በኦሮሚያ ክልል የደረሰውን የሰብዓዊ ጉዳት አስመልክቶ በ33 ወረዳዎች ብቻ 103 ዜጎች መገደላቸውን የሚገልፅ ገለልተኛ የምርመራ ሪፖርት ይፋ ሆነ

ከህዳር አጋማሽ 2008 ዓ.ም. በምዕራብ ሸዋ ተጀምሮ በነበረው እና መላው ኦሮሚያ ክልልን ያዳረሰው ህዝባዊ ተቃውሞን ተከትሎ የደረሰው ሰብዓዊ ጉዳት ልዩ የምርመራ ሪፖርት መግለጫ ይፋ ሆነ፡፡ ልዩ መግለጫው ይፋ የሆነው መጋቢት 5 ቀን 2008 ዓ.ም. አዲስ አበባ በሚገኘው የሰመጉ ዋና ጽህፈት ቤት ሲሆን፤ መግለጫውም የ103 ዜጎች ህይወት መጥፋቱን አስታውቋል፡፡
ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ) ይባል የነበረውና በኋላም የሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ(ሰመጉ) እየተባለ የሚጠራው ብቸኛው ሀገር በቀል መነግሥታዊ ያልሆነ ገለልተኛ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅት ሲሆን፤ ባለፉት አራት ወራት በተጀመረውና እስካሁንም በቀጠለው የኦሮሚያ ክልል ህዝባዊ ተቃውሞ የሰብዓዊ ጉዳት ቀዳሚውን ልዩ መግለጫ ይፋ አድርጓል፡፡ ሰመጉ በ140ኛው የተቋሙ ሪፖርት “የኦሮሚያ ክልል በ18 ዞኖች እና በ342 ወረዳዎች የተከፋፈለ ሲሆን ሰመጉ ከ9 ዞኖች ውስጥ በ33 ወረዳዎች ብቻ ባደረገው የመስክ ምርመራ ባገኘው ውጤት መሰረት 103 ሰዎች የተገደሉ ሲሆን 57 ሰዎች በጥይት የመቁሰል እና ከባድ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡” ብሏል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ከተገደሉትና ከቆሰሉት በተጨማሪ በ22 ሰዎች ላይ ማሰቃየት እና ድብደባ መፈፀሙን፣ 84 ሰዎች መታሰራቸውን እንዲሁም 12 ሰዎች የደረሱበት ወይም ያሉበት አለመታወቁንም ጠቁሟል፡፡

ሰመጉ 34 ገፅ ባለው ልዩ መግለጫው እንዳስታወቀው ከሆነ፤ የደረሰው የሰብዓዊ ጉዳት ምርመራ የሚያካትተው ከህዳር 2 ቀን እስከ የካቲት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. የደረሱ የሰብዓዊ ጉዳቶች ብቻ መሆኑን አስታውቋል፡፡ በተለይ በምርመራ ወቅት ድርጅቱ የጋጠሙትን ችግሮችም የጠቀሰ ሲሆን በተለይም የገንዘብ ፣ የሰው ኃይልና የምርመራ መሳሪያ እጥረት፣ በሀገሪቱ ያለው የፖለቲካ ሁኔታ ውጥረት የተሞላበት በመሆኑ በኦሮሚያ ክልል በተከሰተው ቀውስ እንደልብ ተዘዋውሮ ለመስራት አለመቻል፣የመንግሥት የደህንነት እና የፀጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ጫና እና ክትትል ማድረጋቸው፣ ሕዝቡ ከፍተኛ ፍርሃት ውስጥ በመግባት ማንንም ሰው አለማመን እና መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆን ዋነኞቹ መሆናቸው ጠቅሷል፡፡
በክልሉ አሁንም በተለያዩ ቦታዎች ተቃውሞች መቀጠላቸውንም በመጥቀስ፣ ማንኛውም የሰብዓዊ መብት የሚመለከተው አካል የኢትዮጵያ መንግሥት የዜጎችን ሰብዓዊ መብት እንዲያከብር፣ እንዲያስከብርና እንዲያስጠበቅ ጫና እንዲያደርጉ ጠይቋል፡፡
ሙሉ መግለጫውን ከዚህ ቀጥሎ ያለውን መስፈንጠሪያ (ሊንክ) በመጠቀም ያገኙታል፡- http://ehrco.org/wp-content/uploads/2016/03/The-Human-Rights-Council-HRCO-140th-Special-Report-Amharic-Scanned-March-14-2016.pdf
በደቡብ ክልል ሱርማ በሚገኙ የሙርሲ ማኀበረሰብ ላይ የመንግሥት ልዩ ኃይል የወሰደው እርምጃና ያለተገባ አያያዝ በርካታ ኢትዮጵያውያንን አስቆጣ!
ቀኑ በትክክል ባይታወቅም ባለፈው ሳምንት የተከናወነ እንደሆነ የሚታመነውና በፖሊስ ቁጥጥር ስር ባልተገባ አያያዝ እርቃናቸውን ይታዩ የነበሩ በደቡብ ክልል በቤንች ማጂ ዞን የሚገኙ እና የደቡብ ኦሞ ዞን አጎራባች የሆኑት የሙርሲ ማኀበረሰብ በአካባቢው በመንግሥት ለማከናወን የታቀደውን የኩራዝ ስኳር ፕሮጀክት ማስፋፊያ ባደረሰባቸው ተፅዕኖ ተቃውሞ ማሰማታቸውን ተከትሎ የተሰጠ የመንግሥት ምላሽ መሆኑ እየተነገረ ነው፡፡

በተለይ በክልሉ ልዩ ኃይል ፖሊስ ቁጥጥር ስር የነበሩት የሙርሲ ማኀበረሰብ አባላት ኢሰብዓዊ በሆነና ለህይወታቸው በሚያሰጋ መልኩ እር በርስ በመጠላለፍ የታሰሩበት ሁኔታ ቁጣን ቀስቅሷል፡፡ ይንንም በተመለከተ የስርዓቱ ደጋፊዎች ምስሉ ኢትዮጵያ ውስጥ የተፈፀመ ሳይሆን ደቡብ ሱዳን በሚል ለማስተባበል ከመሞከራቸው በስተቀር ከመንግሥት በኩል የተሰጠ ምላሽ የለም፡፡

መረጃዎች እንደሚያሳዩት በቁጥጥር ስር የነበሩት የሙርሲ ማኀበረሰብ እርቃናቸውን እር በርስ በአሰቃቂ ሁኔታ ካሰሯቸው መካከል የሁለቱ ፖሊስ አባላት ማንነት ከነ ምስላቸው በሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ኢትዮጵያውን መለየት መቻላቸው ተጠቁሟል፡፡
ከታሰሩት ጋር ይታዩ ከነበሩት ፖሊሶች መካከል ሁለቱ ማንነታቸው የተለየ ሲሆን፤ እነሱም ኮንስታብል ደመቀ አራርሳ ወጊ የሚባል የወለንጪቲ ተወላጅ ሲሆን፤ ረዳት ኮንስታብል የኑስ ተማም ቦሬ የሚባል የዲላ ተወላጅ መሆናቸው ተጠቁሟል፡፡ በቁጥጥር ስር የነበሩ አካላትን ጭኖ የነበረው ተሽከርካሪ ንብረትነቱ እና ፖሊሶቹ ለብሰውት የነበረው የደንብ ልብስ የደቡብ ክልል ልዩ የፖሊስ ኃይል እንደነበርም መረጃዎች አመልክተዋል፡፡
ይሁን እንጂ፤ የፖሊስን ኢ-ሰብዓዊ አያያዝ በተመለከተ የረህ እስከተዘገበበት ድረስ ከኢትዮጵያ መንግሥት የተሰጠ ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ የለም፡፡
በአካባቢው ከዚህ በፊት መንግሥት ያለምንም በቂ ማኀበራዊና አካባቢዊ ተፅዕኖ ግምገማ እናያለ በቂ ካሳ ከ200 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ማፈናቀሉ ከፍተኛ ትችት አስከትሎ እንደነበር ይታወሳል፡፡
Increasing human rights violations and deaths from careless state-owned sugar plantation in the Omo Valley!
By Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE)
We in the Solidarity Movement for a New Ethiopia (SMNE) sounds an urgent emergency alert regarding the present endangerment of the people of the Omo Valley.
These fellow-Ethiopians are being threatened with human rights violations and atrocities by the TPLF/EPRDF’s troops in the region as the regime moves ahead to remove the people from their land in another crony development scheme for a state-owned sugar plantation on245,000 hectares of land with an additional 100,000 or more hectares of some of the most fertile land committed for other agricultural projects. Those who resist, face state-sponsored human rights crimes.
In all of Ethiopia, the 500,000 people of the Omo Valley may be among the most neglected of Ethiopians by the current TPLF/EPRDF regime.
These dark-skinned and marginalized tribes—the Bodi, the Mursi, the Kwego, the Suri, the Hamer, the Karo as well as others—have only been valued in Ethiopia for the tourism business they attracted due to their unique and primitive customs that have remained unchanged for centuries. Now, the TPLF/EPRDF has found a better use for their land and it does not include them.
The previous and present government of Ethiopia never did value them and even now, they do not see them as their own people. In the entire Diaspora of about a million Ethiopians, some experts suggest that only one person from Omo Valley is among them. This is an example of how marginalized these people are.

Not only have they been intentionally denied access to entering the 21st century—it would negatively impact tourism—they have also been denied access to clean water, education, health care and other opportunities to a much greater degree than most other marginalized groups.
Now, as their land is being taken away from them, they are also being denied their most prized asset, their indigenous land and water.
Just wait, the TPLF/EPRDF regime will suddenly pretend to be forcing the people from their land and into resettlement camps—where they have no means for independent sustenance—in order to “help” bring these people into the 21st century. Do not believe it! It is just an excuse to cover up for illegally stealing their ancestral land and they are ill-prepared to defend themselves!
The people of the Omo Valley are living in a nation set up under the flawed government policy of ethnic federalism. Each ethnic group is supposed to look after people of their own ethnicity, without the expectation that others will care about the rights, interests and well being of those outside their own groups. Because of this, the people of the Omo Valley are more deprived of their rights than many others. Who speaks for them?
Their land is being taken over by their own government without any consultation. The authorities did not care about them and now the people of the Omo Valley have taken matters into their own hands.

Some limited fighting has broken out and as the TPLF/EPRDF sends troops to silence them through intimidation, human rights crimes and secretive extra-judicial killings, they seem to think they can eliminate these people without the world knowing.
The people of the Omo Valley are depending on the world not caring about them, but the SMNE has already received information from the people and we want to warn the ethnic apartheid regime in Ethiopia to stop the human rights abuses against these people and if they do not, they will be found accountable.
We also call on other peace and justice loving Ethiopians to stand up with the people of the Omo Valley. They are us. The people of the Omo Valley may be deprived and they may have been used as commodities for tourism in the past, but to God and to us, they are precious, just like everyone else.
The establishment of the SMNE was to educate Ethiopians about the value of those outside our villages, tribes and regions. One of the SMNE goal was to eradicate this primitive thinking where some devalue the humanity of others and turn away in apathy to their pain and suffering.
This SMNE principle of putting “humanity before ethnicity” and caring about the freedom, justice and well being of others—neighbors near and far—is the basis for healthy societies and cooperative global partnerships.
We in the SMNE will continue investigate and gather evidence to be used for future prosecution so perpetrators of these crimes will face justice and not get away with these crimes.
The people of Ethiopia will hold them accountable under the rule of law that is not simply rhetoric.
If any think that they can commit crimes without being found out, you are wrong as we already have our sources from this remote region of the country. We will continue to monitor what is going on there.
As we stand up for the people of the Omo Valley, let it bring us together as one people of Ethiopia who stand up for the freedom, rights and well-being of all of us.
በኢትዮጵያ ለተከታታይ አራት ወራት የቀጠለው ተቃውሞ ላይ የሚፈፀመው ግድያና እስር መቀጠሉ አስመልክቶ ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አስታወቀ
ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የሆነው ሂውማን ራይትስ ዎች አራተኛ ወሩን ይዞ የቀጠለውን የኦሮሚያ ክልል ህዝባዊ ተቃውሞ ላይ መንግሥት በፀጥታ ኃይሉ በወሰደው የኃይል እርምጃ ሰዎች መደላቸውን፣ በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን እና መታሰራቸውን እንዲሁም ታግተው የደረሱበት ያልታወቁ ሰዎች መኖራቸውን በመግለፅ መግለጫ አወጣ፡፡

ሂውማን ራይትስ ዎች በመግለጫው “አጠቃላይ የተገደሉ ሰዎችን ቁጥር ለማረጋገጥ አልቻለም ምክንያቱም በኢትዮጵያ ያለው እንቅስቃሴ እና በነጻነት የመዘገብ ሁናቴ የተገደበ በመሆኑ ነው፡፡ ተሟጋቾች በተለይ ከማህበራዊ ድረ-ገፆችን መሰረት በማድረግ ባገኟቸው የቪዲዮ፣ የፎቶ እና የድረ-ገጽ ላይ ጽሁፎች መረጃዎች መሰረት ከኖቬምበር 12 ቀን ጀምሮ ከ200 በላይ ሰዎች መገደላቸውን ጠቁመዋል፡፡ ያለው መረጃ እንሚጠቁመው በበርካታ ሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታስረዋል፤ በርካቶቹ የት እንሚገኙም አይታወቀም፤ የሚገመተው በሃይል እንዲሰወሩ መደረጉን አስታውቋል፡፡

እ.አ.አ.ከህዳር ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል በስፋት እየተካሄደ ያለውን ሰላማዊ ተቃውሞ የኢትዮጵያ የጸጥታ ሃይል በጉልበት እያፈነው እንደሚገኝ ሂውማን ራይትስ ዎች አስታወቀ፡፡ ከ2016 ዓ.ም. መነሻ ጀምሮ በእየለቱ ሰዎች እንደሚገደሉ እና በዘፈቀደ እንደሚታሰሩ በመግፅ፤ የወታደራዊ ሰራዊትን ያካተተው የጸጥታ ሃይል ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ላይ የሚገኙ በርካታ ሰዎችን ቀጥታ በመተኮስ ገድሏል፡፡ በሺህዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ታስረው ያለምንም ክስ እንደታገቱ ይገኛሉ፡፡ ባለፉት ሳምንታት የተቃውሞው ድግግሞሽ የቀነሰ መስሎ ቢታይም አፈናው ግን ቀጥሏል፡፡” ይላል ፤በመግለጫው፡፡
የተቋሙን ሙሉ መግለጫ (በአማርኛ እና በእንግሊዘኛ) ለማግኘት የሚከተለውን ሊንክ ይጠቀሙ፤
ምንጭ፡ https://www.hrw.org/am/news/2016/02/21/287126
https://www.hrw.org/news/2016/02/22/ethiopia-no-let-crackdown-protests
ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ታሰረ
የነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ዛሬ ታህሣሥ 15 ቀን 2008 ዓ.ም. ጠዋት ለስራ ከቤቱ ሲወጣ በፌደራል ፖሊሶችና በደህንነት ሰዎች ተይዞ ታስሯል። የፀጥታ ኃይሉ መኖሪያ ቤቱን ከፈተሹ በኋላ ፣ጋዜጠኛውን ወደ ፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማዕከል ማዕከላዊ መስደው ማሰራቸው ቢገለፅም፤ መንግሥት ጋዜጠኛውን ለምን እንዳሰረ የገለፀው ነገር የለም፡፡
ጋዜጠኛ ጌታቸው የነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ ከመሆኑ በተጨማሪ የእንቁ መፅሔትም ፀሐፊ እንደነበር የሚታወቅ ሲሆን፤ ከዚህ በፊት በመንግሥት ኃይሎች ከፍተኛ ማስፈራሪያና ዛቻ ይፈፀምበት እንደነበርም ታውቋል፡፡ጌታቸው ነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣን እና ደረ- ገፅን ጨምሮ በተለያዩ ድረ-ገፆችና የራሱ ማኀበራዊ ገፅ ላይ የተለያዩ ሐሳቦችን ይፅፍ እንደነበርም ይታወቃል፡፡
ከጋዜጠኛ ጌታቸው በተጨማሪ በተደጋጋሚ ሲታሰሩና ሲፈቱ የነበሩት ሶስቱ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መካከል ዳንኤል ተስፋዬ፣ ኤርምያስ ፀጋዬ እና ቴዎድሮስ አስፋው ዛሬ መታሰራቸውን የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡

በተመሳሳይ ዜና ባለፈው ቅዳሜ ታህሣሥ 9 ቀን 2008 ዓ.ም. ጠዋት አዲስ አበባ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በፀጥታ ኃይሎች ተይዞ የታሰረውና የኦሮሚያ ሬዲዮናቴሊቪዥን ዜና አንባቢ ጋዜጠኛ ፈቃዱ ምረከና አለመፈታቱ ታውቋል፡፡ ይህ እስከተዘገበበት ድረስ ጋዜጠኛ ፈቃዱ ምርከናም ሆነ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው በምን ምክንያት እንደታሰሩ ከመንግሥት በኩል የተገለፀ ነገር የለም፡፡

ከጋዜጠኛ ፈቃዱ እና ጌታቸው በተጨማሪ በርካታ ጋዜጠኞች በእስር ላይ እንደሚገኙና በዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቾች ድርጅቶች፤ ኢትዮጵያም ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ የሁለተኛ ደረጃን ተቀዳጅታ እንደነበር አይዘነጋም፡፡