እነ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱና ንግስት ይርጋ ክሳቸው ተቋርጦ ፤ እነ ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ እና አሳምነው ጽጌ በይቅርታ እንዲፈቱ መወሰኑ ተገለፀ
(ዳጉ ሚዲያ) ከወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ህዝባዊ ተቃውሞ በእስር ላይ ከነበሩት ሰዎች መካከል ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ፥ አቶ ጌታቸው አደመ፥ አቶ አታላይ ዛፌ፥አቶ ተሻገር ወልደሚካኤል እና ንግስት ይርጋ ጨምሮ የ 101 እስረኞቸ ክሳቸው እንዲቋረጥ መደረጉን ለመንግሥት ቅርበት ያላቸው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እና ወ/ት ንግስት ይርጋ
ክሳቸው እንዲቋረጥ ከተወሰነላቸው እስረኞች መካከል 56 በግንቦት ሰባት፥ 41 እንዲሁም ከኦነግ ጋር ተባብራችኋል በሚል ክስ የተመሰረተባቸው ነበሩ።
ብ/ጄነራል ተፈራ ማሞ እና ብ/ጄነራል አሳምነው ጽጌ
በተያያዘ ዜና፤ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የሚል ክስን ጨምሮ በተለያየ ጉዳይ ተከሰው የተፈረደባቸውና በይቅርታ ከእስር እንዲለቀቁ ከተወሰነላቸው መካከል ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞና ብርጋዴር ጀነራል አሳምነው ጽጌን እንደሚገኙብት ተጠቁሟል።