የዋልድባ መነኮሳት ክሳቸው ተቋረጦ ከእስር ተለቀቁ
በፌደራል አቃቤ ህግ በሽብር ወንጀል ተከሰው ለበርካታ ወራት ታስረው የነበሩት የዋልደባ መነኮሳት ከእስር ተፈቱ። መነኮሳቱ ከዋልደባ ገዳም ታፍነው ለበርካታ ወራት ታስረው ጉዳያቸው በፍደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ችሎት ሲታይ ቆአይቶ በመጨረሻም ክሳቸው ተቋርጦ ተፈተዋል።
መነኮሳቱ ልደታ ፍርድ ቤት ሳሉ
መነኮሳቱ በአዲስ አበባ በሚገኘው ቃሊቲ ፌደራል ወህኒ ቤት ባሉ የጥበቃና የደህንነት አባላት ተደጋጋሚ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ይፈፀምባቸው እንደነበር አብቱታዎቻቸውን ለፍርድ ቤት ሲያቀርቡ እንደነበር ይታወሳል።
መነኮሳቱ አባ ገብረኢየሱስ ኪዳነ ማርያም፥ አባ ገብረሥላሴ ወልደኃይማኖት፥ መርጌታ ዲበኩሉ እንዲሁም አቶ ለገሰ ወልደሐና፥ አቶ ሀብታሙ እንየው ጨምሮ 114 የፖለቲካ እስረኞች ክሳቸው ተቋርጦ ከታሰሩበት ወህኒ ቤት ተለቀዋል።
በመጨረሻም፤ መነኮሳቱ ከእስር በመፈታታቸውን ፈጣሪን በማመስገን አሁንም በርካታ ዜጎች ፍርድ ቤት እንኳ ሳይቀርቡ ለዓመታት በውህኒ ቤት ያሉ እንዳሉ እና ሀገሪቱ ኢትዮጵያ እና ኃይማኖታቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን እስር ላይ እንዳሉ በማስታወስ ሁሉም ከእስር ነፃ ካልወጡ ራሳቸውን ከእስር እንደተፉ እንደማይቆጥሩ ተነግረዋል።
የዋልድባ ገዳም መነኮሳት አባ ገብረ-ሥላሴ ስና አባ ገብረ-ኢየሱስ የፍርድ ቤት ውሎ
ሀብታሙ ምናለ
የፌደራሉ ከፍተና ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ወንጀል ችሎት፤ የካቲት 30 ቀን 2010 ዓ. ም. በዋለው ችሎት የዋልድባ መነከሳት ባቀረቡት “የሰብዓዊ ጥሰት በማረሚያ ቤቱ ተፈፅሞብናል ፍርድ ቤቱ ተትዕዛዝ ይስጥልን!” ብለው ያቀረቡትን አቤቱታ ሰምቶ የማረሚያ ቤቱን ምላሽ ለመስማት ሲኾን ማረሚያ ቤቱም ምላሽ የሚለውን በደብዳቤ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡
ፍርድ ቤቱ ማረሚያ ቤቱ የሰጠውን ምላሽ እንደተመለከተው እና ውሳኔ እንደሚሰጥ አሳውቋል፡፡ አባ ገብረ ኢየሱስ ኪዳነ ማርያም “የተከሰስነውም የታሰርነው አንድ ላይ ቢኾነም እኔን ያለምንም ምክንያት ወደ ዞን አምስት በተለምዶ ጨለማ ወይም ቅጣት ቤት ወደሚባለው አዘዋውረውኛል፡፡ ተቀጥቼ ከኾነ ጥፋቴ ተነግሮኝ፤ ቅጣቴ ምን ያህል ቀን እንደኾነ አውቄ ቅጣቴን ልቀበል፤ ያለምንም ጥፋት ዝም ብዬ ነው፡፡ እየተሰቃየኹ ያለኹት ብዙ በደል ደርሶብናል፡፡ ከአመት በላይ ልብስ ሳንቀይር ቆይተን በቅርብ ቀን አንድ ምዕመን ልብስ አምጥቶልኝ እኔ ለመቀየር ችያለሁ፡፡
ነገር ግን አባ ገብረሥላሴ ከተያዙ ጀምሮ ምንም ልብስ ቀይረው አያውቁም። ሰዎች ልብስ ሲያመጡ ማስገባት አይቻልም፡፡ እያሉ እያስመለሱ ከአንድ ዓመት በላይ በአንድ ልብስ ብቻ ሳናወልቅ ቆይተናል፡፡ ኹለታችንም አብረን በአንድ ዞን የነበርነው ያለምክንያት በታትነውናል፡፡ ሰዎች ሊጠይቁን ሲመጡ የተለያየ ዞን በመኾናችን ጠያቂዎቻችን እክል እየገጠማቸው ነው፡፡ ወደነበርኩበት ዞን ልመለስ” ብለው ጠይቀዋል፡፡
ዳኞቹም፡- “ልብስ ለምን አይገባም?” ብለው የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች ሲጠይቁ መልስ መስጠት ባለመቻላቻው “ልብስ ማነው የሚያመጣላችሁ?” ብለው ዳኞች ሲጠይቁ ችሎቱን ሲከታተሉ ከነበሩት ወጣቶች መካከል ለአንዳቸው የሚኾን የምንኩስና ልብስ ገዝተው ይዘው ነበር፡፡ ልብሱን ሲያቀርቡ ዳኞቹ፡- “ጠባቂዎቹን ፈትሹና ስጧቸው!” ቢልም ፍቃደኛ አለመኾናቸውን ሲያሳዩ ዳኞቹ በቁጣ “ተቀበሉና ፈትሻችሁ ስጡ!” በማለት ሲያዙ የማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ወታደራዊ ሰላምታ በመስጠት ወደ ዳኞቹ ተጠግቶ ሊናገር ሲል ዳኞቹ፡- “የተባልከውን ብቻ አድርግ! ምንም ሌላ አያስፈልግም!” በማለት ልብሱ ተፈትሾ ለአባ ገ/ሥላሴ ተሰጥቷቸዋል፡፡
ፍርድ ቤቱም ያቀረቡትን አቤቱታ እና የተሰጠውን መልስ አይተው ውሳኔ ለመስጠት ለመጋቢት 5 ቀን 2010ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ መጋቢት 18 መደበኛ የክስ የሚቀጥል እና ምስክር እንደሚሰማባቸው ይታወቃል፡፡
አባ ገብረ-ኢየሱስ ዘዋልድባ፤ ተደብድበውና አካላቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶ ጭለማ እንደሚገኙ ተጠቆመ
በጌታቸው ሺፈራው
#የፌደራልከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ውሎ
” #አባገ/እየሱስ ዘ _ዋልድባ ተደብድበው፣ ተሰባብረው እኔ ጋር ጨለማ ቤት ነው ታስረው ያሉት” አስቻለው ደሴ
#እስረኞች ለህይወታቸው እንደሚሰጉ ገልፀዋል
#የዐቃቤሕግ ምስክር ስሙን እየቀያየረ በተለያዩ መዝገቦች እየመሰከረ ነው ተብሏል
#የአማራክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ ዛሬም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣኑን አጥቷል የሚል ብይን ተሰጥቶበታል
ፎቶ:- አባ ገብረ-ኢየሱስ ዘ-ዋልድባ
~የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ዛሬም (ህዳር 28/2010) የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣኑን አጥቷል የሚል ብይን ሰጥቷል። ፍርድ ቤቱ ብይን የሰጠው በእነ አስቻለው ደሴ መዝገብ የተከሰሱ 4 ግለሰቦች ወንጀል ፈፅማችኋል የተባልነው በአማራ ክልል በመሆኑ ጉዳያችንን ሊያየው የሚገባው የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው ብለው ላቅቡት የክስ መቃወሚያ ነው።
ብይኑን በአብላጫ ድምፅ የሰጠው ፍርድ ቤቱ በአዲስ አበባና ድሬዳዋ እንዲሁም ሶማሊ፣ አፋር፣ ሀረሪ(?)፣ ደቡብና ቤንሻንጉል ክልሎች የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶችየፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤትን ስራ ደርበውና ወክለው እንዲሰሩ ስልጣን ስለተሰጣቸው የአማራ ክልልን ጨምሮ ሌሎች ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣንን አጥተዋል ተብሏል።
በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ ወንጀል ችሎት ለቀረቡለት የክስ መቃወሚያዎች ከአዲስ አበባ፣ ድሬዳዋ፣ ሶማሊ፣ አፋር፣ ቤንሻንጉልና ሀረሪ(?) ክልሎች ውጭ ያሉ የክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣንን አጥተዋል ብሎ በተደጋጋሚ ብይን ሰጥቷል።
~ብይኑ የተሰጠው በአብላጫ ድምፅ ሲሆን የመሃል ዳኛው ዮሃንስ ጌስያብ ለሌሎች ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ስልጣን በሕግ መሰጠቱ፣ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይህን ስልጣን እንዲያጣ አያደርገውም በሚል የልዩነት ሀሳባቸውን አስመዝግበዋል። መሃል ዳኛው ለብይኑ መንስኤ በሆነው ምክንያት ልዩነት ቢያስመዘግቡም የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የ”ሽብር” ጉዳይን የማየት “ተፈጥሯዊ መብት” አለው በሚል በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጉዳዩ ሊታይ አይገባም በማለት በብይኑ ውጤት ከሌሎች ዳኞች ላይ ተስማምተዋል።
~ በእነ አስቻለው ደሴ ክስ መዝገብ አንደኛ ተከሳሽ እና ህዳር 14/2010 ሱሪውን አውልቆ በምርመራ ወቅት ብልቱ መኮላሸቱን ያሳየው አስቻለው ደሴ አሁንም ህይወቱ አደጋ ውስጥ መሆኑን ተናግሯል። አስቻለው ደሴ ምንም አይነት ጥፋት ሳያጠፋ ጨለማ ቤት ታስሮ እንደሚገኝና አሁን የታሰረበት ሁኔታ ለህይወቱ አስጊ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ ተናግሯል። አባ ገ/ እየሱስ ኪዳነ ማርያም ጨለማ ቤት መታሰራቸውን ገልፆአል። ” አባ ገ/እየሱስ ዘ ዋልድባ ተደብድበው፣ ተሰባብረው እኔ ጋር ጨለማ ቤት ነው ያስረው ያሉት” ሲል አባ ገ/እየሱስ ስለታሰሩበት ሁኔታ ገልፆአል።
~ ከክፍለ ሀገር የመጡ ቤተሰቦቹ ፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ በፖሊስ መያዛቸውን ገልፆ፣ ለምን እንደተያዙና የት እንደሚገኙ እንዲጣራ በጠየቀው መሰረት ቤተሰቦቹን የያዘችው ፖሊስ የአስቻለው ቤተሰቦች እጃቸውን አጣምረው ለተከሳሹ ሰላምታ ሲሰጡ በማየቷ እንደያዘቻቸውና መክራ እንደለቀቀቻቸው ገልፃለች። አስቻለው ደሴ “ካላየኋቸው አላምንም” በማለቱ ፍርድ ቤቱ “ዘመነኛውን የተቃውሞ ምልክት አሳይተው መለስኳቸው ብላለች። ከዚህ ግቢ ውስጥ እንዲህ አይነት ነገር አይደረግም” ብሏል።
~በአስቻለው የክስ መዝገብ 4ኛ ተከሳሽ ማዕከላዊ በደረሰበት ድብደባ ምክንያት አንድ ጉድን፣ ኩላሊት እና ልቡ ላይ ጉዳት እንደደረሰበት ገልፆአል። በዚህም ምክንያት በአንድ ጉኑ ብቻ ለመተኛት መገደዱን፣ በቂ ህክምናም እያገኘ እንዳልሆነ ገልፆ “በቅርቡ ህይወቴ ያልፋል ብየ እሰጋለሁ” ሲል ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል። ማዕከላዊ የደበደቡት ቸርነት እና ተስፋዬ የተባሉ መርማሪዎችም እንዲጠየቁ አቤቱታ አቅርቧል።
~በእነ አብዱ አደም ክስ መዝገብ የተከሰሱ 7 ግለሰቦች አንድ የአቃቤ ህግ ምስክር ለመስማት በሚል 6 ጊዜ እንደተቀጠረባቸው በመግለፅ ምስክርነቱ እንዲታለፍ ጠይቀዋል። አድራሻው ሻሸመኔ ነው የተባለውን ምስክር ለመስማት በተደጋጋሚ እንደተቀጠረባቸው የገለፁት ተከሳሾቹ ምስክርነቱ ታልፎ እንዲበየንላቸው ጠይቀዋል።
~ 1ኛ ተከሳሽ :_
” ከታሰርን አንድ አመት ከአራት ወር ሆኖናል። እኔ ተማሪ ነኝ። ከትምህርት ቤት ነው የተያዝኩት። አባቴ የ70 አመት አዛውንት ናቸው። በሌላ መዝገብ ተከሰው ቂሊንጦ ታስረው ነበር። የተለያየ ዞን ታስረን ነበር። ለቤተሰብ ጥየቃ ስለማይመች በደብዳቤ ጠይቄ ከእኔ ጋር ታስረው ነበር። ነገር ግን ካቦ(የእስረኞች ኃላፊ) ይቀየር ብለው ስለጠየቁ ትናንት ማታ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደዋል። የት እንደሄዱ አላውቅም። ያሉበትን ሁኔታ ማወቅ እፈልጋለሁ።”
~እነ አበራ ለሚ ክስ መዝገብ ስር የተከሰሱ የመከላከያ ምስክር አሰምተዋል። ለ3ኛ ተከሳሽ ሆራ ከበደ የመከላከያ ምስክርነቱን የሰጠው ቡልቲ ተሰማ በእነ አበራ ለሚ መዝገብ ያሉ ተከሳሾች ላይ የመሰከረው ግለሰብ ስም እየቀየረ በተለያዩ መዝገቦች ክስ የቀረበባቸው እስረኞች ላይ እንደሚመሰክር አስረድቷል። ምስክሩ ሀምሌ 13/2009 ዓም በእነ አበራ ለሚ ክስ መዝገብ ሀብታሙ ፈይሳ፣ እንዲሁም ነሃሴ 6/2009 ደግሞ ጋድጌዳ ግርማ ብሎ በራሱ በአቶ ቡልቲ ላይ እንደመሰከረ ተገልፆአል።
~እነ መልካሙ ክንፉ ክሳቸው እንዲሻሻል በጠየቁት መሰረት ሁለት ጊዜ ተሻሻለ ተብሎ ሳይሻሻል መቅረቱን ገልፀዋል። በዛሬው እለት ለ3ኛ ጊዜ የተሻሻለ ነው የተባለ ክስ ተነቦላቸዋል። ፍርድ ቤቱ የአንደኛ ተከሳሽ መልካሙ ክንፉ ክስ መሻሻሉን ገልፆአል። ሆኖም ክሱ ከተነበበ በኋላ ተከሳሾች ይሻሻል የተባለው የ1ኛ እና 4ኛ ተከሳሾች መሆኑን አስታውሰው የተነበበላቸው የመጀመርያው ክስ እንጅ የተሻሻለ ነገር እንደሌለው ገልፀዋል። ባለፈው ቀጠሮ ፍርድ ቤት አቃቤ ህግ ክሱን አሻሽሎ በቶሎ ካላመጣ ተከሳሾቹን በነፃ አሰናብታለሁ እንዳለ አስታውሰው ቃሉን እንዲጠብቅ ገልፀዋል።
~ፍርድ ቤቱ የሟች አየለ በየነ ክስ እንዲቋረጥ በመወሰን ለአቃቤ ህጉ ትዕዛዝ ባስተላለፈበት ወቅት አቃቤ ህጉ አቶ መኩሪያ አለሙ “ተከሳሽ መሞቱን ሳላረጋግጥ ክሱን ማቋረጥ አልችልም” ብለዋል። ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ መስጠቱን በማስታወስ፣ የአስከሬን ምርመራ ማስረጃም መዝገቡ ጋር መያያዙን ገልፆአል። አቃቤ ሕጉ ይህን መረጃ ካገኘ ክሱን እንደሚያቋርጥ ገልፆአል። ፍ/ ቤቱ መዝገቡን አይቶ ክሱ ተሻሽሏል አልተሻሻለም የሚለውን አይቶ ለመበየን ለታህሳስ 10/2010 ዓም ቀጠሮ ይዟል።
~ በማስተር ፕላኑ ምክንያት የተነሳውን የህዝብ ተቃውሞ አስተባብሯል፣ የኦነግ አባላትን አደራጅቶ አመፅ መርቷል የሚል የ”ሽብር” ክስ የተመሰረተበት ጃራ ሃዋዝ 5 አመት ተፈርዶበታል።