Tag Archives: Ethiopia

በርካቶችን ለሞት የዳረገው የኦሮሚያ – ሶማሌ ግጭት እስከ ትናንት አለመቆሙን መንግስት አስታውቋል

አለማየሁ አንበሴ
Abdi,kassa & Lemma
አቶ አብዲ መሐመድ፥ እቶ ካሳ ተክለብርሃን እና አቶ ለማ መገርሳ

በኦሮሚያ እና በሱማሌ ክልሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት እንደቀድሞ የወሰን ጉዳይ እንዳልሆነ የተጠቆመ ሲሆን፣ ትክክለኛ መንስኤው እየተጣራ መሆኑን ያስታወቁት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ፤ ግጭቱ እስከ ትናንት አርብ ድረስ በተለያዩ ቀበሌዎች መቀጠሉንና በርካቶች ተገድለው፣ ከ20 ሺህ በላይ ዜጎች መፈናቀላቸውን አስታውቀዋል፡፡

ለበርካታ ቀናት በቀጠለ ግጭት፤ የሠው ሕይወት ጠፍቷል፣ ንብረት ወድሟል፣ ዜጎች ተፈናቅለዋል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ግጭቱ በቅርቡ እንዲገታ ይደረጋል፤ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎችም በመሃል ገብተው የማረጋጋት ስራ ይሠራሉ ብለዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለ ማርያም ደሣለኝ፤ ከሁለቱ ክልል አመራሮች ጋር በግጭቱ ላይ በስልክ ውይይት ማድረጋቸውንና ግጭቱ እንዲቆም ማሣሠቢያ መስጠታቸውንም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡
በአካባቢው ለግጭቱ መባባስና ለሠው ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆኑ ለህግ እንዲቀርቡ ይደረጋል ያሉት ሚኒስትሩ፤ የመሳሪያ ትጥቅ የማስፈታት ስራም ይሰራል ብለዋል፡፡

የመከላከያ ሰራዊትና የፌደራል ፖሊስ በግጭቱ መሃል ገብቶ ለማረጋጋት ለምን ዘገየ ተብለው የተጠየቁት ሚኒስትሩ፤ ክልሎቹ ችግሮቹን በራሳቸው ይፈቱታል የሚል እምነት በመጣሉ ነው ብለዋል፡፡
በግጭቱ የሶማሊያ ሪፐብሊክ ኃይሎችና የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል መሳተፋቸው ተጣርቶ ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል ብለዋል – ሚኒስትሩ፡፡ ግጭቱ በታጠቁ አካላት የታገዘ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ እነዚህ የታጠቁ አካላት እነማን ናቸው የሚለው ግን እስካሁን ምላሽ አለማግኘቱንና በማጣራት ሂደቱ እንደሚታወቅ ተናግረዋል፡፡ ግጭቱ የህዝብ ለህዝብ አለመሆኑን ግን አስረግጠው በመግለፅ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሁለቱ ክልሎች የመንግስት ኮሚኒኬሽን ኃላፊዎች ጉዳዩን አስመልክቶ በየሚዲያው የሚያስተላልፏቸው መግለጫዎች፣ ግጭቱን ሊያባብሱ የሚችሉ በመሆኑ ከእንግዲህ በኋላ ግጭት አባባሽ መግለጫዎችን ከመስጠት እንዲቆጠቡ ዶ/ር ነገሪ አሳስበዋል፡፡

የኮሚኒኬሽን ኃላፊዎቹ ከዚህ ድርጊታቸው የማይቆጠቡ ከሆነ፣ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድም ሚኒስትሩ ጠቁመው፤ በሁለቱም የሚገለፁ አሃዛዊ መረጃዎችንም ገና ያልተጣሩ መሆናቸውንና መንግስት ሁኔታውን አጣርቶ እንደሚገልፅ አስታውቀዋል፡፡

የሶማሌ ክልል ግጭቱን አስመልክቶ ለቪኦኤ በሰጠው መግለጫ፤ በአወዳይ ከተማ 50 ሠዎች መገደላቸውን ሲገልፅ፣ የኦሮሚያ ክልል በበኩሉ፤ በአወዳይ ከተማ 18 ሰዎች መገደላቸውን፣ ከነዚህ ውስጥ 12ቱ የሶማሌ ተወላጆች፣ ቀሪዎቹ የኦሮሞ ጃርሶ ጎሣ አባላት መሆናቸውን አስታውቋል፡፡

የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ቃል አቀባይ አቶ አዲሱ አረጋ ትናንት ምሽት ባሰራጩት መረጃ፤በሰሞኑ ግጭት ከተፈናቀሉት ከ22ሺ በላይ ዜጎች በተጨማሪ አጠቃላይ የድንበር ግጭቱ ከተከሰተበት ከ2009 ጀምሮ 416ሺ807 ዜጎች መፈናቀላቸውን አስታውቀዋል፡፡

በአወዳይ የደረሠውን ግጭት ተከትሎ፣ ከሶማሌ ክልል ከ21 ሺህ በላይ ዜጎች ተፈናቅለው በጭናቅሠን፣ ባቢሌና ሐረር ከተሞች ተጠልለው እንደሚገኙ የኦሮሚያ ክልል ቃል አቀባይ አቶ አዲሱ አረጋንና ምንጮቹን ጠቅሶ ቪኦኤ ዘግቧል፡፡

የሱማሌ ክልል የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሃላፊ አቶ ኢንድሪስ አህመድ በበኩላቸው፤ “ሰዎች ከአካባቢው የተፈናቀሉት በግዴታ ሳይሆን በፍቃዳቸው ነው፤ ጥቃት አልተፈፀመባቸውም” ብለዋል፡፡ ምንጮች በበኩላቸው፤ የግዳጅ ማፈናቀል መፈፀሙንና በዜጎች ላይ ድብደባና እንግልት እንደደረሰባቸው ለመገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል፡፡

የሱማሌ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ሃላፊ አቶ ኢንድሪስ አህመድ፤ በአወዳይ ከተማ የደረሰውን ግድያ ተከትሎ ባስተላለፉት መግለጫ፣ የኦሮሚያ ክልል መንግስትን “የአሸባሪነት አላማ አራማጅ” በሚል የፈረጀ ሲሆን የኦሮሚያ ክልል ቃል አቀባይ በበኩላቸው፤ ፍረጃውን አጣጥለው፣ ከአንድ ክልልን ከሚያስተዳድር አካል የማይጠበቅ ነው ብለዋል፡፡

የሶማሌ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ሃላፊ ለቪኦኤ በሰጡት መረጃ፤ በአስራ አንድ የሶማሌ ወረዳዎች፣ ማንነታቸው ባልታወቀ አካላት በተሠነዘሩ ጥቃቶች፣ ከሁለት መቶ አስራ ሶስት ሰዎች በላይ ህይወት ማለፉን አስታውቀዋል፡፡ ይሄን ተከትሎም የሶማሌ ክልላዊ መንግስት፣ ለ5 ቀናት የሚቆይ ብሄራዊ የሃዘን ቀናት በክልሉ ማወጁንም ለማወቅ ተችሏል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፣የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የግጭቱን መነሻና የደረሰውን ጉዳት የሚያጣራ ቡድን ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ወደ አካባቢው መላኩንና ማጣራት መጀመሩን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደምሰው በንቲ ለአዲስ አድማስ አስታውቀዋል፡፡

ሰሞኑን የሁለቱ ክልሎች የመንግስት ኮሙኒኬሽን ኃላፊዎች በማህበራዊ ድረ-ገፆቻቸው የሚያሰፍሯቸው የእርስ በርስ ውንጀላዎች አስደንጋጭና ግጭቱን የሚያባብሱ መሆናቸውን አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ፡፡ ክልላዊ መንግስታቸውን ወክለው መልዕክት የሚለዋወጡ እንደማይመስሉና ኃላፊነት የጎደሏቸው እንደሆነም ተገልጿል፡፡
ምንጭ፡ አዲስ አድማስ

The world loves Ethiopian pop star Teddy Afro. His own government doesn’t.

By Paul Schemm

Teddy Afro

Tewodros Kassahun (Teddy Afro) Photo Credit: Ethionewsflash.

ADDIS ABABA, Ethiopia — Monday marked the first day of the new Ethiopian year, but it hasn’t been much of a holiday for Teddy Afro, the country’s biggest pop star.

First, the government informed him that his New Year’s concert was canceled. Then, on Sept. 3, police broke up the launch party for his successful new album, “Ethiopia,” in the middle of the sound check at the Hilton Hotel, claiming Teddy hadn’t received permission to hold the event.

“Asking for a permission to organize an album launch is like asking a permit for a wedding or birthday party,” Teddy wrote on his Facebook page. “This is unprecedented and has never been done before because it is unconstitutional.”

But government disapproval certainly isn’t anything new for Teddy: This year was his third straight aborted New Year’s concert. And even as “Ethiopia,” which briefly hit No. 1 on Billboard’s world music chart, could be purchased or heard on virtually every street corner in the capital, Addis Ababa, after its May release, Teddy’s songs were nowhere to be found on state radio and TV. An interview with a public TV network was even canceled at the last minute, prompting the resignation of the journalist involved.

At first glance, there seems to be nothing controversial about Teddy Afro, born Tewodros Kassahun, and his traditionally influenced pop songs about love, unity and the glory of Ethiopia. His tunes have earned him a rapturous audience both at home and among the vast Ethiopian diaspora.

If anything, Teddy is quite the patriot. He’s just the wrong kind of patriot.

Teddy’s music has increasingly focused on extended history lessons glorifying Haile Selassie, the last emperor of Ethiopia, who was overthrown by a communist coup in 1974, as well as the great kings of the 19th century. The title track of his 2012 album, “Tikur Sew,” for example, celebrated Emperor Menelik II and his defeat of Italian troops invading Ethiopia in 1896 — complete with a music video that was practically a war movie.

But those rulers came from the Amhara people, the ethnic group that has historically dominated the country and, according to other Ethiopian peoples, brutally repressed its rivals. “Wherever he faced fierce resistance, Menelik responded with the most barbaric and horrific forms of violence,” read a 2013 statement by activists from the Oromo people, who led a boycott campaign of the Heineken-owned brewery Bedele after it sponsored Teddy’s concerts.

Teddy’s celebration of historic Amhara rulers is dramatically different from the nationalism of the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front, which is dominated by a political party from the Tigrayan people. The government promotes Ethiopia’s ethnic diversity and uses “unity through diversity” as its slogan. Teddy’s songs — and his criticism of rising ethnic division in Ethiopia — seem like challenges to its vision of the country.

The government is also particularly sensitive at the moment. The ruling party has carefully crafted a narrative of progress and development for the country, created partly in response to the bitterness that followed Ethiopia’s 2005 elections. It was the country’s first free and fair vote, and the results were heavily disputed. Hundreds died in the ensuing unrest, and — whether intentionally or not — a then-newly released song from Teddy became part of the soundtrack of the protests.

Now the government’s narrative is starting to fray. The country’s largest ethnic group, the Oromos, recently spent a year and a half protesting its alleged marginalization, saying that government development plans seemed to leave Oromo areas behind. Hundreds of people died at the hands of security forces during protests, and the situation calmed down only after a 10-month state of emergency was called in October 2016. The Amhara region also saw protests against the government in the same period, during which some people attacked Tigrayans as “usurpers.”

Teddy “is instigating a quarrel during a very sensitive time for them,” said Seyyoum Teshome, an independent political analyst who has had run-ins of his own with the government.

Ethiopia’s government has been repeatedly criticized — albeit in fairly muted terms — by the United States and other countries for suppressing dissent. The Parliament is entirely under the control of the ruling party, and some of the most prominent opposition leaders, especially Oromos, are in prison. And while Teddy has insisted that he has nothing to do with politics, it appears that the government isn’t willing to take any chances on his music.

Source:-The Washington Post

FIRE AT BIGGEST STADIUM CONSTRUCTION SITE IN ETHIOPIA KILLS SEVEN, SEVERELY INJURES ABOUT A DOZEN; NEWS KEPT SECRET

AS 1.png
Families of the deceased were offered just 15,000 Birr (about US$640) as compensation while the injured have received medical treatments only

By Samuel Bogale

Addis Abeba, September 5/2017 – A fire that engulfed workers’ dormitory at the construction site of Adey Abeba Stadium, the biggest stadium Ethiopia is constructing, has claimed the lives of seven people so far while almost a dozen were burned severely, the survivors told Addis Standard.

Around 20 day laborers who came from various parts of the country in search of jobs were believed to have been inside their dormitory when the fire broke out on Saturday August 08/2017. Some of them were readying to sleep and others were preparing dinner when a gas cylinder exploded at about 8:00 PM local time.

Officials from the Chinese State Engineering Corporation Ltd (CSCEC), which is constructing the stadium in the capital Addis Abeba (near the Bob Marley Square), have refused to speak about the accident to the press, an silence that led the victims to believe is a deliberate silence to protect the company’s interest and its image.

AS2.png
Desta Zeleke is currently receiving treatment at Menelik II Hospital

Addis Standard has confirmed the incident by visiting Desta Zeleke, one of the dozen badly injured worker who is currently receiving medical treatment at Menelik II Hospital and several other victims who were already discharged from hospitals.

Wondosen Demeke, Omer Abdela and Yalew Tsehaye, who had their legs and hands burned but had already left hospital, told Addis Standard that five of the deceased: Gutema Meshu, Shuferi Abdurahman, Aliye Mohammed, Kediro Midaso and Dita Geleto had come from Torban Hansawe Woreda in Shashemene, 250 km south of Addis Abeba; while two of them: Berihun Belay and Mengistu Dibash, came from Wolo, 508 km north east of Addis Abeba. Their bodies have all been sent to their families.

AS3.png
Wondosen Demeke, Omer Abdela &Yalew Tsehaye are discharged fromthe clinic and they want to go back to their birth places

Alemnew, another laborer who wanted to be identified by his first name only, also confirmed the accident and said it was caused by an explosion from a gas cylinder. He survived unscathed because he “was outside the dormitory” he told Addis Standard. Another victim who was badly injured by the fire is Getachew who left the city and “went to his family,” according to Alemnew. No one knew Getachew’s current location.

Chen, who is the site manager of CSCEC, but only wanted to give his first name, admitted to Addis Standard that the accident has indeed happened but refused to show the place or give more details of the accident. When asked if he was willing to show Addis Standard the scene of the accident, he said it was already “demolished and not safe [to visit].”

The victims were first taken to Haya Hulet health center, a government clinic, but later on they were transferred to various government hospitals. There was also a time lapse, as there were not enough ambulances to take the victims to hospitals.

“It was beyond our capacity to handle so we took many of the victims to Zewditu Memorial Hospital and a few of them to Yekatit 12 and Addis Hiwot Hospitals in a [crowded] ambulance, putting one victim on top of another,” said one of the nurses at the clinic in Haya Hult. The ones admitted to Zewuditu Memorial Hospital were subsequently referred to Menelik II, Dejazmach Balcha Hospitals, and Addis Abeba Burn, Emergency and Trauma (AaBET) Hospital, which is under the administration of St. Paul Hospital.

The seven were pronounced dead in these three different hospitals on various dates. Addis Standard’s several attempts to reach out to the families of the victims were not successful as of the publishing of this story.

AS4
Berihun Belay came from South Wollo. He is one of the seven victims. He was only 19

Meager or no compensations

According to the information from some of the victims, the families of the deceased who came all the way from Shashemene and Wollo were promised 15,000 Birr (about US$640) each as compensations package to “avoid controversy and potential lawsuits”, but they declined to accept. In addition to that, they were also offered 4,000 Birr (about US$170) for burial costs, which was what they were paid so far. They used it to cover the cost of transporting the bodies of their loved ones to their respective places of birth.

Chen of CSCEC claims that his company has “given money” to the families of the deceased and is taking care of those who are in hospital and who were already discharged from hospitals after treatment, “even though it is not the responsibility of the company”; but he did not want to disclose the exact amount of money the company paid.

Saturday, September 2, 2017, was the last day of the medical treatment Wendosen, Omer and Yalew were receiving at the Haya Hulet clinic, where Addis Standard met them. They were joined by three of their colleagues who were discharged earlier from Yekatit 12 Hospital. They complained that they were discharged from Yekatit 12 Hospital to return back to their dormitories while the burns on their bodies were still hurting.

Wendosen, Omer and Yalew wanted to leave Addis Abeba on Monday, September 04, 2017 to their birth places after receiving their salaries, but that was not made available to them, Addis Standard has learned. They were told they would get a fixed payment of just 3,000 birr (about US$127) including compensations for their properties lost in the fire.

AS5.png
The dormitories for Chinese workers are by far better and safe

Work place abuses

According to the victims Addis Standard talked to, currently there are around 800 Ethiopians and close to 200 Chinese construction workers at the site. Among the Ethiopians, around half were living in the compound in 19 dormitories. Each dormitory, about the size of 90m² and is built from corrugated iron, houses 20 people on average. The workers also said that there was no fire distinguisher in and around the dormitories and parts of the dormitories were covered with plastic canvas, which has likely exacerbated the fire.
The story is different for the dormitories accommodating their Chinese co-workers; there, one dormitory hosts a maximum of four Chinese workers and is equipped with fire distinguishers and other safety equipment.

Following the fire accident, many of the dormitories where Ethiopian laborers lived were dismantled without replacements, forcing the laborers to live outside, but with no additional pay to compensate their housing expenses. Their Chinese colleagues were allowed to remain.

The salary of the employees at the construction site ranges from 80 -120 Birr (US$3-5) per day. Alemnew complains of labor exploitation and says Ethiopian laborers “work the same job [with their Chinese co-workers] every day,” but get paid “way too less.” Other laborers spoke of disputes and other trivial cases for which their salaries are often deducted as punishment.

The Ethiopian laborers are not also provided with construction safety equipment such as proper clothes, shoes and hand gloves. According to the nurse at Haya Hulet clinic, the clinic often treats laborers from the site for injuries both big and small sustained at their work places.

Chen, the project manager, denies that. According to him, the company provides all safety equipment except for “shoes”. The company pays 200 birr (about $US8.5) to each laborer to buy safety shoes for themselves, Chen claims. But many laborers deny receiving neither the money nor the safety shoes. “We only have helmets (and use to get a pair of gloves once a month) but it has been more than two months since we received the last pair of gloves,” said Alemnew.

Adey Abeba Stadium is the biggest stadium Ethiopia is building among a number of other stadiums both in Addis Abeba and in regional cities. Its design has been approved by FIFA standards. In January 2015, a deal was signed between Redwan Hussien, then Ethiopia’s Youths and Sport Minster and Song Sudong, Director of CSCEC, for the later to begin the construction of the stadium in two phases. The first phase of the construction is estimated to consume around 2.4b. Birr. When completed Adey Abeba Stadium is expected to hold up to 60,000 people. It will also contain other sport facilities such as basketball and volleyball fields as well as an Olympic size swimming pool.

CSCEC has done other big constructions in Ethiopia, including the new AU Headquarters, which was entirely funded by the Chinese government, and the 20-storey building for the headquarters of the National Oil Company (NOC). Currently it is also building the new 46-storey headquarters of the state owned Commercial Bank of Ethiopia (CBE).

Source: Addisstandard

የቂሊንጦ ቃጠሎና የሀሰት ክስ

ጌታቸው ሺፈራው

እስረኞች ውጩን ከሚናፍቁበት ጊዜያት አንዱ የበዓል ወቅት ነው። የውጩን ትዝታ ለመርሳት ከቤተሰብ የገባላቸውን ምግብና ገንዘብ ከሌሎች ጋር ተካፍለው በዓሉን በዓል ለማስመሰል ይሞክራሉ። ከቤተሰብ የሚገባላቸውን ገንዘብ አዋጥተው ዳቦ እና ፈንድሻ ያስገባሉ። የድምፅና የምግብ ውድድር ያዘጋጃሉ። ለበዓል ወጫቸው ይሸፍንላቸው ዘንድ ሌሎች ውድድሮችን ያዘጋጃሉ። ለምሳሌ አንዱ ተነስቶ ሽንት ቤቱን ” ከአሁን በሁዋላ በ1000 ብር አዘግቸዋለሁ። እንዲከፈት የሚፈልፍግ ካለ 1000 ብር ከፍሎ ያስከፍተው ” ብሎ ሽንት ቤቱን ይዘጋል። ጨረታ መሆኑ ነው። እስረኛው አዋጥቶ ወይንም አንዱ ሀብታም እከፍላለሁ ካላለ ሽንት ቤቱ ይዘጋል። ገቢው ግን ለእስረኛው ነው። አንዱ ተነስቶ በተለይ ሀብታሞቹን እንትና ጎላውን ከተሸከመ ይህን ያህል ብር እከፍላለሁ ይላል። ያ ሰው ወይ ጎላ መሸከም ይኖርበታል ወይንም ገንዘቡን ይከፍላል።የተጠራበት ሰውም ራስህ ተሸከም 2ሺህ ብር እከፍላለሁ ሊል ይችላል። ሌላው ተነስቶ ይህ ቲቪ ይዘጋና እኔ 600 ብር እከፍላለሁ ይላል። ተዋጥቶ ወይንም ሀብታም ተለምኖ ከፍሎ ያስከፍተዋል። ይህ ሁሉ ገቢ እስረኛው በአንድነት በዓልን ደመቅ አድርጎ እንዲውል ያግዛል። ከዚህ በተጨማሪ ቃል የሚገባ ይኖራል። ገንዘብ አሰባሳቢ ኮሚቴ ግዴታ የሚጥልባቸው እስረኞች አሉ። ቤተሰብ ይጠይቃቸዋል የሚባሉ።

ነሃሴ አጋማሽ ጀምሮ እስረኛው ለበዓል ገንዘብ ያሰባስባል፣ ያቅዳል። ነሃሴ 21 እነሰ 22 2008 ዓም ማታ ቂሊንጦ እስር ቤት ዞን 1 ያሉ ቤቶች አዳሩን ሲጨበጨብ እና ሲሳቅ ነበር ያደረው። በየቤቱ ያሉ ኮሚቴዎች ገንዘብ ማሰባሰቡን ተያይዘውታል። ቃል ለሚገባ ይጨበጨባል። እንትና ጎላ ይሸከም፣ ሽንት ቤት ዳር ይተኛ፣ በፓንት ክፍሉን እየዞረ ይሩጥ፣ አንድ ጀሪካን ውሃ ይሸከም፣ ይዝፈን………… ተብሎ ጨረታ ሲወጣበት ይሳቃል። አንዱ ጥጋበኛ ቲቪ ወይንም ሽንት ቤቱን አዘግቶ ሌላኛው ከፍሎ ሲያስከፍተው ይጨበጨባል! ቀን የተጫራቾች ጀብድ፣ የከፋዮች ልግስና አውልቀው ለሮጡት ፌዝ ሲወራ ይውላል። አንዱ ቤት ቅዳሜ ያደረገውን ሌላው እሁድ ይደግመውና ገንዘብ ይሰበስብበታል። የቂሊንጦ እስረኞች ነሃሴ መጨረሻ ያስቡ የነበረው ስለ በዓል ነው። ሌላ ነገር አልነበረም!

ነሃሴ መጨረሻ የቂሊንጦ ድባብ እንዲህ እየቀጠለ፣ በዓል እየቀረበ እስር ቤቱ አንድ ያልተጠበቀ ነገር ይዞ ብቅ አለ። አጣዳፊ ተቅማጥና ተውከት ተከስቷል በሚል ከነሃሴ 28/2008 ዓም ጀምሮ ከቤተሰብ ከደረቅ ምግቦች ውጭ እንደማይገባ የሚገልፅ ማስታወቂያ ተለጠፈ። ከዛ በፊትም ይህ ሀሳብ ቀርቦ እስረኛው እንደማይቀበል በግልፅ አስቀኝጦ ነበር። ነሃሴ 28 እና 29/2008 ተመሳሳይ የገንዘብ ማሰባሰብ ሊቀጥል አቅዶ የነበረው እስረኛ በምግብ መከልከሉ ምክንያት ትኩረቱ ተቀየረ። የእስረኛ ተወካዮች ለቂሊንጦ አስተዳዳሪዎች እስረኛው ደስተኛ እንዳልሆነ እና መነጋገር እንደሚያስፈልግ ቢገልፁም እነ ተክላይ ፈቃደኛ አልሆኑም። የእስረኛው ብቸኛ አማራጭ “ምግብ” ብሎ ለመጥራት የሚከብደውን እስር ቤቱ የሚያቀርበውን “ደያስ” አልበላም ማለት ነው። ምግብ መከልከል የሚጀምረው ቅዳሜ ነሃሴ 28 ነውና ቁርስ አንበላም አለ። በጆንያ የመጣው ዳቦና በጎላ የመጣው ሻይ ከቤት እንዳይገባ ተደረገ። ይህን ያዩት ፖሊሶች ከቆጠራ በሁዋላ ከፍተውት የሚሄዱትን የኮሪደር በር ዘግተው እስረኛው ወደ መስጊድና ቤተ ክርስቲያን፣ ካፌ፣ ፀጉር ቤት እንዳይሄድ ከለከሉ። እስረኛው በሩ እንዲከፈት ቢጠይቅም ፖሊሶቹ ፈቃደኛ አልሆኑም።

ቂሊንጦ ውስጥ እስረኛ ይደበደባል፣ ተገዶ የማረሚያ ቤት ልብስ ለብሷል፣ ፍርድ ቤት በተደጋጋሚ የወርና ለዛ በላይ ቀጠሮ ይሰጠዋል። እስረኛው በበርካታ ጉዳዮች ተማሯል። አሁን ደግሞ ምግብ ተከልክሏል። ይህ በሆነበት በር ዘግተውበት ወጥተዋል። ይህ ሁሉ የሚደርስበት እስረኛ በር ዘግተውበት የሄዱ ፖሊሶች ላይ ጩኸት ማሰማት ጀመረ። በተነሳውግርግር ከክላሽ አልፎ መትረየስ ወደ እስረኛው ተተኮሰ። በዚሁ ሰዓት ዞን 2 እና ዞን 3 እየነደደ ነው። በሁሉም ዞኖች አሮጌ ፍራሾች ስለተቃጠሉ እስር ቤቱ በጭስ ታፍኗል። ፖሊስ የሚተኩሰው አስለቃሽ ጭስ እስር ቤቱን የባሰ በጭስ እንዲታፈን አድርጎታል። በዚህ በታፈነ እስረኛ ላይ የእሩምታ ተኩስ ይተኮሳል። ዞን 2 እና ዞን 3 ቤቶቹ በመቃጠላቸው እስረኛ ሊያልቅ ሲሆን ፖሊስ የዘጋውን በር ከፈተ። እስከዛ ሰዓት ድረስ ግን ብዙ እስረኞች ሞተዋል። ቆስለዋል። የመተንፈሻ አካል በሽታ ያለበት ውሃ እየተደፋለት፣ ሻወር ቤት ውስጥ ገብቶ፣ አፍና አፍንጫውን አፍኖ ለመትረፍ ችሏል። ራሱን ስቶ የወደቀው ብዙ ነበር።

የሌሎች ዞኖች እስረኞች ከወጡ በሁዋላ ፌደራል ፖሊስና እስረኛውን በማግባባት የዞን 1 በር ተከፍቶ እስረኛው ወደ ውጭ እንዲወጣ ተደረገ። መትረየስ በየቦታው ተጠምዶ እስረኛው ሜዳ ላይ ተቀመጠ። ከቆይታ በሁዋላ እስረኛው በየ ተራ ወደ ውጭ እንዲወጣ ሲያዙ እስረኛውም የተሻለ ቦታ ይወስዱናል የሚል ተስፋ ነበረው። ሆኖም የያዘውን እቃ እያስጣሉ፣ ጫማውን እያስወለቁ፣ በካናቴራና በቁምጣ ( ልብስ ያለው እንኳ ልብስ እንዳይደርብ ከልክለው ) ወደ አንድ ሰፊ አዳራሽ አስገቡት። ቀሪው ዝናብ እየወረደበት ሜዳ ላይ ተቀመጠ። ማታ 12 ሰዓት አካባቢ አዳራሽ ውስጥ እና ሜዳ ላይ ከነበረው ወደ ዝዋይና ሸዋ ሮቢት መጫን ጀመሩ። እስረኛ በሚጫንበት ወቅት በ”ሽብር” ክስ ገብተው የማረሚያ ቤቱን አስተዳደር የሚጠይቁ እስረኞች እየተለዩ ለብቻ ተያዙ። አግባው ሰጠኝ የመጀመሪያ ስሙ የተጠራ እስረኛ ነበር። ብዙዎቹ እየተለዩ ተደብድበዋል።

ሸዋ ሮቢትና ዝዋይ ከተወሰዱት ውጭ የቀሩት ዶፍ ሲጥልበት ውሎ ከጨቀየው ሜዳ ላይ እንዲያድሩ ተደረገ። እስከ ነሃሴ 29 11 ሰዓት እዛው ጭቃ ላይ ታግተው ዋሉ። ፀሀይና ዝናብ እየተፈራረቀባቸው። ከነሃሴ 30/2008 ጀምሮ ደግሞ እየተገረፉ በባዶ እግራቸው ሶስቱንም ዞን በግዳጅ እንዲያፀዱ ተደረገ። ለ15 ቀን ያህል እየተደበደቡ የግዳጅ ስራ ከሰሩ በሁዋላ ወደ ዝዋይ እስር ቤት እንዲዛወሩ ተደረገ።
እስረኞች ወደ ዝዋይና ሸዋሮቢት ተወስደው በርካታ የትህነግ/ኢህአዴግ አባላት ግን ቂሊንጦ እንዲቆዩ ተደረገ። እነዚህ አባላቱ ቂሊንጦ የቆዩት እስር ቤቱ ውስጥ ትህነግን የሚቃወሙ እስረኞችን ቀድመው ስለሚያውቋቸው እንዲጠቁሙ ነው። ካድሬዎቹ በስም የማያውቋቸው ነገር ግን ገዥዎቹን ሲቃወሙ የሰሟቸውን ይለዩ ዘንድ ደግሞ ሸዋ ሮቢትና ዝዋይ የነበሩ እስረኞች ፎቶ ተነስተው ፎቷቸው ወደ ቂሊንጦ ተላከላቸው። ሸዋሮቢትና ዝዋይ አብረው የሄዱ ካድሬዎችን ትህነግ/ ኢህአዴግን ሲቃወም ያዩትን፣ የሰሙትንና እስር ቤት ውስጥ ከአስተዳደሮቹ ጋር የማይስማማው ስም አሳልፈው ሰጡ። አቃጥለዋል በሚል የሀሰት ክስ ለመበቀል!

በነሃሴ ወር 2007 ውጭ ተቃውሞ የበረታበት ስለነበር፣ እስር ቤቱ ይቃጠላል ተብሎ ባይገመትም በአሳሪዎቹም በኩል ስጋት፣ በእስረኛው በኩል ደግሞ ተስፋ ነበር። በተለይ የእስር ቤቱ አስተዳዳሪዎች ውጭ በሞቀ ቁጥር የሚጠሏቸውን እስረኞች ያስፈራሩ ነበር። ምግብ በመከልከሉ ምክንያት ነሃሴ 26/2008 ዞን 3 መጠነኛ ተቃውሞ ታይቶ ስለነበር ዞን 1 የነበረው አግባው ሰጠኝ ተጠርቶ ” አንድ ነገር ቢፈጠር እንገድልሃለን!” የሚል ማስፈራሪታ ደርሶታል። ከቀጠሎው በሁዋላ ገና ምርመራ ሳይጀመር የቂሊንጦ አዛዦች” ከኦነግ ተከሳሾች በቀለ ገርባን፣ ከግንቦት 7 ደግሞ አግባው ሰጠኝ ዋና ተከሳሾች ናቸው” ብለው ለራሳቸው ሰዎች ተናግረዋል። ቀድመው ማን መከሰስ እንዳለበት ወስነዋል።

ትህነግን ስለሚቃወሙ ብቻ በቃጠሎው እጃቸው አለበት ተብለው የተጠረጠሩት እስረኞች ወደ ሸዋ ሮቢት ተወስደው ሰቆቃና ስቃይ ደርሶባቸዋል። እንደሚታረድ በግ ተሰቅለው ተገርፈዋል። መስቀል አደባባይ ላይ እንዳይደገም ብለው ሀውልት የሰሩት ሰዎች ሸዋ ሮቢት ላይ የቀይ ሽብርን ግርፋት ደግመውታል። ጫካ ውስጥ ወስደው ” ብትፈልግ በአማርኛ፣ ብትፈልግ በኦሮምኛ፣ ብትፈልግ በእንግሊዘኛ ጩኽ! ማን እንደሚደርስልህ እናያለን” እያሉ የባዕድ ሀገር ዜጋ አድርገው ገርፈዋቸዋል። እነዚህ እስረኞች በእስር ቤቱ አስተዳደር ጥርስ ውስጥ እንደገቡ ስለሚያውቁ በቃጠሎው ወቅት ከቤት አልወጡም፣ ቤቱ መንደድ ሲጀምርም ወጥተው ከፖሊስ ጋር አልተጋተሩም። እነ ማስረሻ ሰጤ፣ አበበ ኡርጌሳን የመሰሉት ጨለማ ቤት ፣ ፍቅረ ማርያም አስማማው ዝዋይ፣ ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ደግሞ ቃሊቲ ነበሩ። ግን ለቂሊንጦ እስር ቤት ቃጠሎ ተጠያቂ ተደርገዋል። ድራማ የማይችሉት አሳሪዎች እስር ቤቱን ሰብሮ ለማምለጥ እስረኞች 20 ያህል ሆነው ቴኳንዶ ይሰለጥኑ ነበርም ብለዋል።

ለቂሊንጦ እስር ቤት ቃጠሎ ምንም ገንዘብ አስፈላጊ አልነበረም። ሆኖም የእስረኛውን ልብስና ንብረት ሲወርሱ ገንዘብም ይዘዋል። ወደ ዝዋይ ከተጫኑት እስረኞች ብቻ ከ170 ሺህ ብር በላይ ወርሰዋል። ልብሱን በጆንያ እየጫኑ ውጭ ላሉ ሰዎቻቸው አስረክበዋል። በተለይ ይህ ቃጠሎ ይመጣል ብሎ ያላሰበው እስረኛ ለበዓል በቅጣትና በሌሎች መንገዶች በየቤቱ ብር ሰብስቦ ነበር። ይህንና እስረኛው በግሉ ያስቀመጠውን ብር የቀሙት አሳሪዎቹ ገንዘቡ ለቃጠሎ ማስፈፀሚያ የገባ ነው አሉ። ይህም አንደኛ የእስረኛውን ገንዘብ ለመቀማት ሲሆን በሌላ በኩል የእስር ቤቱ ቃጠሎ ታስቦበት እና ሆን ብሎ የተደረገ ለማስመሰል ነበር። በዚህ አልበቃቸው ስላለ በምርመራ ወቅት እስረኞች ብር እንደገባላቸው እንዲያምኑ ተደረገ። ለዚህ የጦስ ዶሮ የሆኑት ደግሞ ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ናቸው። እስረኞቹ በሀሰት እንዲያምኑ በተደረገው መሰረት ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ከ1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር በላይ ለቃጠሎው ማስፈፀሚያ እንዳስገቡ ተደርጎ ቀርቧል።

ግንቦት 7፣ ኦነግና አልሻባብ የት እንዳሉ የማያውቋቸው እስረኞች ከእነዚህ ድርጅቶች ጋር በመገናኘት እስር ቤቱን ሰብረው ወደ ድርጅቶቹ ሊቀላቀሉ ነበር ተብለው ተከሰሱ። እነዚህን እስረኞች ወደ ኤርትራ፣ ወደ ኬንያ እና ሶማሊያ ለማጓጓዝ 80 አውቶቡስ እስር ቤቱ አጠገብ ቆሞ እየጠበቀ ነበር ተብሎ የፈጠራ ክስ ቀርቦባቸዋል።

በቃጠሎወረ ወቅት በተተኮሰ ጥይት በርካቶች ቆስለዋል። ሞተዋል። ሆኖም በምርመራ ወቅት እስረኞች በእሳትና በጥይት የተገደሉትን ” እኔ ነኝ የገደልኩት” ብለው እንዲያምኑ ተደርገዋል። አንድ ሰው እስከ 5 ሰው ገድለሃል ተብሏል። ምርመራው አሰቃቂ ስለነበር ያልሞተ ሰው ሁሉ ገድያለሁ ያለ እስረኛ አለ። እስረኞች የሚድሩበት ቆርቆሮ ቤት ነው። ከጎኑ ደግሞ ሶስት መግረፊያዎች አሉ። አንድ እስረኛ ሲገረፍ ሌላው የሚሆነውን ይሰማል። ከ170 በላይ እስረኛ ተሰቅሎ ሲገረፍ ሌላው ይሰማል። በዚህ ሁሉ መከራ የስነ ልቦና ችግር ያጋጥማል። ይህን ሁሉ ሰቆቃ ሲሰማ የሰነበተ አንድ እስረኛ ሳይገረፍ ገና ወደ ምርመራ ክፍሉ ሲገባ ያልገደለውን ገደልኩ ብሏል። እስረኛው ማንን እንደገደለ ሲጠየቅ ” ጠሃን እኔ ነኝ የገደልኩት “ይላል።

መርማሪዎቹ አልተስማሙም። ጠሃን በተመሳሳይ ሁኔታ ለሌላ ሰው አድለውታል። በዚህ መከራ ወቅት እንትናን ገድየዋለሁ ብሎ ከመርማሪው ይሁንታ ማግኘት ቀላል አይደለም። ከሰቆቃ ያድናል። እስረኛው አሁንም ሞቷል የተባለ ሰው ስም ጠርቶ እኔ ነኝ የገደልኩት ይላል። ሲሰማ የሰነበተው መከራ እንዳይደርስበት ነው። አሁን የጠራው ሟችንም ቀድሞ የተመረመረ “እድለኛ” ወስዶታል። እስረኛው በዚህ ሁኔታ እስከ አምስት ሰው እየጠራ ” እድሉን ይሞክራል”። አልቀናውም። በሙሉ ተይዘዋል። መርማሪውም ” ተይዘዋል” እያለ ሌላ እድል ይሰጠዋል። አምስተኛ ላይ የሰጠኝ ሙሉን ስም ጠራ። “እስኪ ቆይ” ብሎ መርማሪው መዝገቡን አገላበጠና ” ያዘው አልተያዘም! አለው። ሰጠኝ ሙሉን ገድለኸዋል ተብሎ ተከሰሰበት። የቂሊንጦ ድራማ እንዲህ ነው። ሰው ባልሰራው የሚከሰስበት ድራማ!

የእነ አቶ በቀለ ገርባ መከላከያ የመስማት ሂደት አቃቤ ህጉ እርቦኛል በማለቱ ምክንያት ተቋረጠ

ጌታቸው ሺፈራው

አቃቤ ህግ ለሚያቀርበው ጥያቄ ተደጋጋሚ መቃወሚያ የቀረበበት ሲሆን መሃል ላይ “አርብ እንደመሆኑ እኛ ለምሳ መውጣት ያለብን 5:30 ላይ ነው። የምሳ ሰዓታችን ይከበር” ብሎ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት መጠነኛ ክርክር ተደርጓል።

ሌላ አቃቤ ህግ ስለነበር ፍርድ ቤቱ ሌላኛው አቃቤ ህግ ራበኝ ያለውን ተክቶ የሚሰራበት አጋጣሚ ስለመኖሩ ቢጠይቅም ራበኝ ያለው አቶ አንተነህ የተሰየመው እሱ ብቻ መሆኑን ገልፆአል።
” እኔም ከጤናዬ አንፃር ሊታሰብልኝ ይገባል።ጨጓራ አለብኝ። መብላት አለብኝ” ብሏል አቶ አንተነህ።

የቀኝ ዳኛው አቃቤ ህጉ ያነሱት ጥያቄ መስቀለኛ ጥያቄ ሳይጀመር ቢሆን ኖሮ ተገቢ ይሆን እንደነበር ገልፀው መታገስ እንደሚገባ በመጠቆማቸው አቃቤ ህጉ ” ትክክል ነው። ታግሼ መስራት እንዳለብኝ አውቃለሁ። እዚህ ቦታ ላይ ቆሜ የምሰራው ጤና ሲኖረኝ ነው። ህመሜን እያዳመጥኩ ልጠይቅ አልችልም።” ብሎ የምሳ ሰዓቴ ይከበር የሚለውን ጥያቄ ገፍቶበታል።

አቶ በቀለ ገርባ በበኩሉ ” ይህ ከዚህ ትልቅ ተቋም የሚጠበቅ አይደለም። እኛ እየተራብን፣ ብዙ መከራ እያየን ነው ያለነው። ህዝቡም የፍትህ ሂደቱን እንዲያይ ነው። አቃቤ ህግ ከተለየ አካል ትዕዛዝ ሊቀበል ካልሆነ በስተቀር ይህ በምክንያትነት ሊቀርብ አይገባም” ብሏል።

መሃል ዳኛው” ከዚህ ወንበር ተቀምጠን ትዕዛዝ መስጠት አለብን። ሁለት አቃቤ ህጎች ስላሉ አንዱ ተክቶ ሊሰራ እንደሚችል እንረዳለን። ይህ የትዕዛዝ ጉዳይ አይደለም።” ቢልም ሂደቱ ተቋርጦ ለምሳ ተወጥቷል።
ይህ የምሳ ሰዓት ይከበር ጥያቄና ክርክር በታዳሚውና ተከሳሾች ሳቅ የታጀበ ነበር።

በሌላ በኩል በእነ ጉርሜሳ መዝገብ ያሉ ተከሳሾች ነሃሴ 9 ቀን 2009 ዓ.ም. ምሳ እንዳይበሉ የተከለከሉ ሲሆን በወቅቱ የከለከሉት አመራሮች ተጠይቀው በማረሚያ ቤቱ ደንብ መሰረት መከልከላቸውን ገልፀው ነበር። ይሁንና ደንቡ ለእስረኞች የተመጣጠነ ምግብ እንደሚያቀርብና፣ ፍርድ ቤት ለሚውሉ እስረኞች ምሳ ተብሎ የሚቀርበው አንድ ደረቅ ዳቦ ያለማወራረጃ በመሆኑ ደንቡ ጋር የማይሄድ ስለሆነ የከለከሉት አዛዦች ጥፋተኛ መሆናቸውን ፍርድ ቤቱ ወስኗል።በዚህም መሰረት አዛዦቹ ፍርድ ቤት ቀርበው ይቅርታ ጠይቀው ታልፈዋል።

ዛሬ አቃቤ ህጉ የምሳ ሰዓቱ እንዲከበር ከጠየቀ በሁዋላ እስረኞቹም ምግብ እንዲገባላቸው የጠየቁ ሲሆን ፍርድ ቤቱ “እንዲያውም እዚሁ ጥሩ ማስረጃ አለ። ሌላኛው ወገንም ተገቢውን ምግብ አግኝቶ መከራከር አለበት” ብሎ ለእስረኞች ምግብ እንዲፈቀድ ወስኖ ነበር። ይሁንና ፖሊሶች ተከሳሾቹ ምግብ እንዳይገባላቸው ከልክለዋል።