ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የሥራ መልቀቂያ አስገቡ

ጠቅላይ ሚኒስትር እቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የሥራ መልቀቂያ ማስገባታቸውን ዛሬ የካቲት 8 ቀን 2010 ዓ. ም. በፅህፈት ቤታቸው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አረጋግጠዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሥራ መልቀቂያቸውን በቅድሚያ በስልጣን ላይ ያለው የገዥው ፓርቲ አባል ለሆነውና ተወክለው ለመጡበት ለደኢህዴን እና ኢህአዴግ ከሊቅመንበርነት ለመልቀቅ ያስገቡት ጥያቄ ተቀባይነቱን ማግኘቱን አስታውቀዋል። ይህንንም ተከትሎ ከጠቅላይ ሚኒስትርነት ኃላፊነት ለመነሳት ለገዥው ኢህአዴግ ምክር ቤት ጥያቄ ማስገባታቸውንና ውሳኔያቸው ተቀባይነት አግኝቶ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሲፀድቅላቸው እንደሚንሱ ይጠበቃል።
Hailemariam Desalegn
አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ

ለረጅም ጊዜ በሥላጥን ላይ ቆይተው በሞት የተለዩት አቶ መለስ ዜናዊን በመተካት ከነሐሴ 2004 ዓ. ም. ጀምሮ በሥልጣን ላይ ያሉት አቶ ኃይለማርያም፤ ዛሬ በፅህፈት ቤታቸው በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በሰጡት ይፋዊ የሥራ መልቀቂያ መግለጫ እንዳስታወቁት ከሆነ በእርሳቸው ምትክ በፓርላማው ሌላ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር እስኪሾም ድረስ ሥራቸውን እንደሚቀጥሉ አስታውቅዋል። የሥልጣን መልቀቃቸውም በሀገሪቱ ያለውን ችግር ለመፍታት የመፍትሄ አካል አድርገው እንዳሰቡትም አስታውቀዋል።

Leave a comment