በሽብር ወንጀል የተከሰሱት የነ መሪ ጌታ ዲበኩሉ አስማረ የፍርድ ቤት ውሎ
ቴዎድሮስ አስፋው
“እየተመገብንና እየጠጣን ያለው አሸዋ ነው” ተከሳሾች
~”ስሜ መሪጌታ ዲበኩሉ አስማረ እንጂ ወይዘሪት ዲበኩሉ አስማረ አይደለም”
~የመቃወሚያ ብይን ለመስጠት 9 ወር ፈጅቷል
በፀረ ሽብር አዋጅ አንቀፅ 3 ንዑስ አንቀፅ 1 ተጠርጥረው በነ አቶ ክንዱ የክስ መዝገብ ክስ የተመሰረተባቸው 8 ተከሳሾች መጋቢት 3 ቀን 2010ዓ.ም የክስ መቃወሚያ ብይን ለመስጠት ለመጋቢት 6 ቀን 2010ዓ.ም ተቀጥሮ በነበረው መስረት ተከሳሾች የሚመለከታቸው አካላት ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ ችሎቱ በሚካሄድበት የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 4ኛ ወንጀል ችሎት አዳራሽ ውስጥ የተገኙ ቢሆንም ችሎቱ ግን ዘግይቶ 5 ሰዓት ላይ ነው የጀመረው።
የመሀል ዳኛው ዳኛ በመጓደሉ ምክንያት መዘግየታቸውን ገልፀው ዘግይተው በመጀመራቸው ይቅርታ በመጠየቅ ከሳሽ ዐቃቤ ህግ የተከሳሽ ጠበቆች እንዲሁም ተከሳሾች መኖራቸው በስም ጥሪ በሚያረጋግጡበት ግዜ 6ኛ ተከሳሽ መሪጌታ ዲበኩሉ አስማረን ወይዘሪት ዲበኩሉ ሰመረ ብለው በመጥራታቸው ተከሳሹ ስሜ መሪጌታ ዲበኩሉ ሰመረ እንጂ ወይዘሪት ዲበኩሉ አስማረ አይደለም በማለት ስማቸው እንዲስተካከልለት ጠይቀዋል።
በዚህም መሰረት ዳኛው መዝገቡ ላይ ወ/ት ተብሎ መመዝገቡን ገልፆ ለስህተቱ ይቅርታ ጠይቋል። በመጨረሻም የክስ መቃወሚያ ብይኑን በዳኛ መጓደል ምክንያት እንዳልሰሩት በመግለፅ ተለዋጭ ቀጠሮ ለመስጠት የተከሳሽ ጠበቆችና ተከሳሾች አስተያየት እንዲሰጡ ጠይቀዋል።
ከ2ኛ እስከ 6ኛ እና የ10ኛ ተከሳሾች ጠበቃ መዝገቡ በዚህ ሳምንት ብቻ ብይን ለመስጠት ለ3ኛ ግዜ መቀጠሩን በመግለፅ የአሁኑ ቀጠሮ የመጨረሻ እንዲሆን ጠይቀዋል። 7ኛ ተከሳሽ ሀብታሙ እንየው መዝገቡ እየተጓተተ ያለው በኔ የመቃወሚያ ብይን ነው ይህም 9 ወር መፍጀቱ አሳዛኝ ነው ብሏል። ከዚህ በተጨማሪ 10ኛ ተከሳሽ ለገሰ ወልደሃና በማረሚያ ቤቱ የሚቀርብልን ምግብና መጠጥ አሸዋ ያለበት በመሆኑ በተደጋጋሚ ግዜ እንዲስተካከልልን ለአስተዳደሩ ብናቀርብም መልስ ማግኘት ስላልቻልን ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ይስጥልን ሲል አቤቱታውን በጽሁፍ ጭምር አቅርቧል።
የመሀል ዳኛው ፍርድ ቤቱ በማረሚያ ቤቱ የውስጥ አስተዳደር ጣልቃ የማይገባ ቢሆንም የምግብና የመጠጥ አቅርቦቱን በሚመለከት አስተዳደሩን ጠርተን እናናግራለን ዛሬ ከሰዐትም አጠቃላይ የፍትህ አካላት ውይይት ያለ በመሆኑ በዚሁ አጋጣሚ መልስ እንደሚያገኝ ገልፀዋል። ቀጠሮውንም በሚመለከት ለቀጣዩ ሳምንት ለመጋቢት 13 ጠዋት ላይ እንዲሆን በመወሰን የመጨረሻ እንደሚሆን ገልፀዋል።
የተከሳሾች ስም ዝርዝር
1ኛ. ክንዱ ዱቤ
2ኛ. ዘመነ ጌጤ
3ኛ. ደበበ ሞገስ
4ኛ. ዘራይ አዝመራው
5ኛ. ገብረስላሴ ደሴ
6ኛ. መሪጌታ ዲበኩሉ ሰመረ
7ኛ. ሀብታሙ እንየው
10ኛ. ለገሰ ወልደ ሃና ናቸው
8ኛ እና 9ኛ ተከሳሾች ክሳቸው መቋረጡ በፍርድ ቤቱ ተገልፆል።
የዋልድባ ገዳም መነኮሳት አባ ገብረ-ሥላሴ ስና አባ ገብረ-ኢየሱስ የፍርድ ቤት ውሎ
ሀብታሙ ምናለ
የፌደራሉ ከፍተና ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት፤ የካቲት 30 ቀን 2010 ዓ. ም. በዋለው ችሎት የዋልድባ መነከሳት ባቀረቡት “የሰብዓዊ ጥሰት በማረሚያ ቤቱ ተፈፅሞብናል ፍርድ ቤቱ ተትዕዛዝ ይስጥልን!” ብለው ያቀረቡትን አቤቱታ ሰምቶ የማረሚያ ቤቱን ምላሽ ለመስማት ሲኾን ማረሚያ ቤቱም ምላሽ የሚለውን በደብዳቤ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡
ፍርድ ቤቱ ማረሚያ ቤቱ የሰጠውን ምላሽ እንደተመለከተው እና ውሳኔ እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡ አባ ገብረ ኢየሱስ ኪዳነ ማርያም “የተከሰስነውም የታሰርነው አንድ ላይ ቢኾነም እኔን ያለምንም ምክንያት ወደ ዞን አምስት በተለምዶ ጨለማ ወይም ቅጣት ቤት ወደሚባለው አዘዋውረውኛል፡፡ ተቀጥቼ ከኾነ ጥፋቴ ተነግሮኝ፤ ቅጣቴ ምን ያህል ቀን እንደኾነ አውቄ ቅጣቴን ልቀበል፤ ያለምንም ጥፋት ዝም ብዬ ነው፡፡ እየተሰቃየኹ ያለኹት ብዙ በደል ደርሶብናል፡፡ ከአመት በላይ ልብስ ሳንቀይር ቆይተን በቅርብ ቀን አንድ ምዕመን ልብስ አምጥቶልኝ እኔ ለመቀየር ችያለሁ፡፡
ነገር ግን አባ ገብረሥላሴ ከተያዙ ጀምሮ ምንም ልብስ ቀይረው አያውቁም። ሰዎች ልብስ ሲያመጡ ማስገባት አይቻልም፡፡ እያሉ እያስመለሱ ከአንድ ዓመት በላይ በአንድ ልብስ ብቻ ሳናወልቅ ቆይተናል፡፡ ኹለታችንም አብረን በአንድ ዞን የነበርነው ያለምክንያት በታትነውናል፡፡ ሰዎች ሊጠይቁን ሲመጡ የተለያየ ዞን በመኾናችን ጠያቂዎቻችን እክል እየገጠማቸው ነው፡፡ ወደነበርኩበት ዞን ልመለስ” ብለው ጠይቀዋል፡፡
ዳኞቹም፡- “ልብስ ለምን አይገባም?” ብለው የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች ሲጠይቁ መልስ መስጠት ባለመቻላቻው “ልብስ ማነው የሚያመጣላችሁ?” ብለው ዳኞች ሲጠይቁ ችሎቱን ሲከታተሉ ከነበሩት ወጣቶች መካከል ለአንዳቸው የሚኾን የምንኩስና ልብስ ገዝተው ይዘው ነበር፡፡ ልብሱን ሲያቀርቡ ዳኞቹ፡- “ጠባቂዎቹን ፈትሹና ስጧቸው!” ቢልም ፍቃደኛ አለመኾናቸውን ሲያሳዩ ዳኞቹ በቁጣ “ተቀበሉና ፈትሻችሁ ስጡ!” በማለት ሲያዙ የማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ወታደራዊ ሰላምታ በመስጠት ወደ ዳኞቹ ተጠግቶ ሊናገር ሲል ዳኞቹ፡- “የተባልከውን ብቻ አድርግ! ምንም ሌላ አያስፈልግም!” በማለት ልብሱ ተፈትሾ ለአባ ገ/ሥላሴ ተሰጥቷቸዋል፡፡
ፍርድ ቤቱም ያቀረቡትን አቤቱታ እና የተሰጠውን መልስ አይተው ውሳኔ ለመስጠት ለመጋቢት 5 ቀን 2010ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ መጋቢት 18 መደበኛ የክስ የሚቀጥል እና ምስክር እንደሚሰማባቸው ይታወቃል፡፡
የሀገረ ስብከቱ ጳጳስ: በወልድያ የበዓለ ጥምቀት ግጭትና ግድያ የጸጥታ ኃይሉን ወቀሱ፤“የእነርሱ መዘዝ ነው፤ወጣቱ አበላሸ የምንለው ነገር የለም”
“መከላከያዎቹ እንዳይመጡ ቀድመን አሳስበናል፤ከዞኑም ጋር ተናበን እየሠራን ነበር፤”
“በሰላም ሊጠናቀቅ ባለበት ሰዓት መጥተው ግጥም አሉ፤ ይኸው ወጣቱን አሳበዱት፤”
“ወጣቱን ሌላ የፖሊቲካ አካል ቀሰቀሰው አሉ፤ ወታደሮቹን ማን ነው የቀሰቀሳቸው?”
“የበቀል ነው የሚመስለው፤እንደው ከራሳቸው መካከልም የሚያጠፋ ያለ ይመስለኛል፤”
“ታቦቱን ያከበሩት ካህናት፣በጎናቸው ባሉት ካህናት ተገድፈው ነው እንጅ ወድቀዋል፤”
“ተዉ ብሎ ይህን ማስተካከል እና መሥመር ማስያዝ ያለበት መንፈሳዊ አባት ነው፤”
“ቤተ ክርስቲያኗን ወጣቱ ሰምቶልናል፤ታቦቱ ከገባ በኋላ ሁሉም እንሙት እያለ ነበረ፤”
†††
“ተረጋግቶ እያለ ድኻ የሚረዳ ልጅ ገድለው ዳግም በእነርሱ ስሕተት ግጭቱ ቀጠለ፤”
“ሕንፃ እግዚአብሔር እያፈረሳችሁ ፎቅ ትጠብቃላችሁ፤”ብሎ ሕዝቡ በጣም ተቆጨ፤
“ስንቱስ ንብረት ወደመ? የእነርሱ መዘዝ ነው፤ ወጣቱ አበላሸ የምንለው ነገር የለም፤”
“መከላከያ ይውጣ፤ ወጣቱ ከከተማው ፖሊስ ጋር ይጠብቀዋል፤” በሚል ተስማማን፤
ርእሰ መስተዳድሩም፣ “ሠራዊቱን አስወጣለሁ፤ አጣሪ እልካለሁ፤ አጥፊው ለሕግ ይቀርባል፤ ይፋም አደርጋለሁ፤” ብለዋል፤ ልቅሶ ቤትም ገብተው አብረው እያለቀሱ አጽናንተዋል፤
“ከኹለት ዙር ውይይት በኋላ፣ ወጣቱን በየአቅጣጫው የሚመሩ ካህናት መድበን ወደየቤቱ እንዲገባ አድርገናል፤ በሰላም እየዘመረም ወደየቤቱ ተመልሷል፤”
“እኛም በየሐዘን ቤቱ እየዞርን ስናጽናና ውለናል፤ ርእሰ መስተዳድሩ ከተመለሱ በኋላ ከላኳቸው ልኡካን ጋራ የሃይማኖት አባቶችና የሀገር ሽማግሌዎች ተካትተን እየመከርን ነው፤”
†††
ፎቶ፡ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፤ የሰሜን ወሎ እና ከሚሴ ዞን ሀገረ ስብከት ረዳት ሊቀ ጳጳስ
በሰሜን ወሎ ዞን ወልዲያ ከተማ፣ በጥምቀት እና በቃና ዘገሊላ በዓል አከባበር ወቅት የተቀሰቀሰው ግጭትና የተፈጸመው ግድያ፣ በጸጥታ ኃይሉ ስሕተት የደረሰ ነው፤ ያሉት የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ረዳት፣ ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ፣ ለጠፋው የዜጎች ሕይወት እና ለወደመው ንብረት ወቀሱት፡፡
የቃና ዘገሊላ በዓል፣ እንደ በዓለ ጥምቀት ኹሉ በሥርዐቱ እየተከበረ በሰላም ሊጠናቀቅ በተቃረበበት ሰዓት የመጣው የጸጥታ ኃይል “ያልተጠራ” እንደነበር የጠቀሱት ብፁዕነታቸው፣ ከመጣ ችግር እንደሚፈጠር ስለታመነ እንዳይመጣ ሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ቀድመው አሳስበው እንደነበር አውስተዋል፡፡
his-grace-abune-qerlos
ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ፤ የሰሜን ወሎ እና ዋግ ኽምራ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ለበዓሉ አከባበር፣ ሀገረ ስብከቱ ከዞኑ ሓላፊዎች ጋራ እየተናበበ በመሥራቱ የተጠየቀ ተጨማሪ ኃይል እንዳልነበርና “እነርሱ አይምጡ፤ እኛው በእኛው ፕሮግራማችንን እንመራለን፤” በማለት ቀድሞ እንዳሳወቀ ብፁዕነታቸው ጠቁመዋል፡፡
ይኹንና በመምጣታቸው ወጣቱን ለተቃውሞ እንዳነሣሡ ተናግረዋል፤ “ወጣቱን አሳበዱት፤ የተሳደበም ይመስለኛል፤ ድንጋይም ሳይወረውር አይቀርም፤ በጥይት ለቀሙት፤” በማለት የርምጃውን ኢፍትሐዊነት አስረድተዋል፡፡ በማግሥቱም ቀጥሎ የነበረው ግጭትና የንብረት ውድመት መንሥኤ የጸጥታ ኃይሉ እንደኾነ የተናገሩት ብፁዕነታቸው፣ “የእነርሱ መዘዝ ነው፤ እኛ ወጣቱ አበላሸ የምንለው ምንም ነገር የለም፤” ሲሉ ድርጊቱን ኮንነዋል፡፡
በሞትና መቁሰል ስለደረሰው ጉዳትም፣ “ብዙ ሰው ነው የተጎዳብን፤ ያላወቅነውም ይኖራል፤” ብለዋል ብፁዕ አቡነ ኤርሚያስ፡፡ ግጭቱ በተከሠተበት ወቅት ከመርሳ ከተማ ወደ ወልዲያ ተመልሰው በዚያው አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ለማስተማር በዝግጅት ላይ እንደነበሩ ገልጸው፣ የጸጥታ ኃይሎቹ ለብተና በተጠቀሙበት አስለቃሽ ጢስ ታቦቱን ያከበሩት ካህናት፣ “በጎናቸው ባሉ ካህናት ተገድፈው ነው እንጅ ወድቀዋል፤” ብለዋል ጥልቅ ቅሬታ በሚደመጥበት አነጋገር፡፡
የጸጥታ ኃይሉን ለምን ማሠማራት እንዳስፈለገ እንደማያውቁ ብፁዕነታቸው ጠቅሰው፣ ኾነ ተብሎ የታቀደ እንደሚመስላቸው ሳይገልጹ አላለፉም – “ለምን እንደመጡ አናውቅም፤ ኾን ብለው ለመምታት ይመስላል፤ ከራሳቸው መካከልም የሚያጠፋ ያለ ይመስለኛል፤” ብለዋል፡፡ አያይዘውም፣ “ወጣቱን ሌላ የፖሊቲካ አካል ቀሰቀሰው ይባል፤ እነርሱን ወታደሮቹን ማን ነው የቀሰቀሳቸው? ሰላም እንዳይኾን!” ሲሉ ጠይቀዋል፡፡
ከክልሉ ርእሰ መስተዳድር ጋራ በኹለት ዙሮች በተካሔደው ውይይት፣ ወጣቱ በአጠፌታ ተሠማርቶበት ከነበረው የንብረት ማቃጠልና ማውደም አረጋግተው ወደ አዳራሽ እንዲገባ በማድረግ ከሌሎች የሃይማኖት አባቶች እና የአገር ሽማግሌዎች ጋራ የተሳካ ሥራ እንደሠሩ ብፁዕነታቸው ይገልጻሉ፡፡ ቀደም ሲል ከእግር ኳስ ጨዋታ ጋራ ተያይዞ ተከሥቶ በነበረው የከተማዋ ግጭት በተለይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን የማረጋጋት አባታዊ ሚና እንደነበራቸው በማውሳት፣ “ቤተ ክርስቲያኗን ወጣቱ ሰምቶልናል፤” ሲሉ አመስግነዋል፡፡
ባለፈው ሰኞ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር በተገኙበት በተደረገው ውይይት፣ የመንግሥት ጥፋት በግልጽና በዝርዝር መቅረቡን፤ ለከተማው ሰላምና ጸጥታ በሚረዱ አጠቃላይ መፍትሔዎች ላይም ስምምነት እንደተደረሰ አስታውቀዋል፡፡ ሠራዊቱን ከከተማው እንደሚያስወጡ ርእሰ መስተዳድሩ የገለጹ ሲኾን፣ ለሰላሙና ጸጥታው ወጣቱ ከፖሊስ ተባብሮ እንደሚሠራም አረጋግጧል፡፡ ርእሰ መስተዳድሩ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው፣ “ስለተፈጸመው ነገር የሚያጣራ አካል እልካለሁ፤ አጥፊው ለሕግ ይቀርባል፤ ለእናንተም ይፋ አደርጋለሁ፤” ማለታቸው ታውቋል፡፡
ከውይይቱ በኋላ አቶ ገዱ፣ ሐዘንተኞችን በየቤታቸው ተገኝተው በማጽናናታቸው ያመሰገኑት ብፁዕነታቸው፣ በቤተ ክርስቲያንም በኩል ካህናትን መድቦ ወጣቱ በሰላም ወደየቤቱ እንዲገባ ከማድረግ ባሻገር፣ እስከ ትላንት ድረስ ሐዘንተኞችን ሲያጽናኑ መቆየታቸውን ተናግረዋል፡፡ በአኹኑ ወቅትም በክልሉ መንግሥት ተሠይሞ ከተላከው ልኡካን ቡድን ጋራ፣ እርሳቸውን ጨምሮ የከተማው የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሽማግሌዎች የተካተቱበት ምክክር እየተካሔደ እንዳለ አስታውቀዋል፡፡
እየተከሠተ ያለው የግፍና የጥፋት ድርጊት፣ ሕዝብን ከሕዝብ እያለያየ መኾኑ በእጅጉ እንደሚያሳዝናቸው ብፁዕነታቸው ተናግረዋል፡፡ “ተዉ ማለት ያለበት፣ ይህን ማስተካከልና መሥመር ማስያዝ ያለበት መንፈሳዊ አባት ነው፤” ሲሉ ቤተ ክርስቲያን ጥፋትን የመከላከል፣ አጥፊውን የማውገዝና የመገሠጽ፣ የተበደለው እንዲካስና እንዲጽናና የማድረግ በአጠቃላይ የአገርን ሰላምና የሕዝብን አንድነት የማስጠበቅ ከባድ መንፈሳዊና ታሪካዊ ሓላፊነት እንዳለባት አመልክተዋል፡፡
አባቶችና መንበረ ፓትርያርኩ፣ የቤተ ክርስቲያናችንን ክብር በመዳፈርና ሥርዐቷን በመጣስ ጭምር ስለተፈጸመው የወልዲያው ግፍ፣ አቋማቸውን እንዲያሳውቁና ኖላዊነታቸውን እንዲያረጋግጡ በብዙኃን መገናኛዎችና በመግለጫዎች የሚሰነዘሩት ጥያቄዎችና ወቀሳዎች እንደቀጠሉ ናቸው፡፡
መኢአድ እና ሰማያዊ ፓርቲዎች፣ ከትላንት በስቲያ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የጥምቀት እና የቃና ዘገሊላ በዓልን ለማክበር በወጡ የወልዲያ ሰላማዊ ዜጎች ላይ የተፈጸመውን ግድያ የተመለከተችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ድርጊቱን አለማውገዟ ያስተዛዝበናል፤ ብለዋል፡፡
ለተነሣው ግጭትና ለተወሰደው የግድያ ርምጃ የቀረበው ምክንያት፣ “መንግሥትን የሚቃወም ዜማ አሰማችሁ፤” የሚል እንደኾነ በመግለጫቸው የጠቀሱት ፓርቲዎቹ፣ “ይህ ደግሞ መብት መጣስ ነው፤” ብለዋል፡፡
አክለውም፣ “የጸጥታ ኃይሎች ቅዱስ ታቦትን ባከበሩ ቀሳውስት ላይ አስለቃሽ ጭስ መተኮሳቸው ሃይማኖቱን መዳፈር በመኾኑ መንግሥት ድርጊቱን በማውገዝ የእምነቱን ተከታዮች በዐደባባይ ይቅርታ ይጠይቅ፤ ለሟች ቤተ ሰዎች የደም ካሳ እንዲከፍል፤ ግድያው እንዲፈጸም ትእዛዝ የሰጡም ኾነ ጉዳዩን በቸልተኝነት የተመለከቱ የዞኑ ባለሥልጣናት በሕግ እንዲጠየቁ፤ ግድያውን የፈጸሙ የመንግሥት ታጣቂዎች ለሕግ እንዲቀርቡ እንጠይቃለን፤” ሲሉ አቋማቸውን አስታውቀዋል፡፡
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤን በመወከል በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ርእሰ መንበርነት አመራር የሚሰጠው ቋሚ ሲኖዶስ፣ ከልደት ጀምሮ በነበሩት ዐበይት ክብረ በዓላት ሳቢያ የተመደቡት ተለዋጭ አባላቱ ብፁዓን አባቶች በየአህጉረ ስብከታቸው በመኾናቸው አለመሰብሰቡ ተጠቁሟል፡፡ ሰሞኑን እስከ ግንቦቱ የርክበ ካህናት ምልአተ ጉባኤ ድረስ በተለዋጭነት በተመደቡት አራት ብፁዓን አባቶች አባላቱ በሚቀጥለው ሳምንታዊ መደበኛ ስብሰባው፣ ጉዳዩን ይመለከተው እንደኾነም ለማረጋገጥ አልተቻለም፡፡
ምንጭ፦ ሐራ ዘተዋሕዶ
7 die at Ethiopia’s Epiphany in clashes with security forces
By ELIAS MESERET
January 21, 2018, ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — An Ethiopian police official in the restive Amhara region in the north confirmed Sunday evening that seven people were killed when worshippers celebrating the Epiphany holiday clashed with security forces.
The killings on Saturday, January 20,2018 in the town of Woldiya, some 500 kilometers (310 miles) north of the capital Addis Ababa, happened on the second day of the colorful Epiphany celebrations in this East African nation.
Amare Goshu, a police official in the region, told the state-owned Ethiopian Broadcasting Corporation that seven people died, including one security officer, during the confrontation. He said that the security forces responded with force when youths in the town tried to attack officers who were patrolling the holiday procession areas. “More than 15 citizens and 2 police officers were also injured and are now receiving treatment,” he said.
Two Woldiya residents, who spoke to The Associated Press on condition of anonymity for fear of reprisal, said the measures taken by the security forces were excessive and feared the death toll was higher. One claimed police fired on demonstrators who were throwing stones. The other said the death toll could rise further as gunshots could be heard until midday Sunday. Both added that a number of hotels, restaurants and shops were burned down by angry protesters.
Ethiopia’s Amhara and Oromia regions have seen violent anti- government protests since November, 2015, when people took to the streets demanding political freedom and the release of political prisoners. Hundreds have been killed and more than 11,000 arrested, although most have since been released.
Ethiopia is an ally of the U.S. but it is often accused by rights groups of stifling dissent and arresting opposition figures and journalists critical of the government. A prominent opposition politician, Merera Gudina, was released on Wednesday as part of a pledge by the government to open up the political space and create a national consensus.
Source: AP.
አባ ገብረ-ኢየሱስ ዘዋልድባ፤ ተደብድበውና አካላቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶ ጭለማ እንደሚገኙ ተጠቆመ
በጌታቸው ሺፈራው
#የፌደራልከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ውሎ
” #አባገ/እየሱስ ዘ _ዋልድባ ተደብድበው፣ ተሰባብረው እኔ ጋር ጨለማ ቤት ነው ታስረው ያሉት” አስቻለው ደሴ
#እስረኞች ለህይወታቸው እንደሚሰጉ ገልፀዋል
#የዐቃቤሕግ ምስክር ስሙን እየቀያየረ በተለያዩ መዝገቦች እየመሰከረ ነው ተብሏል
#የአማራክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ዛሬም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣኑን አጥቷል የሚል ብይን ተሰጥቶበታል
ፎቶ:- አባ ገብረ-ኢየሱስ ዘ-ዋልድባ
~የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬም (ህዳር 28/2010) የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣኑን አጥቷል የሚል ብይን ሰጥቷል። ፍርድ ቤቱ ብይን የሰጠው በእነ አስቻለው ደሴ መዝገብ የተከሰሱ 4 ግለሰቦች ወንጀል ፈፅማችኋል የተባልነው በአማራ ክልል በመሆኑ ጉዳያችንን ሊያየው የሚገባው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው ብለው ላቅቡት የክስ መቃወሚያ ነው።
ብይኑን በአብላጫ ድምፅ የሰጠው ፍርድ ቤቱ በአዲስ አበባና ድሬዳዋ እንዲሁም ሶማሊ፣ አፋር፣ ሀረሪ(?)፣ ደቡብና ቤንሻንጉል ክልሎች የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶችየፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትን ስራ ደርበውና ወክለው እንዲሰሩ ስልጣን ስለተሰጣቸው የአማራ ክልልን ጨምሮ ሌሎች ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣንን አጥተዋል ተብሏል።
በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ለቀረቡለት የክስ መቃወሚያዎች ከአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ ሶማሊ፣ አፋር፣ ቤንሻንጉልና ሀረሪ(?) ክልሎች ውጭ ያሉ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣንን አጥተዋል ብሎ በተደጋጋሚ ብይን ሰጥቷል።
~ብይኑ የተሰጠው በአብላጫ ድምፅ ሲሆን የመሃል ዳኛው ዮሃንስ ጌስያብ ለሌሎች ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣን በሕግ መሰጠቱ፣ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይህን ስልጣን እንዲያጣ አያደርገውም በሚል የልዩነት ሀሳባቸውን አስመዝግበዋል። መሃል ዳኛው ለብይኑ መንስኤ በሆነው ምክንያት ልዩነት ቢያስመዘግቡም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ”ሽብር” ጉዳይን የማየት “ተፈጥሯዊ መብት” አለው በሚል በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጉዳዩ ሊታይ አይገባም በማለት በብይኑ ውጤት ከሌሎች ዳኞች ላይ ተስማምተዋል።
~ በእነ አስቻለው ደሴ ክስ መዝገብ አንደኛ ተከሳሽ እና ህዳር 14/2010 ሱሪውን አውልቆ በምርመራ ወቅት ብልቱ መኮላሸቱን ያሳየው አስቻለው ደሴ አሁንም ህይወቱ አደጋ ውስጥ መሆኑን ተናግሯል። አስቻለው ደሴ ምንም አይነት ጥፋት ሳያጠፋ ጨለማ ቤት ታስሮ እንደሚገኝና አሁን የታሰረበት ሁኔታ ለህይወቱ አስጊ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ ተናግሯል። አባ ገ/ እየሱስ ኪዳነ ማርያም ጨለማ ቤት መታሰራቸውን ገልፆአል። ” አባ ገ/እየሱስ ዘ ዋልድባ ተደብድበው፣ ተሰባብረው እኔ ጋር ጨለማ ቤት ነው ያስረው ያሉት” ሲል አባ ገ/እየሱስ ስለታሰሩበት ሁኔታ ገልፆአል።
~ ከክፍለ ሀገር የመጡ ቤተሰቦቹ ፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ በፖሊስ መያዛቸውን ገልፆ፣ ለምን እንደተያዙና የት እንደሚገኙ እንዲጣራ በጠየቀው መሰረት ቤተሰቦቹን የያዘችው ፖሊስ የአስቻለው ቤተሰቦች እጃቸውን አጣምረው ለተከሳሹ ሰላምታ ሲሰጡ በማየቷ እንደያዘቻቸውና መክራ እንደለቀቀቻቸው ገልፃለች። አስቻለው ደሴ “ካላየኋቸው አላምንም” በማለቱ ፍርድ ቤቱ “ዘመነኛውን የተቃውሞ ምልክት አሳይተው መለስኳቸው ብላለች። ከዚህ ግቢ ውስጥ እንዲህ አይነት ነገር አይደረግም” ብሏል።
~በአስቻለው የክስ መዝገብ 4ኛ ተከሳሽ ማዕከላዊ በደረሰበት ድብደባ ምክንያት አንድ ጉድን፣ ኩላሊት እና ልቡ ላይ ጉዳት እንደደረሰበት ገልፆአል። በዚህም ምክንያት በአንድ ጉኑ ብቻ ለመተኛት መገደዱን፣ በቂ ህክምናም እያገኘ እንዳልሆነ ገልፆ “በቅርቡ ህይወቴ ያልፋል ብየ እሰጋለሁ” ሲል ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል። ማዕከላዊ የደበደቡት ቸርነት እና ተስፋዬ የተባሉ መርማሪዎችም እንዲጠየቁ አቤቱታ አቅርቧል።
~በእነ አብዱ አደም ክስ መዝገብ የተከሰሱ 7 ግለሰቦች አንድ የአቃቤ ህግ ምስክር ለመስማት በሚል 6 ጊዜ እንደተቀጠረባቸው በመግለፅ ምስክርነቱ እንዲታለፍ ጠይቀዋል። አድራሻው ሻሸመኔ ነው የተባለውን ምስክር ለመስማት በተደጋጋሚ እንደተቀጠረባቸው የገለፁት ተከሳሾቹ ምስክርነቱ ታልፎ እንዲበየንላቸው ጠይቀዋል።
~ 1ኛ ተከሳሽ :_
” ከታሰርን አንድ አመት ከአራት ወር ሆኖናል። እኔ ተማሪ ነኝ። ከትምህርት ቤት ነው የተያዝኩት። አባቴ የ70 አመት አዛውንት ናቸው። በሌላ መዝገብ ተከሰው ቂሊንጦ ታስረው ነበር። የተለያየ ዞን ታስረን ነበር። ለቤተሰብ ጥየቃ ስለማይመች በደብዳቤ ጠይቄ ከእኔ ጋር ታስረው ነበር። ነገር ግን ካቦ(የእስረኞች ኃላፊ) ይቀየር ብለው ስለጠየቁ ትናንት ማታ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደዋል። የት እንደሄዱ አላውቅም። ያሉበትን ሁኔታ ማወቅ እፈልጋለሁ።”
~እነ አበራ ለሚ ክስ መዝገብ ስር የተከሰሱ የመከላከያ ምስክር አሰምተዋል። ለ3ኛ ተከሳሽ ሆራ ከበደ የመከላከያ ምስክርነቱን የሰጠው ቡልቲ ተሰማ በእነ አበራ ለሚ መዝገብ ያሉ ተከሳሾች ላይ የመሰከረው ግለሰብ ስም እየቀየረ በተለያዩ መዝገቦች ክስ የቀረበባቸው እስረኞች ላይ እንደሚመሰክር አስረድቷል። ምስክሩ ሀምሌ 13/2009 ዓም በእነ አበራ ለሚ ክስ መዝገብ ሀብታሙ ፈይሳ፣ እንዲሁም ነሃሴ 6/2009 ደግሞ ጋድጌዳ ግርማ ብሎ በራሱ በአቶ ቡልቲ ላይ እንደመሰከረ ተገልፆአል።
~እነ መልካሙ ክንፉ ክሳቸው እንዲሻሻል በጠየቁት መሰረት ሁለት ጊዜ ተሻሻለ ተብሎ ሳይሻሻል መቅረቱን ገልፀዋል። በዛሬው እለት ለ3ኛ ጊዜ የተሻሻለ ነው የተባለ ክስ ተነቦላቸዋል። ፍርድ ቤቱ የአንደኛ ተከሳሽ መልካሙ ክንፉ ክስ መሻሻሉን ገልፆአል። ሆኖም ክሱ ከተነበበ በኋላ ተከሳሾች ይሻሻል የተባለው የ1ኛ እና 4ኛ ተከሳሾች መሆኑን አስታውሰው የተነበበላቸው የመጀመርያው ክስ እንጅ የተሻሻለ ነገር እንደሌለው ገልፀዋል። ባለፈው ቀጠሮ ፍርድ ቤት አቃቤ ህግ ክሱን አሻሽሎ በቶሎ ካላመጣ ተከሳሾቹን በነፃ አሰናብታለሁ እንዳለ አስታውሰው ቃሉን እንዲጠብቅ ገልፀዋል።
~ፍርድ ቤቱ የሟች አየለ በየነ ክስ እንዲቋረጥ በመወሰን ለአቃቤ ህጉ ትዕዛዝ ባስተላለፈበት ወቅት አቃቤ ህጉ አቶ መኩሪያ አለሙ “ተከሳሽ መሞቱን ሳላረጋግጥ ክሱን ማቋረጥ አልችልም” ብለዋል። ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ መስጠቱን በማስታወስ፣ የአስከሬን ምርመራ ማስረጃም መዝገቡ ጋር መያያዙን ገልፆአል። አቃቤ ሕጉ ይህን መረጃ ካገኘ ክሱን እንደሚያቋርጥ ገልፆአል። ፍ/ ቤቱ መዝገቡን አይቶ ክሱ ተሻሽሏል አልተሻሻለም የሚለውን አይቶ ለመበየን ለታህሳስ 10/2010 ዓም ቀጠሮ ይዟል።
~ በማስተር ፕላኑ ምክንያት የተነሳውን የህዝብ ተቃውሞ አስተባብሯል፣ የኦነግ አባላትን አደራጅቶ አመፅ መርቷል የሚል የ”ሽብር” ክስ የተመሰረተበት ጃራ ሃዋዝ 5 አመት ተፈርዶበታል።