Tag Archives: Ethiopian Protest

በኢትዮጵያ የፖለቲካ ውጥረት ተባብሷል፤ መንግሥት በሰላማዊ ዜጎች ላይ እወሰደ ያለው የኃይል ርምጃም ቀጥሏል

(ዳጉ ሚዲያ) የኢትዮጵያ መንግሥት ሀገሪቱን በመደበኛው ህግ ስርዓት ፀጥታ መጠበቅም ሆነ ማስጠበቅ አልቻልኩም በማለት ከባለፈው የካቲት 9 ቀን 2010 ዓ ም ጀምሮ ለ6 ወራት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ህግ ተግባራዊ አድርጓል። ይሁን እንጂ አርብ የካቲት 23 ቀን 2010 ዓ ም በተደረገው ድንገተኛ የአስችኳይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ አዋጁ በአወዛጋቢ ሁኔታ መፅደቁን ፓርላማው አስታውቋል።

አፈ ጉባዔው አቶ አባዱላ ገመዳ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይፋ እንዳደረጉት ከሆነ 547 መቀመጫ ካሉት የፓርላማው አባላት መካከል 8ቱ በህይወት እንደሌሉ በመግለፅ፤ ቀሪዎቹ “539” የፓርላማ አባላት እንዳሉ አስታውቀዋል። ከነዚህ ውስጥ አዋጁ በህገ መንግሥቱ ድንጋጌ መሰረት እንዲፀድቅ ከፓርላማው 2/3 ኛ ድምፅ ድጋፍ ማግኘት እንዳለበት በመጠቆም፥ አዋጁን ለማፅደቅ 2/3ኛ ድምፅ 339 ድምፅ ብቻ እንደሚያስፈልግ፥ የተሰጠው የድጋፍ ድምፅ ግን 346 እንደሆነና ይህም ከሚጠበቀው በላይ ድምፅ ድጋፍ እንደተገኘ፥ በ88 ተቃውሞ እና በ7 ድምፀ ተዓቅቦ አዋጁ መፅደቁን አስታውቀው ነበር። ይሁን እንጂ አፈ ጉባዔው በርካታ የተሳሳቱ መረጃዎችን ለፓርላማ አባላቱና ለህዝቡ እንደገለፁ በዕለቱ የወጡ መረጃዎች አመልክተዋል።

በአፈ ጉባዔው ከተላለፉአት የሐሰት መረጃዎች መካከል በዕለቱ በፓርላማ የተገኙ አባላት ቁጥር 539 ሳይሆን 441 እንደሆነ የፓርላማው ህዝብ ግንኙነት ክፍል ወዲያውኑ በድህረ ገፁ በሰጠው እርማት ያጋለጠ ሲሆን፤ በዕለቱ የኦህዴድ/ኢህአዴግ ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር አብይ አህመድን ጨምሮ በርካታ የፓርላማ አባላት በዕለቱ ያልተገኙ እንደነበር፥ ከፓርላማው 2/3ኛ ድምፅ ለማግኘት ቢያንስ 365 ድምፅ ድጋፍ ማግኘት የሚገባ ሲሆን በዕለቱ የተገኘው የድጋፍ ድምፅ 346 ብቻ መሆኑ ቀድሞ በአፈጉባዔው መገለፃቸው አዋጁ በህጉ አግባብ እንዳልፀደቀ መረጃዎች አመልክተዋል። ይሄንንም የፓርላማው አባላት ከተበቱ በኋላ የነበረውን ስሀተት ለማረም የገዥው ስርዓት ደጋፊ የሆኑትን ጨምሮ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃንም ተደጋጋሚ የቁጥር መሰረዝና ማስተካከል ሲሞክሩ ተስተውሏል።

ይህንንም ተከትሎ አዋጁ ባለፈው ዓመት ምስከረም 2009 ዓ ም ጀምሮ ለ10 ወራት ከቆየው የአስቸኳይ አዋጅ በባሰ ህገ መንግሥቱን የሚፃረሩ፥ የዜጎችን የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች የሚጥሱ አፋኝ ድንጋጌዎችን ይዟል በሚል በህዝቡ ዘንድ ተቃውሞ ቢደረግበትም፤ አዋጁ ከህግ አግባብ ውጭ በአወዛጋቢ ሁኔታ ፀድቆ ስራ ላይ መዋሉ ታውቋል። ይህንንም ተከትሎ በተለይ በምዕራብ ኢትዮጵያ የዋጁ አስፈፃሚ ተደርጎ ሙሉ ሥልጣን የተሰጠው ወታደራዊ ዕዝ “ኮማንድ ፖስት” በጥቂቱ ከ8 በላይ ሰላማዊ ዜጎች መገደላቸው ተጠቁሟል።

በተለይም በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ወለጋና ቄለም ወለጋ ዞን፥ ደንቢ ዶሎ፥ ጊንቢ፥ ሻምቡ፥ነጆ፤ ነቀምት፥ በምዕራብ ሽዋ አምቦ፥ ጊንጪ ከተገደሉት በተጨማሪ በርካታ ሰላማዊ ዜጎች በተተኮሰባቸው ጥይት መቆሰላቸውን ከስፍራው የተገኙ የዓይን እማኞች ገልፀዋል። ከተገደሉ ዜጎች መካከልም በኃይማኖት የአምልኮ ሥፍራ የነበሩ የኃይማኖት ሰባኪ “ፓስተር” እና በ80 ዎቹ የዕድሜ ክልል ያሉ አዛውንት ይገኙበታል።

መንግሥት እየወሰደ ያለውን የኃይል ርምጃ ተከትሎ ህዝባዊ ቁጣው ከምዕረብ ኢትዮጵያ ወሌሎች አካባቢዎች እየተዛመተ ይገኛል። ይህ በእንዲህ እንዳለ አዋጁን እና የመንግሥትን ወታደራዊ የኃይል ርምጃ በሚቃወሙ አካላት ከነገ ሰኞ የካቲት 26 እስከ ረቡዕ የካቲት 28 ቀን 2010 ዓ ም ከቤት ያለመውጣት፥ የንግድና የሥራ እንቅስቃሴ እቀባ መጠራቱ ታውቋል። ከነገ የካቲት 28 ቀን 2010 ዓ ም ጀምሮ ለተከታታይ 3 ቀናት በተለይ በኦሮሚያ ክልል ምንም ዓይነት መደበኛ የትራንስፖርት እና ንግድን ጨምሮ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እንዳይኖር፥ ህዝባዊ እቀባውን ጥሶ የሚገኝ አካልም በየ አካባቢው በሚገኙ የተቃውሞ አስተባባሪዎች ርምጃ ሊወሰድበት እንደሚችል ተጠቁሟል። ነገር ግን የጤና ተቋማትና አምቡላንሶች የተለመደ ሥራቸውን መስራት እንደሚችሉና በተቃውሞ አስተባባሪዎቹ ጥበቃ እንደሚደረግላቸው ተጠቁሟል። የአስቸኳይ አዋጁ ውድቅ እስካልተደረገ ድረስ ህዝባዊ ተቃውሞ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል በተለያየ መንገድ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ተጠቁሟል። ይሁን እንጂ በመንግሥት በኩል ግን አዋጁን በተግባር ከማስፈፀም ውጭ የተሰጠ ሌላ ምላሽ የለም። ስለሆነም ይህ እስከተዘገበበት ድረስ በሀገሪቱ ያለው የፖለቲካ ውጥረት ተባብሶ ቀጥሏል።

ስጋት ያንዣበበት የኢትዮጵያ ፖለቲካ ትኩሳት

ብስራት ወልደሚካኤል

ኢትዮጵያ ውስጥ ከወትሮ በባሰ መልኩ ውጥረት አንዣብቦበታል። በአገዛዙ ህወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ህዝቡ ላይ የደረሰውና ዛሬም ያላባራው በደል ተደጋጋፊ በርካታ የመብት ጥያቄዎችን ወልዷል። ይሁን እንጂ ከአገዛዙ እየተሰጠ ያለው ምላሽ የመብት ተማጋችና ጥያቄው ላይ ተሳትፎ ያልነበራቸው ላይ ሳይቀር እየተወሰደ ያለው ርምጃ ወታደራዊ የፀጥታ ኃይል በማሰማራት ማስፈራራት፥ መግደል፥ ማሰር፥ ማሰቃየት ብሎም ከሀገር ማሰደድ ላለፉት 26 ዓመታት የተለመደ አካሄድ ነበር።

ከህዳር 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ጀምሮ በተለይ “የአዲስ አበባ የተቀናጀ ማስተር ፕላን” የሚለው የመንግሥት መሪ ዕቅድ ይፋ መደረጉን ተከትሎ በምዕራብ ኢትዮጵያ በተለይም በጊንጪ የአደባባይ ህዝባዊ ተቃውሞ ተጀመረ። በሂደትም ይህ ተቃውሞ መላው ኦሮሚያ ክልልን አዳርሶ የክልሉን አመራሮች ሹም ሽር ድረስ የዘለቀ የፀረ አገዛዝ ህዝባዊ ተቃውሞ ተዛመተ። ገዥው መንግሥትም ለህዝቡ ጥያቄና የፀረ አገዛዝ ተቃውሞ የሰጠው ምላሽ ወታደራዊ ኃይል በመሆኑ ለበርካታ ዜጎች ሞት፥ የአካል መጉደልና ንብረት መውደም ዋነኛ ምክንያት ሆኖ ቀጥሏል።

በተለይ ህዝባዊ ተቃውሞ ተጠናክሮ በቀጠለበት ወቅት የአገዛዙ አስኳል የሆነው የህወሓት እጅ አለበት እየተባለ የሚታመንበትና በኢትዮጵያ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ “በብሔር” ማንነት ላይ ባነጣጠረ ጥቃት ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ የኦሮሚያ ማኅበረሰብ አባላት ከምሥራቅ ኢትዮጵያ ተፈናቅለዋል። ይሄም ተጨማሪ ቅራኔ ፈጥሮ የአገዛዙ አጋር አባላትንም አስቆጥቶ ህዝባዊ ተቃውሞ እንዲአቀጥል ሌላ ተጨማሪ የተቃውሞ ማቀጣጠያ ሆኗል ማለት ይቻላል።

በኦሮሚያ ክልል ያለው ህዝባዊ ተቃውሞ ተጠናክሮ በቀጠለበት ሁኔታ ሐምሌ 5 ቀን 2009 ዓ ም ሌላ ተጨማሪ ህዝባዊ ተቃውሞና ቁጣ በአማራ ክልልም ተጀመረ። በአማራ ክልል ህዝባዊ ተቃውሞ መነሻ የወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ ያነገቡ የህዝቡ ወኪል ተደርገው የተመረጡ ኮሚቴ አባላትን ከሚኖሩበት ጎንደርና አካባቢ ባሉ ከተሞች በሌሊት አፈኖ ለመያዝ የተደረገው ሙከራ በአብዛኞቹ ላይ ቢሳካም በተለይም ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በወሰዱት የአፀፋ መልስና የህወሓት/ኢህአዴግ የኃይል ርምጃ የታፈነውን የህዝቡን ቁጣ ለተቃውሞ እንደ መነሻ ርሾ ሆኖታል። በኋላም ልክ እንደ ኦሮሚያ ክልልም በአማራ ክልልም ህዝባዊ ተቃውሞ ተዛምቶ ክልሉን ከተሞችና ወረዳዎች አዳርሶ ዛሬም እልባት አላገኘም።

በተመሳሳይም በደቡብ ክልል ኮንሶ ወረዳ፤ በቅርቡ ደግሞ በጉራጌ ዞን ተመሳሳይ የፀረ አገዛዝ ህዝባዊ ተቃውሞዎች ተደርገዋል። ይሁን እንጂ መንግሥት ተመሳሳይ ወታደራዊ የኃይል ርምጃ ከመውሰድ ያገደው አልነበረም። በዚህም ከ5 በላይ ዜጎች ሲገደሉ በርካታ ሰላማዊ ዜጎችም የቆሰሉ ሲሆን፤ የንብረት ውድመትንም አስከትሏል። ይህ በእንዲህ እንዳለ መንግሥት ከህዝባዊ ጥያቄዎች መካከል አንዱ የሆነውን የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ በሚል፤ የተወሰኑ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችን፥ የመብት ተሟጋቾችንና ጋዜጠኞችን ከእስር ለቋል። በርካቶች ግን ዛሬም እስር ቤት እንዳሉና ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ሊለቀቁ እንደሚገባም በቅርቡ ከእስር የተፈቱት፥ የታሳሪ ቤተሰቦችና የመብት ተሟጋቾች ጥያቄ ማቅረባቸው አልቀረም። በመጨረሻም ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ በሀገሪቱ የፖለቲካ ቀውስ መኖሩን በማመንና እርሳቸውም የመፍትሄው አካል ለመሆን ሥልጣናቸውን በገዛ ፍቃዳቸው ለመልቀቅ የሥራ መልቀቂያ ማቅረባቸውን ይፋ አደረጉ። በርካታ የህዝቡ ጥያቄዎች ግን ዛሬም መልስ አላገኙም።

በቅርቡ የተወሰኑ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞችን መለቀቅ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩን ከሥልጣን ለመልቀቅ መወሰናቸውን ተከትሎ ህዝቡ የፖለቲካ ማሻሻያዎች ይደረጋሉ ብሎ ሲጠብቅ፤ ሚኒስትሮች ምክር ቤትን ጠቅሶ ለቀጣይ 6 ወራት የሚቆይ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታውጆ፤ ከየካቲት 9 ቀን 2010 ዓ. ም. ጀምሮ ተግባራዊ ተደርጓል። አዋጁም በቅርቡ በህዝብ ተወካዮች እንደሚፀድቅ በመንግሥት ቢነገርም፤ አዋጁ በርካታ የዜጎችን ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶችን ከመጣስ በተጨማሪ ህገ መንግሥቱን የሚፃረሩ ድንጋጊዎችን ያዘለ በመሆኑ ለሌላ ጠንካራ ህዝባዊ ተቃውሞና አለመረጋጋት ያመራል በሚል ስጋት ከወዲሁ በሀገር ውስጥና በዓለም ዓቀፍ ተቋማትና ማኀበረሰብ ተቃውሞ ቀርቦበታል።

በሌላ በኩል ተተኪ ዕጩ ጠቅላይ ሚኒስትር ለማቅረብና ለመሾም በገዥው ግንባር ፓርትዎች ሽርጉዱ ቀጥሏል። በዚህም በእቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ይመራ ከነበረው ደኢህዴን/ኢህአዴግ በስተቀር ሶስቱ የግንባሩ አባል ድርጅቶች፤ ህወሓት፥ ኦህዴድ እና ብአዴን ጣጣቸውን የጨረሱ ይምስላሉ።

ህወሓት ዶ/ር ደብረጺዮን ገብረሚካኤልን ሊቀመንበር፥ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር (ሞንጆሪኖ)ምክትል ሊቀመንበር አድርገው መርጧል። እስካሁን ባለው መረጃም የትክግራይ ክልል ምክር ቤት አባል ያልሆኑት ዶ/ር ደብረጺዮን በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የትግራይ ክልል ፕሬዘዳንት ሆነው ቢሾሙም፤ ቀደም ሲል የነበራቸውን የፌደራሉን የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትርነት ሥልጣናቸውን እላስረከቡም።

ኦህዴድ በበኩሉ ቀደም ሲል የድርጅቱ ሊቀመንበር የነበሩትን አቶ ለማ መገርሳን በፓርቲው ዋና ጸሐፊ በነበሩት ዶ/ር አብይ አህመድ ተተክተው፤ የድርጅቱ ምክትል ሊቀመንበርና የኦሮሚያ ክልል ፕሬዘዳንት ሆነው ተሹመዋል። በተለይ ኦህዴድ ቀጣይ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲሆኑ በማሰብ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑትን ዶ/ር አብይ አህመድን በዕጩን ለማቅረብ የወሰነ ይመስላል።

ብዙ የተለየ ነገር ይዤ ቀርባለሁ ሲል የነበረውና ሌላኛው የህዝባዊ ተቃውሞ አካባቢ አስተዳደርን የሚመራው ብአዴን ከመሰብሰቡ በስተቀር የአመራር ሹም ሽር ወይም ማሻሻያ ሳያደርግ በነበረበት መቀጠሉን ይፋ አድርጓል። በዚህም መሰረት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ደመቀ መኮንን የድርጅቱ ሊቀመንበር፥ የአማራ ክልል ፔሬዘዳንት የሆኑትን አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ምክትል ሊቀመንበር እሆነው በነበሩበት እንዲቀጥሉ መወሰኑን ይፋ አድርጓል።

ሌላኛው የግንባሩ አባል የሆነው ደኢህዴን ይህ እስከተጠናቀረበት ድረስ ስብሰባውን ያልጨረሰ ሲሆን፤ ቀጥዩ የድርጅቱ ሊቀመንበርና ምክትሉ እንዲሁም የደቡብክ ክልል ፕሬዘዳንት ምን ማሻሻያ ወይም ለውጥ ሊኖረው እንደሚችል ለመገመት አስቸጋሪ አድርጎታል።

ሀገሪቱ በበርካታ ህዝባዊ ጥያቄና የፀረ አገዛዝ ተቃውሞ ባየለባትና መደበኛው የሀገሪቱ የህዝብ አስተዳደር በአስቸኳይ አዋጅ ሥር ወደ ወታደራዊ አገዛዝ በተቀየረበት ሁኔታ በዚህ በመጪው ሳምንት ኢህአዴግ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ይሾማል ተብሎ ይጠበቃል። በበርካታዎች ግምት ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ከኦህዴድ ዕጩ ሊሾም እንደሚችል ተጠብቋል። በተለይ የኦህዴድ/ኢህአዴግ ዕጩ የሆኑት ዶ/ር አብይ አህመድ ዓሊ ቀጣዩ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊሆኑ እንደሚችሉ በርካቶች ግምታቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።

ነገር ግን የሀገሪቱ ፖለቲካ በበላይነት የሚዘውረው ህወሓት በአዲሶቹ የኦህዴድ አአመራሮች በሐሳብና በተግባር እየተገዳደሩት፤ ይልቁንም ህዝባዊ ቅቡልነት ማግኘታቸው የበላይነቱን እንደተነጠቀ ስለሚሰማው በተፎካካሪነት ከራሱ ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሔር ነጋን አሊያም ለህወሓት የምንጊዜም ታዛዥ እንደሆኑ የሚነገርላቸውን የብአዴን ሊቀመንበሩን አቶ ደመቀ መኮንን ሐሰንን ዕጩ ጠቅላይ ሚኒስትር አድርጎ በማቅረብ የፖለቲካ ጨወታውን ሊቀይረው እንደሚችልም መጠርጠር አይከፋም። ደኢህዴን የህወሓትን የበላይነት ለማስጠበቅ በአጋርነት ለመቆም ዕጩ ተፎካካሪ ካላቀረበ በስተቀር፤ አዲስ ለሚጠበቀው ጠቅላይ ሚኒስትር ዕጩ ያቀርባል ተብሎ አይጠበቅም።

ምንም ሆነ ምን በቀጣይ ከሚጠበቀው አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር በነበረው የሟቹ አቶ መለስ ዜናዊ አሊያም የተሰናባቹን የአቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ዓይነት አገዛዝ ማስቀጠል እጅግ አስችጋሪ ነው። ስለሆነም ብዙ ግምት የሚሰጠው ስጋት ያንዣበበትን የሀገሪቱን የፖለቲካ ትኩሳት ለማርገብ አዲሱ ተሿሚ ምን ዓይነት ማሻሻዮችን ያደርጉ ይሆን የሚለው ነው። ምክንያቱም ያለውን ትኩሳት ለማብረድና ሀገሪቱን እና ህዝቡን ከተጋረጠው አደጋ ለመታደግ ከአዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ብዙ ይጠበቃልና። ሁሉን አቀፍና አሳታፊ የሆነ የሽግግር መንግሥት ምሥረታን ጨምሮ በርካታ የፖለቲካ ማሻሻዮች የማይደረጉ ከሆነ፤ ባለፉት 3 ዓመታት በሁለትና ሶስት ክልሎች የነበረው የፀረ አገዛዝ ህዝባዊ ተቃውሞ በሌሎችም የሀገሪቱ አካባቢዎች በመዛመት አገዛዙን በህዝባዊ አመፅ ከመገርሰስ በተጨማሪ የሀገሪቱ ደህንነት ላይ አደጋ ሊጋርጥ ይችል ይሆናል። ይህም በቀጣይ አገዛዙ በሚወስዳቸው ርምጃዎች የየተመሰረተ ይሆናል።

እነ ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱና ንግስት ይርጋ ክሳቸው ተቋርጦ ፤ እነ ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞ እና አሳምነው ጽጌ በይቅርታ እንዲፈቱ መወሰኑ ተገለፀ

(ዳጉ ሚዲያ) ከወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ህዝባዊ ተቃውሞ በእስር ላይ ከነበሩት ሰዎች መካከል ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ፥ አቶ ጌታቸው አደመ፥ አቶ አታላይ ዛፌ፥አቶ ተሻገር ወልደሚካኤል እና ንግስት ይርጋ ጨምሮ የ 101 እስረኞቸ ክሳቸው እንዲቋረጥ መደረጉን ለመንግሥት ቅርበት ያላቸው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

Colonel-Demeke-ZewduNigist Yirga

ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ እና ወ/ት ንግስት ይርጋ

ክሳቸው እንዲቋረጥ ከተወሰነላቸው እስረኞች መካከል 56 በግንቦት ሰባት፥ 41 እንዲሁም ከኦነግ ጋር ተባብራችኋል በሚል ክስ የተመሰረተባቸው ነበሩ።

General Tefera MamoGeneral Asaminew Tsige

ብ/ጄነራል ተፈራ ማሞ እና ብ/ጄነራል አሳምነው ጽጌ

በተያያዘ ዜና፤ የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የሚል ክስን ጨምሮ በተለያየ ጉዳይ ተከሰው የተፈረደባቸውና በይቅርታ ከእስር እንዲለቀቁ ከተወሰነላቸው መካከል ብርጋዴር ጀነራል ተፈራ ማሞና ብርጋዴር ጀነራል አሳምነው ጽጌን እንደሚገኙብት ተጠቁሟል።

በኢትዮጵያ የፀረ አገዛዝ ህዝባዊ ተቃውሞዎች ዳግም ተቀሰቀሱ

በኢትዮጵያ 2010 አዲስ ዓመት ህዝባዊ ተቃውሞዎች ዳግም ተቀሰቀሰ። በተለይ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ከተሞች በገዥው መንግሥት ላይ ዳግም ህዝባዊ ተቃውሞች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተከትሎ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በወሰዱት ወታደራዊ የኃይል ርምጃ 8 ያህል ሰዎች መገደላቸውን መረጃዎች አመልክተዋል።

ባለፈው ህዳር 2008 ዓ. ም. ጀምሮ ክዓመት በላይ የዘለቀው የኦሮሚያ፥ አማራ እና ደቡብ ክልል በተለይም ኮንሶ አካባቢ የተከሰተውን ህዝባዊ የፀረ አገዛዝ ተቃውሞ ተከትሎ ሀገሪቱ ለ10 ወራት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር እንደነበረች ይታወሳል። ይሁን እንጂ በአስችኳይ አዋጁ ጊዜ ህዝባዊ አመፁ የተረጋጋ ቢመስልም በያዝነው ጥቅምት 2010 ዓ .ም. ዳግም ማገርሸቱ ታውቋል።

የህዝቡ ተቃውሞ ዋነኛ ምክንያት ተደርጎ የተጠቀሰውም ባለፈው መስከረም 2010 ዓ ም በኦሮሚያ እና በኦጋዴን የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ድንበር አካባቢ በተቀሰቀሰ ግጭት በርካታ ሰላማዊ ዜጎች መገደላችውን እና በኦጋዴን የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል አስተዳደርና በክልሉ ልዩ ኃይል ፖሊስ አማካኝነት ከ70,000 በላይ ዜጎች ከሚኖሩበት ቀዬ መፈናቀላቸውን በመቃወም እንዲሁም የታአሰሩ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ የሚል ጥያቄም እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

በተለይ ባለፈው መስከረም 2010 ዓ ም በሁለቱ ክልሎች ድንበር አካባቢ በተቀሰቀሰ ግጭት ከሁለትም ክልል በርካታ ንፁሃን ዜጎች መገደላቸው ይታወሳል።

ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስም በተለይ በኦሮሚያ ክልል ባሉ አንዳንድ ከተሞች ህዝባዊ ተቃውሞች መቀጠላቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል።

Ethiopia’s ethnic federalism is being tested

Violence between ethnic groups has put the country on edge

FOR centuries the city of Harar, on the eastern fringes of the Ethiopian highlands, was a sanctuary, its people protected by a great wall that surrounded the entire city. But in the late 19th century it was finally annexed by the Ethiopian empire. Harar regained a bit of independence in 1995, when the area around it became the smallest of Ethiopia’s nine ethnically based, semi-autonomous regions. Today it is relatively peaceful and prosperous—and, since last month, a sanctuary once more.

In recent weeks thousands of Ethiopians have poured into areas around Harar, fleeing violence in neighbouring towns (see map). Nearly 70,000 people have sought shelter just east of the city. Several thousand more are huddling in a makeshift camp in the west. Most are Oromo, Ethiopia’s largest ethnic group. Its members clashed with ethnic Somalis in February and March, resulting in the death of hundreds. The violence erupted again in September, when more than 30 people were killed in the town of Awaday. Revenge killings, often by local militias or police, have followed, pushing the death toll still higher. In response, the government has sent in the army.

Ethio-conflict map.png

Ethnic violence is common in Ethiopia, especially between Oromos and Somalis, whose vast regions share the country’s longest internal border. Since the introduction of ethnic federalism in 1995, both groups have tried to grab land and resources from each other, often with the backing of local politicians. A referendum in 2004 that was meant to define the border failed to settle the matter. A peace agreement signed by the two regional presidents in April was no more successful.

When the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) swept to power in 1991 after a bloody 15-year civil war, federalism was seen as a way to placate the ethnic liberation movements that helped it to power. The previous regime had been dominated by the Amhara, the second-largest ethnic group (the Eritreans broke away to form a new state). Eventually ethnic loyalties would wither as people grew richer, went the thinking of the Marxist-inspired EPRDF.

But the way federalism was implemented caused problems from the start.New identity cards forced people to choose an ethnicity, though many Ethiopians are of mixed heritage. Territories often made little sense. In the Harari region, a minority of Hararis rule over much bigger populations of Oromos and Amharas, a source of resentment. Boundaries that were once porous became fixed, leading to disputes.

For years the EPRDF sought to dampen the tension by tightly controlling regional politics. But its grip has loosened over time. Local governments have grown stronger. Regional politicians are increasingly pushing ethnic agendas. The leaders of Oromia, the largest region, have drafted a bill demanding changes to the name, administration and official language of Addis Ababa, the capital, which has a special status but sits within Oromia. They have stoked ethnic nationalism and accused other groups of conspiring to oppress the Oromo.

Politicians in the Somali region are no more constructive. They have turned a blind eye to abuses by local militias and a controversial paramilitary group known as the Liyu. The region’s president “has a fairly consistent expansionist agenda”, says a Western diplomat. “He may have spied an opportunity.” The federal government, now dominated by the Tigrayan ethnic group, was rocked by a wave of protests last year by the Oromo and other frustrated groups.

Many complain that the rulers in Addis Ababa are doing too little. They have been slow to respond to the recent violence, fuelling suspicions that they were complicit. “We are victims of the federal government,” shouts Mustafa Muhammad Yusuf, an Oromo elder sheltering in Harar. “Why doesn’t it solve this problem?”

Federalism may have seemed the only option when it was introduced in 1995. But some now suggest softening its ethnic aspect. “In the past the emphasis was too much on ethnic diversity at the expense of unity,” says Christophe Van der Beken, a professor at the Ethiopian Civil Service University. “The challenge now is to bring the latter back.”

Source: The Economist.

%d bloggers like this: