Category Archives: Social and Culture

የሆሳዕና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ተቃጠለ

የሆሳዕከና ከተማ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከመቃጠሉ በፊት

የሆሳዕከና ከተማ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ከመቃጠሉ በፊት

በደቡብ ክልል በከንባታ፣ሀዲያ፣ጉራጌና ስልጤ ሀገረ ስብከት፤ሆሳዕና ከተማ የሚገኘው ታሪካዊው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ጵጵስና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ተቃጠለ፡፡ የእሳት አደጋ ቃጠሎው የደረሰው ትናንት የካቲት 21 ቀን 2007 ዓ.ም. ሲሆን፤ የቃጠሎው መንስኤ እስካሁን አልታወቀም፡፡ በረደሰው ቃጠሎ የቤተክርስቲያኗ ህንፃ ላይ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰ ሲሆን፤ የጉዳቱ መጠን በአሀዝ ግን እስካሁን የተገለፀ ነገር የለም፡፡ በደረሰው የቃጠሎው አደጋ በቤተክርስቲያኗ የነበሩ ታሪካዊ ቅዱሳት መፃህፍትን ጨምሮ በርካታ ንብረቶች መውደማቸው የተገለፀ ሲሆን፤ የአካባቢው ህዝብ እሳቱን ለማጥፋት ባደረገው ርብርብ ታቦታቱን ከአደጋው ማትረፍ መቻሉን ከስፍራው የመረጃው ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡

እሳቱንም ለማጥፋት በተደረገው ርብርብ ከከተማው የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ተከታይ ምዕመናን በተጨማሪ በርካታ የአካባቢው የእስልምና እና የፕሮቴስታንት ኃይማኖት ተከታዮች በፍጥነት ደርሰው መሳተፋቸውንና በዚሀም ታሪካዊ የብራና መፅሐፍቱን እና ታቦታቱን ማዳን እንደተቻለ ከስፍራው የደረሱን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ጀቤተክርስቲያኗን ጨምሮ በቤተመቅደሱ ውስጥ ያሉ ሌሎች ንብረቶች በቃጠሎው አደጋ ሙሉ ሙሉ መውደዋማቸው ታውቋል፡፡ ይሄንንም የሀዲያ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣የዞኑ የፀጥታ ዘርፍ ዋና ኃላፊ፣ የከተማው የሆሳዕና ከተማ ከንቲባ፣ የከተማው የእስልምና እና የፕሬቴስታንት ኃይማኖት መሪዎች በስፍራው በአካል በመገኘት ቤተክርስቲያኗ ታንፃ ወደ ቀድሞ ይዞታ እስክትመለስ ድረስ በግላቸው አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ ለቤተክርስቲያኗ አስተዳዳሪዎችና ሰባካ ጉባዔ ቃል መግባታቸውም ተነግሯል፡፡ ነገ ሰኞ የካቲት 23 ቀን 2007 ዓ.ም. የሀገረ ስብከቱና የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቀለምኒጦስ በተገኙበት  የቤተክርስቲያኗ የህንፃ አሰሪ ኮሚቴ እንደሚዋቀርና የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብርም ይፋ እንደሚደረግ ከሆሳዕና የደረሰን መረጃ አመልክቷል፡፡

የሆሳዕከና ከተማ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የእሳት አደጋ በደረሰበት ወቅት

የሆሳዕከና ከተማ ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን የእሳት አደጋ በደረሰበት ወቅት

በሆሳዕና ከተማ በርካታ የመንግሥትና የህዝብ ተቅማት ቢኖሩም፤አሁን ከደረሰው የቤተክርስቲያን ቃጠሎ በተጨማሪ ከዚህ በፊት በደረሱ የእሳት አደጋዎች ከተለመደው የህዝብ ርብር ውጭ የከተማው መስተዳደር የእሳት አደጋ መከላከያ ዝግጅትም ሆነ መሳሪያ ባለመኖሩ በርካታ የንግድ ሱቆች ተቃጥለው በሚሊዮን የሚቆጠሩ ንብረቶች መውደማቸው አይዘነጋም፡፡

የካቲት 21 ቀን 2007 ዓ.ም.  በደረሰው ድንገተኛ የእሳት አደጋ ቃጠሎ ምክንያት 106 ዓመታት ዕድሜ ያስቆጠረው ታሪካዊው የሆሳዕና ደብረ ገነት ቅድስት ማርያም ቤተክርስቲያን ህንፃ ሙሉ ለሙሉ መውደሙ ይታወቃል፡፡ ስለሆነም በተቃጠለው ቤተክርስቲያን ምትክ አዲስ ህንፃ ቤተክርስቲያን ለማሰራት በይፋ እንቅስቃሴ በመጀመሩ፤ የገንዘብ ድጋፍ ማድረግ ለምትፈልጉ፡-

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣

ባቴና ቅርንጫፍ፤ ሆሳዕና

ዝግ የባንክ አካውንት ቁጥር  100 011 0719 969

መርዳት እንደሚቻል በመጠቆም፤ ለምታደርጉት ድጋፍ ሁሉ በቤተክርስቲያኗ ስም ከወዲሁ ማመስገኑን የህንፃ አሰሪው ኮሜቴ አስታውቋል፡፡

ለበለጠ መረጃ 

ሀገር ውስጥ ላሉ በስልክ ቁጥር 0912- 446829 ወይም 0913-750229

ከውጭ ሀገር ከሆነ  +254 912-446829 ወይም +254 913 750229  ማነጋገር እንደሚቻል የህንፃ አሰሪው ኮሚቴ አስታውቋል፡፡

በአዋሳ በደረሰው የእሳት ቃጠሎ የሟቾች ቁጥር ከ20 በላይ ነው ሲሉ የቃጠለው ሰለባ የሆኑ ሰዎች ገለፁ

የአዋሳ ከተማ ሲቲ ሴንተር አካባቢ

የአዋሳ ከተማ ሲቲ ሴንተር አካባቢ

በደቡብ ክልል ዋና ከተማ በአዋሳ የካቲት 14 ቀን 2007 ዓም በደረሰው ከፍተኛ የእሳት ቃጠሎ የሟቾች ቁጥር በመንግስት እንደተገለጸው አንድ ሳይሆን ከ20 በላይ መሆኑን ተገጂዎች ለኢሳት ገልጸዋል።

ከፍተኛ ንብረት ከወደመባቸውና እሳቱ ሲነሳ በስፍራው ከነበሩት መካከል አንዱ ለኢሳት ሲናገር፣ እርሱ የ6 ሰዎችን የተቃጠለ አስከሬን ማየቱን፣ በስፍራው የሚገኙ ጓደኞቹ ደግሞ በአጠቃላይ እስካሁን 27 አስከሬን ተፈልጎ መቀበሩን ተናገሩዋል።

አንድ ህጻነት እና አንዲት እናት ከ3 ልጆቿ ጋር ሞታ መመልከቱን፣ በማግስቱ ደግሞ ተጨማሪ ሁለት ሰዎች ሞተው ማየቱን የሚናገረው ግለሰቡ፣ የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች አካባቢውን ከነዋሪው በመከለል ማታ ማታ የተቃጠለ አስከሬን እየፈለጉ በመቅበር ላይ ናቸው ብሎአል። እናቶች አሁንም ድረስ ልጆቻቸውን እየጠየቁ ቢሆንም፣ በከንቲባው በኩል የሚሰጠው ምላሽ አሳዛኝ መሆኑን ግለሰቡ ገልጿል። ነዋሪዎቹ በመንግስት በኩል በቂ እርዳታ እንዳልተደረገላቸው በምሬት ተናግረዋል።

መንግስት የእሳቱን መነሻ እስካሁን ይፋ አላደረገም። ነዋሪዎች እንደሚሉት ግን መስተዳድሩ ቦታውን ለመሸጥ እሳቱን ሆን ብሎ አስነስቶታል። በጉዳዩ ዙሪያ የአዋሳን ከንቲባ ለማግኘት ያደረገው ተደጋጋሚ ሙከራም እንዳልተሳካ በመግለፅ ኢሳት ዘግቧል፡፡

በአዲስ አበባና በክልሎች በርካታ ኢትዮጵውያን ሙስሊሞች በመንግሥት እየታሰሩ መሆኑ ተሰማ

Ethio-muslims protest

ከጥር 2004 ዓ.ም. ጀምሮ በሀገር አቀፍ ደረጃ በይፋ የኃይማኖት ነፃነት መብትና ህገ-መንግሥቱ እንዲከበር፤ በሰላማዊ መንገድ እየጠየቁ የሚገኙት የኢትዮጵያ ሙስሊሙ ማኀበረሰብ  የመንግሥትን ህገወጥ እርምጃ ተቃውሞ መቀጠሉን ተከትሎ፤አሁንም በያዝነው የካቲት 2007 ዓ.ም. ከየቤቱና ከስራ ቦታ ጭምር የጅምላ እስሩ ተጠናክሮ መቀጠሉን ከአዲስ አበባና ከተለያዩ የክልል ከተሞች የሚመጡ መረጃዎች ጠቁመዋል፡፡ በተለይ በአዲስ አበባ የመንግሥትን ያይል እርምጃ እና የኃይማኖት ነፃነት መብታቸው እንዲከበርና መንግሥትም ከኃይማኖት ጣልቃ ገብነት እንዲወጣ በተደጋጋሚ መጠየቃቸውን ተከትሎ ሰሞኑን የጅምላ እስር እየተካሄደ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

Anuwar mosque protest

የጅምላ እስሩ እየተከናወነ የሚገኘው መንግሥት በመጪው ምርጫ 2007 ዓ.ም. ከሙስሊሙ ማኀበረሰብ ድጋፍ እንደሌለው በመረዳቱና በርካቶችም የድምፅ መስጫ በረቀት መውሰዳቸው የደረሰው መረጃ አስደንግጦት እንደሆነ ቢጠቆምም፤ ከመንግሥት በኩል ግን እየተወሰደ ስላለው የጅምላ እስር የተሰጠ  ምንም ዓይነት ማብራሪያም ሆነ ምላሽ ማግኘት አልተቻለም፡፡ በተለይ ሰሞኑን በተወሰደውና እየተወሰደ ባለው የጅምላ እስር ተጠናክሮ መቀጠሉን ከመጠቆም ባለፈ፤እስካሁን ምን ያህል ሰዎች እንደታሰሩ ግን ለማወቅ አልተቻለም፡፡

ከዚህ ቀደም መንግሥት የኢትዮጵያ ሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴው ጋር ሲደራደር ቆይቶ፤ በመጨረሻም በጅምላ በማሰር የሽብር ክስ መስርቶባቸው የኮሚቴው አባላት ያለምንም ፍትህ እስካሁን በእስር ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡

ከምርጫው ውጭ እንዲሆን የተደረገው አንድነት ፓርቲ በምርጫ ቦርድ ላይ ያቀረበው ክስ ለየካቲት 27 ተቀጠረ!

 udj

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በብሔራዊ ምርቻ ቦርድ አማካንነት ከግንቦቱ 2007 ዓ.ም.  ሀገር አቀፍ ምርጫ ውጭ እንዲሆን መደረጉን በመቃወም  በፌደራሉ ከፍኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ  በፍትሐ ብሔር 11ኛ ችሎት የመሰረተው ክስ ለየካቲት 27 ቀን 2007 ዓ.ም. ጠዋት ተቀጠረ፡፡

ይህንንም በተመለከተ ፓርቲው በማኀበራዊ ሚዲያ ገፁ ላይ “ህገ ወጥ በሆነ መንገድ በምርጫ ቦርድ እና በኢህአዴግ ሴራ ለእነ አቶ ትዕግስቱ አወሉ በኃይል ተላልፎ መሰጠቱ የሚታወቅ ነው። በዚህም ምክንያት ህጋዊው የአንድነት አመራር በምርጫ ቦርድ ላይ ክስ መስርተዋል፤ ፍርድ ቤቱ ልደታ በሚገኘው ከፍተኛ ፍርድ ቤት 11ኛ ፍትሀ ብሔር ችሎት ለየካቲት 27 ከጠዋቱ 3:30 ጉዳዩን ለማየት ቀጠሮ ሰጥተዋል፤ በመሆኑም በቅርብ የምንገኝ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች በችሎቱ ላይ በአካል በመገኘት ለህጋዊው አንድነት ያለንን አጋርነት እንድናሳይ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።” ብሏል፡፡

ብሔራዊ ምርጫ ቦር ከተመሰረተ ጀምሮ ከገዠው ህወሓት/ኢህአዴግ ጋር ጠንካራ ተፎካካሪ ናቸው ተብለው የሚገመቱትንና በከደፍተኛ ደረጃ የህዝብ ተቀባይነት ያላቸውን  የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለይም ከዚህ በፊት የኦሮሞ ብሔራዊ ኮንግረንስ(ኦብኮ)ን ያፈረሰ ሲሆን፤ በቅርቡ ደግሞ የግንቦቱ ምርጫ 2007 ዓ.ም. ዋዜማ ላይ  አንድነት ፓርቲን እና መኢአድን በማፍረስ ምርጫ ቦርድ ያፈረሳቸውን ፓርቲዎች ስም ለፈለጋቸው ሰዎች መስጠቱን ማሳወቁ ይታወሳል፡፡

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ለግንቦቱ ምርጫ 2007ዓ.ም. በዕጩነት እንዳይቀርቡ ተደረገ

  • “ምርጫ በህዝብ ፍላጎት ሳይሆን በሎተሪ ሆኗል” ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
ይልቃል ጌትነት (የወቅቱ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር)

ይልቃል ጌትነት (የወቅቱ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር)

አዲስ አበባ ከተማ ወረዳ 5 ለመጭው ምርጫ ለተወካዮች ምክር ቤት ሰማያዊ ፓርቲን ወክለው ሊቀርቡ የነበሩት የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት “ከቀረቡት 17 ዕጩዎች መካከል በተጣለ ዕጣ ወድቀዋል” በመባላቸው ለመጭው ምርጫ በዕጩነት እንዳይቀርቡ መደረጋቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል በዕጩነት በቀረቡበት ወረዳ 5 የምርጫ ጣቢያ ኢህአዴግ፣ የትግስቱ አንድነት፣ ቅንጅትን ጨምሮ ሌሎች ስድስት የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች ያለ ምንም ዕጣ አልፈዋል የተባለ ሲሆን “የሚያልፉት በዕጣ ነው” የተባሉት ሰማያዊን ጨምሮ 11 የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች መካከል ሰማያዊና ሌሎች አራት የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች “ዕጣ አልወጣላቸውም፡፡” ተብሏል፡፡

ስለ ጉዳዩ ያነጋገርናቸው የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት “ሰማያዊ ህዝብ ውስጥ በሰፊው እየገባና እያንቀሳቀሰ ያለ ግንባር ቀደም ፓርቲ ነው፡፡ እንደ ኢህአዴግ ያሉን ጨምሮ ዕጣ ውስጥ አይገቡም፡፡ ሰማያዊ ደግሞ ይህ ነው የሚባል እንቅስቃሴ ከማያደርጉት ፓርቲዎች ጋር ዕጣ ውስጥ ገብቶ ወደቀ መባሉ ዴሞክራሲ ከጅምሩ ጀምሮ የህዝብ ድምጽ ሆኖ እያለ በእኛ አገር ሎተሪ ሆኗል ማለት ነው፡፡” ብለዋል

ሊቀመንበሩ አክለውም ‹‹ሂደቱ ምንም ይሁን ምን አንድን ፓርቲ ወይንም ተወካይን ህዝብ ነው መምረጥ ያለበት፡፡ ህዝብ የሚፈልገውና የሚመረጥ ፓርቲ ነው ለምርጫ መቅረብ ያለበት፡፡ አሁን ግን እየተባለ ያለው በአንድ በኩል ህዝብ የማይፈልገው ያለ ዕጣ ሲገባ፣ በሌላ በኩል ህዝብ የሚፈልገው ሰማያዊን የመሰለ ፓርቲ ዕጣ ውስጥ ገብቶ አላለፈም እየተባለ ነው፡፡ በአንድ በኩል ህዝብ የተማረረባቸው ያለ ቅድመ ሁኔታ ህዝብን እንደሚያንቀሳቅስ የሚታወቀው ሰማያዊ ደግሞ ህዝብ ስፈለገው አሊያም በጥንካሬው ሳይሆን በሎተሪ ወድቀሃል ተብሏል›› ሂደቱ የተሳሳተ ነው ማለታቸውን ጨምሮ ነገረ-ኢትዮጵያ ዘግቧል፡፡