግስት ሃላፊዎች መሞታቸው ተረጋግጦ ፎቷቸው የሚለጠፉት ቁጥር እያደር አሳሳቢ ሆኗል። ለምን ቁጥሩ አደገ ተብለው ሲጠየቁ ” በፎቶው የተካተቱት ሀጅ ከተጀመረ ወዲህ በልብ ድካምና በተለያዩ አደጋዎች የሞቱት ከአደጋው ጊዜ ሰለባዎችን ጭምር ነው “ቢሉም የቁጥሩ በአፋጣኝ ማፈግ ብዙዎቹን አሳስቧል።

የህንድና ፖኪስታን ተሞክሮ

የሳውዲ መንግስት የጠፉትን በማፈላለግ ሂደቱን እንዲያፋጥንና የዜጎቻቸው እጣ ፈንታ እንዲያሳውቅ አጥብቀው እየጎተጎቱን ካሉት ሃገራት ዲፕሎማቶች መካከል ህንድና ፖኪስታን የሳውዲ መንግስት አስቸኳይ ጥሪና ተማጽኗቸውን በማቅረብ ላይ ናቸው፡፡

የፓኪስታን አምባሳደር መብዙር አለ ሀቅ እና ቆንስል ጀኔራል አፍታብ አህመድ በተገኙበት ሳውዲ የሀጅና ኡምራ ሚኒስትር በድር ሀጃር ጋር ምክክር ያደረጉት የፖኪስታን የሀይማኖት ጉዳዮች ተወካይ ሳድር መሀመድ በጠፉት ፣ በቆሰሉትና በሞቱት ፖኪስታን ሃጃጆች ዙሪያ መንግስታቸ ው አፋጣኝ መፍትሔ እንዲሰጣቸው የሚኒስትሩን አሳስበዋል ። በአደጋው 46 የሞቱባት ፣ 8 የቆሰለባት እና 42 የጠፉባት ፖኪስታን የሀይማኖት ጉዳይ ተወካይ ሳድር መሀመድ ከሳውዲ ሃጅ ሚኒስትሩ ጋር ባደረጉት ውይይት በሚና ጀማራት አደጋ የቆሰሉት ፣ ሞተው ማንነታቸው ተጣርቶ ባልተነገረ ዜጎቻቸው ዙሪያ ጉዳይ ፖኪስታናውያን ን በእጅጉ ማሳሰቡን ገልጸው አስቸኳይ መፍትሔ እንደሚሹ ለሃላፊው በአጽንኦ አስታውቀዋል። በተለይም መዳረሻቸው የጠፉ ዜጎቻቸው ጉዳይ የሚወዷቸው ቤተሰቦች የጠፉባቸው ቤተሰቦችን በጣም ያጨናነቀ መሆኑን ጠቁመው የሳውዲ መንግስት ምለሽ እንዲሰጣቸው ተማጽኗቸውን አቅርበዋል፡፡

በአደጋው 46 በሞት ያጣችው 62 የቆስለባትና 82 የጠፉባት ህንድ ዲፕሎማቶች በበኩላቸው የሀጃጅ ዜጎቻቸው ጉዳይ ዜጎቹና መንግስትን እንቅልፍ እንደነሳቸው አሳስበዋል ። በጅዳ የሚገኘው የህንድ በቆንስል መስሪያ ቤቷ የጉዳዩን አሳሳቢነት ለሳውዲ መንግስት ለመሳሰብ ትናንት ሮብ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል። መግለጫውን በዋናነት የሰጡት የህንድ ሀጅ ኮሚቴ ዋና ኃላፊ መሀቡባ ሙፍቲ የመሩት ሲሆን ስጋራቸውንና የጠፉ ቤተሰብ አባላት ጉዳይ መጣራት መጓተት መንግስታቸውን እንዳሳሰበው በመጠቆም አስቸኳይ መፍትሔ ይፈለግ ዘንድ የሳውዲን መንግስት አሳስበዋል፡፡

የታክሲዎች ፖለቲካ

ጌታቸው ሺፈራው

ታክሲ ውስጥ በብዛት ከሚፃፉት ጥቅሶችም በላይ አንዳንዴ ታክሲ ውስጥ ካሉት ሰዎች ጣል የሚደረጉት የምሬት አሊያም ሌሎች የፖለቲካ ወጎች የማህበረሰቡን አመለካከት በግልፅ ያሳያሉ፡፡ መጀመሪያ ከጎናቸው ያለውን ሰው የሚጠራጠሩት ተሳፋሪዎች ሁኔታውን አይተው ብሶታቸውን ያወራሉ፡፡ አንዳንዶቹ ወሬ የሚያስጀምር ሳያስፈልጋቸው በከተማው የሚታዘቡትን በግልፅ ይቃወማሉ፡፡ ስርዓቱን የሚደግፉ፣ የሚያስመስሉም እንደሚገኙበት ሁሉ፡፡

tavxi politics

ዛሬ ያጋጠመኝ ግን ትንታኔ ነው፡፡ በቀልድም ቢሆን ደንበኛ የፖለቲካ ትንታኔ፡፡ ህዝቡ ፖለቲካን በደንብ እንደሚከታተልና እንደሚረዳ የሚያሳይ ትንታኔ ነው፡፡ በየ ሰዓቱ የሚነገረውን ፕሮፖጋንዳ ህዝብ ገልብጦ እንደሚያነበው የሚያሳይ አጋጣሚ፡፡

ከአራት ኪሎ ወደ ስድስት ኪሎ ከዛም ወደ ፈረንሳይ እየሄድን ነው፡፡ የፈረንሳይ ህዝብ ‹‹በወንበር›› የሚጫነው ከአራት ኪሎ እስከ ስድስት ኪሎ ብቻ ነው፡፡ ከዛ በኋላ ከሰው ላይ ሰው ይደራረብበታል፡፡ ሰው እንደ ሽንኩርት ነው የሚጭኑት፡፡ ታክሲው እስከ አፍ ጢሙ ሞልቶ ‹‹ሁለት ሰው የቀረው›› እያለ የሚጠራን አንድ የታክሲ ረዳት ለቀልድ ‹‹ለምን ከላይ አትጭንም?›› ብዬው ‹‹ቢፈቀድ እንዴት አሪፍ ነበር መሰለህ! ጥሩ ሀሳብ ነበር›› ብሎኛል፡፡ ሰውን እንደበግ አስሮ ጭኖ ብር ከሀምሳ ሊያስከፍል!

አብዛኛዎቹ ረዳቶች በግድ ነው አጠጋግተው የሚጭኑት፡፡ ካልሆነ አልጠጋም ያለውን ‹‹ውረድ!›› ለማለትም ይዳዳቸዋል፡፡ ዛሬ የመጣንበት ታክሲ ረዳት ግን ተጫዋች ነው፡፡ ያስቃል እንጅ አያስገድድም፡፡ ‹‹ተጠጉ›› ሲልም እያባበለና በቀልድ ነው፡፡ ስድስት ኪሎ ስንደርስ ተሰብስቦ ታክሲ የሚጠብቀውን ሰው ‹‹ፈረንሳይ ፈረንሳይ!›› ብሎ የታክሲውን መዳረሻ ካሳወቀው በኋላ ‹‹ይኸው ቤታችሁ ነው ግቡ፡፡ ለሁላችሁም ይበቃል፡፡ ዋናው ፍቅር ነው!›› እያለ ጎረምሳ የ70 አመት ሽማግሌ፣ ነፍሰ ጥሩ ሴትና ህፃናት ጋር ሲጋፋ ፈንጠር ብሎ ይታዘባል፡፡ ምን አልባት ሊያሳዝነውም፣ ሊያስደስተውም ይችላል፡፡ ለምዶት ምንም ላይመስለው ይችላል፡፡ አብዛኛው ሰው ተገፍትሮም፣ ቦታ አይኖርም ብሎ ተስፋ ቆርጦም ተመልሷል፡፡ ቦታ ይኖራል ብለው ታክሲው በር ላይ ቆመው የቆዩት ሰዎች ቦታ እንደሌለ አውቀው ወደ ኋላ ሲመለሱ እሱ ወደ ታክሲው በር ተጠጋ፡፡ መቀመጫ አጥተው መተላለፊያው ላይ አጎንብሰው የቆሙ መንገደኞች አሉ፡፡ ታክሲዋ ወስጥ በግምት ከ19- 20 ያህል ሰዎች ተጠጋግተው ተቀምጠዋል፡፡ እድል የቀናቸውም አአንዳሚው ወንበር ላይም ተደርድረዋል፡፡ ያን ያህል ተጋፍቶ ወንበር ማግኘት ደስታ የሚፈጥርባቸው አሉ፡፡ በግፊያው ወቅት በነበረው ትይንት የሚስቀም፣ የሚናደደም አለ፡፡ እንዲህም ሆኖ ሶስት ያህል ሰዎችጠባቧ መተላለፊያ ላይ በሰው ተጣብቀው ‹‹ቆመው›› ቦታ እየፈለጉ ነው፡፡
የታክሲው ሚኒስቴር ዴኤታ (ረዳቱ) ቦታ እንደሌለ ቢያውቅም ‹‹ተጠጉላቸው፡፡ ተጠጉላቸው እንጅ!›› እያለ ያባብላል፡፡ ሁለቱ ወንበሮች ሶስት ሶስት ሰው ይዘዋል፡፡ አግዳሚው ወንበርም ሞልቷል፡፡ ሶስቱ ሰዎች አሁንም አልወረዱም፡፡ የታክሲ ሚንስቴር ዴኤታም ‹‹ኧረ ተጠጉ!›› ቢል የሚሰማው አላገኘም፡፡ ቦታ የለማ! እሱ እራሱኮ ቦታ ስለሌለ አልገባም፡፡ አንዱ ወረደ፡፡ ሁለቱ ተስፋ አልቆረጡም፡፡ ረዳቱን ታስፋ አድርገው እንጅ ቦታ እንደሌለስ አይተዋል፡፡

አሁን ረዳቱ ቢያንስ ለመቆሚያ ቦታ አግኝቷል፡፡ ከበሩ ትንሽ ወደ ታክሲው ገብቶ ‹‹ቤታችሁ ነው፡፡ ቆማችሁም ቢሆን ትሄዳላችሁ፡፡›› ይላቸዋል ሁለቱን መንገደኞች፡፡ ግን ማባበሉንም አላቆመም፡፡ ‹‹ተጠጉላቸው! ወገን ተጠጉላቸው! እነሱም እንደኛው መሄድ ይፈልጋሉ፡፡ የሀገራችን ሰዎች ናቸውኮ፡፡ አቅፈንም ቢሆን እንወስዳቸዋለን፡፡ ቻይና እንኳን በታክሲያችን ይሄድ የለ፡፡ ያው በሳምንት የሚፈራርስ መንገድ ቢሰራም ….›› እሱ የተናገረውን ሁሉ ለመያዝ ከባድ ነው፡፡ አብዛኛውን ጊዜ እሱ በላይ በላይ ስለሚናገር ከማዳመጥ በሳቅ ነው ያሳለፍነው፡፡ አሁን ቦታ እንደሌለ እሱም አውቋል፡፡ ግን ቀልዱን ቀጥሏል፡፡ እየሳኩም ቢሆን አንዱ ቀልዱ ግን ትንተና ሆነብኝ፡፡ ሳቄን አስቆመኝ፡፡ አስገረመኝ!

Taxi-Politics Ethiopia

ሰው መጠጋት ተስኖታል፡፡ የት ይሄዳል? እየቀለደ የሚጭነው ልጅ ግን በዛው ፖለቲካም ያወራል፡፡ ሰው አልጠጋለት ሲል ‹‹ተጠጉላቸው! ተጠጉላቸው እንጅ! ያው ከዚህ ሀገር መጠጋጋት እንጅ መተካካት የሚባል ነገር የለም፡፡ ተጠጉላቸው….›› ብሎ ሰውን ከታክሲዋ ጣራ በላይ አሳቀው፡፡ ግሩም ትንታኔ ነው፡፡ ‹‹ምሁራን›› በ10ና በ20 ገፅ ‹‹ጥናታዊ ፅሁፍ›› ሲገልፁት ያልሰማሁት ትንታኔ፡፡

እውነቱን ነው፡፡ መጠጋጋት እንጅ መተካካት የሚባል ነገር ብዙም አይታይም፡፡ እኔን የገረመኝ የእሱ ቀልድና ትንታኔ ብቻ አይደለም፡፡ የሰው ሳቅ ጭምር እንጅ፡፡ የታፈነው ህዝብ የሚቀልድለት ወይንም የሚናገርለት ሲያገኝ ፍርስ እስኪል ይስቃል፡፡ የሚፈራራው፣ የሚጠራጠረው መንገደኛ አይን ገላጭ ሲያገኝ ከጎኑ ምን እንዳለም ጭምር ይረሳዋል፡፡ በሬዲዮና በቴሊቪዥን ስለ መተካካት ብዙ ቢወራም ከልቡ አልገባም፡፡ ምክንያቱም ህዝቡ በውል የሚያውቀው መጠጋጋትን እንጅ መተካካት የሚባል ነገር እንደሌለ ነው፡፡ ታክሲም ውስጥ በፖለቲካውም!

ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖት ተፈታ

በየመን ሁቲ አማጽያን እጅ ለእስር ተዳርጎ የነበረው ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖት ከእስር ተፈትቶ ከቤተሰቡ ጋር ተቀላቅሏል። ጋዜጠኛ ግሩም ተክለኃይማኖት የታሰረበት ምክንያት ይደግፈው በነበረ አንድ ስደተኛ ኢትዮጵያዊ ጥቆማ ሲሆን ” በስደተኛው ስም እርዳታ ይሰበስባል ፣ ስለየመን የተለያዩ መረጃዎችም ወደ ውጭ ያቀብላል ” የሚል ክስ ተመስርቶበት ነበር ።

ጋዜጠኛ ግሩም ተ/ኃይማኖት ከልጁ ጋር

ጋዜጠኛ ግሩም ተ/ኃይማኖት ከልጁ ጋር

ጉዳዩን ያጣራው ፖሊስ በቀረበው ክስ ዙሪያ ጭብጥ መረጃ ማስረጃ በማጣቱ ግሩም በነጻ ተለቋል ። ከዚሁ ጋር በተያያዘ የከሳሽ ምስክር ሆነው የቀረቡት አብዛኛው ምስክሮች ” እውነትን በጥቅም አንለውጥም ” በሚል ከሳሽን በመክዳት ወደ ህሊናቸው መመላሳቸው ታውቋል ።

Ethiopian Pastor, Translator and two others Charged With Terrorism

By Felix Horne

The charging of Pastor Omot Agwa, World Bank Inspection Panel translator and two others under Ethiopia’s anti-terrorism Law. The charges focus around their attendance at a food security workshop in Nairobi put on by several well-known organizations. The charges are absurd, even by Ethiopian standards. The second man was charged largely based on producing a research paper that was intended to be presented at the workshop. It was entitled “Deforestation, Dis-Possession and Displacement of Gambela in General and Majang People in particular.”

Pastor Omot Agwa was charged by Ethiopian authorities under the anti-terrorism law after being detained for nearly six months.

Pastor Omot Agwa was charged by Ethiopian authorities under the anti-terrorism law after being detained for nearly six months.

Here is detail press release as follow;

Ethiopia: World Bank Translator, Activists Face Trial
Activists Heading for Food Workshop Charged With Terrorism

Ethiopian authorities should immediately drop all charges and release a former World Bank translator and two other local activists charged under Ethiopia’s repressive counterterrorism law after trying to attend a workshop on food security in Nairobi, six international development and human rights groups said today.

On September 7, 2015, the authorities charged Pastor Omot Agwa, Ashinie Astin, and Jamal Oumar Hojele under the counterterrorism law after detaining them for nearly six months. The charge sheet refers to the food security workshop, which was organized by an indigenous rights group and two international organizations, as a “terrorist group meeting.” The three were arrested on March 15 with four others while end route to the workshop in Nairobi, Kenya. Three were released without charge on April 24, and a fourth on June 26.

“Ethiopia should be encouraging debate about its development and food security challenges, not charging people with terrorism for attending a workshop organized by respected international organizations,” said Miges Baumann, deputy director at Bread for All. “These absurd charges should be dropped immediately.”

Omot, of the evangelical Mekane Yesus church in Ethiopia’s Gambella region, was an interpreter for the World Bank Inspection Panel’s 2014 investigation of a complaint by the Anuak indigenous people alleging widespread forced displacement and other serious human rights violations in relation to a World Bank project in Gambella. He had raised concerns with workshop organizers about increasing threats from Ethiopian security officials in the weeks before his arrest.

The food security workshop in Nairobi was organized by Bread for All, with the support of the Anywaa Survival Organisation (ASO) and GRAIN. Bread for All is the Development Service of the Protestant Churches in Switzerland. ASO is a London-based registered charity that seeks to support the rights of indigenous peoples in southwest Ethiopia. GRAIN is a small international nonprofit organization based in Barcelona, Spain that received the 2011 Right Livelihood Award at the Swedish Parliament for its “worldwide work to protect the livelihoods and rights of farming communities.”

The objective of the Nairobi workshop was to exchange “experience and information among different indigenous communities from Ethiopia and experts from international groups around food security challenges.” Participants from Ethiopia were selected by ASO based on their experience in supporting local communities to ensure their food security and access to land.

The charge sheet accuses Omot of being the co-founder and leader of the Gambella People’s Liberation Movement (GPLM) and communicating with its leaders abroad, including ASO Director Nyikaw Ochalla, who is described in the charge sheet as GPLM’s London-based “senior group terrorist leader.” Omot faces between 20 years and life in prison. Ashinie is accused of participating in the GPLM, including communicating with Nyikaw and preparing a research document entitled “Deforestation, dispossession and displacement of Gambela in general and Majang people in particular.” Jamal Oumar is accused of being a participant of a “terrorist group” and of organizing recruits to attend the Nairobi workshop.

The GPLM is not among the five organizations that the Ethiopian parliament has designated terrorist groups. It is an ethnic Anuak organization that fought alongside the Tigrayan People’s Liberation Front (TPLF) to oust the repressive Derg regime in the 1990s, and was folded into the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) power structure in 1998. Currently the GPLM has no public profile, no known leadership structure, and has not made any public statement of its goals.
“For the government to make criminal allegations against me because I assisted in coordinating a workshop about land and food issues in Ethiopia is simply incredible,” said Nyikaw Ochalla, ASO executive director. “Trying to give indigenous people a voice about their most precious resources – their land and their food – is not terrorism, it’s a critical part of any sustainable development strategy.”

All three detainees were recently moved to Kalinto prison, on the outskirts of the capital, Addis Ababa, after spending more than five months in Maekelawi, the Federal Police Crime Investigation Sector in the city. Human Rights Watch and other organizations have documented torture and other ill-treatment at Maekelawi. Omot, and possibly the other two, were held in solitary confinement for three weeks upon their arrest, and all have had limited access to family members. Jamal and Omot have reportedly been in poor health.

The detainees were held 161 days without charge, well beyond the four months allowed under Ethiopia’s Anti-Terrorism Proclamation, a period in violation of international human rights standards and among the longest permitted by law in the world. The next hearing in the case is scheduled for October 22, 2015.

Since 2011, Ethiopia’s counter-terrorism law has been used to prosecute journalists, bloggers, opposition politicians, and peaceful protesters. Many have been accused without compelling evidence of association with banned opposition groups.

In August 2015, 18 leaders of protests by the country’s Muslim community were convicted and sentenced to between 7 and 22 years in prison. The ongoing trial of the members of a group called Zone 9 bloggers has been adjourned 36 times.

Human Rights Watch and other organizations have documented numerous incidents in which individuals critical of Ethiopia’s development programs have been detained and harassed, and often mistreated in detention. Journalists have been harassed for writing articles critical of the country’s development policy.

“These three men are the latest victims of the Ethiopian government’s crackdown on independent activists,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director at Human Rights Watch. “The arrests, lengthy detentions, and spurious terrorism charges bear all the hallmarks of Ethiopia’s effort to silence critical voices.”

Case of Pastor Omot Agwa

In February 2014, Omot acted as interpreter and facilitator for the World Bank Inspection Panel during its visit to Gambella to investigate a complaint brought by former Gambella residents concerning the bank’s Protection of Basic Services (PBS) program. The program funded block grants to regional governments, including paying salaries of government officials.

The former residents alleged that the program was harming them by contributing to the government’s abusive “villagization” program. The program forcibly evicted indigenous and other marginalized peoples from their traditional lands and relocated them to new villages. In its report to the World Bank board of directors, which was leaked to the media in December 2014, the Inspection Panel concluded that the bank had violated some of its own policies in Ethiopia.

In February 2015, the World Bank board considered the Inspection Panel’s recommendations. Shortly thereafter, Omot reported that he was under increasing pressure from Ethiopian security personnel. While the Inspection Panel had not disclosed Omot’s identity in its report, it included a photograph of him with other community members, which was removed from subsequent versions. The week before his arrest, several people told Omot that a well-known federal security official from Gambella was looking for him.

On March 15, Omot texted an emergency contact that security officials at Addis Ababa’s international airport had detained him and the six others as they were heading for the workshop in Nairobi. Several days later, a witness saw four armed federal police officers and four plainclothes security officials take Omot, in chains, to his house in Addis Ababa, where they removed computers, cameras, and other documents.

The seizure of Omot’s computers and other materials raises concerns about the security of other Gambella community members the Inspection Panel interviewed. Given the severe restrictions on human rights investigation and reporting in Ethiopia, it is virtually impossible for rights groups to learn about reprisals in the villages the Inspection Panel visited.

Within days of Omot’s arrest, Human Rights Watch and other organizations alerted the World Bank Group president, Jim Yong Kim, and the European Union, United States, and Swiss missions in Addis Ababa. But on March 31, the World Bank board approved a new US$350 million agriculture project in Ethiopia. On September 15, the World Bank approved a $600 million Enhancing Shared Prosperity through Equitable Services project, which is replacing one of the subprograms of the PBS program.
World Bank staff assert that they have privately raised the case with Ethiopian government officials, but the nature of any communications is unclear. In a May meeting with nongovernmental organizations in Washington, DC, World Bank staff said that the government had informed them that Omot’s arrest was in accordance with Ethiopian law and unrelated to the bank’s accountability process.

The organizations seeking this press release of Omot, Ashine, and Jamal are:

Human Rights Watch
Bread for All
GRAIN
Anywaa Survival Organization
Oakland Institute
Inclusive Development International
Source: https://www.hrw.org/news/2015/09/21/ethiopia-world-bank-translator-activists-face-trial