Category Archives: Social and Culture

ሰበር ዜና – ፓትርያርኩ ከሓላፊነታቸው ለመልቀቅ በቃል ጠየቁ፤ ጫና ለማሳደር የታሰበ ስልት መኾኑ ተጠቆመ

• ከሥልጣን የመገለል ስጋት ባይኖራቸውም፣ ተገቢነታቸው ብርቱ ጥያቄ እየተነሣበት ነው፤
• “በአቅም ማነስ ያጡትን ተቀባይነት ለመመለስ፣ ከአማካሪዎቻቸው ጋራ የወጠኑት ነው፤”
• ለብፁዕ አቡነ ፋኑኤል ምክር የሰጡት ምላሽ፣ ብዙዎችን ቢያሳዝንም ሊያግዷቸውም ዛቱ፤
• የተወነጀሉት ብፁዕነታቸው፣ በምልአተ ጉባኤ እና በሕግም እንደሚጠይቋቸው ተጠቆመ፤
• በሀ/ስብከታቸው ተቀባይነት ያጡት ብፁዕ አባ ማርቆስ፣በቦታቸው ለመተካት እየሠሩ ነው፤
†††
Archbishop Abune Matias

ፎቶ፡ ብፁዕ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ

ታማኝነታቸውና መንፈሳዊ አባትነታቸው ተቀባይነት እያጣ መምጣቱ በብርቱ አሳስቧቸዋል የተባሉት፣ ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ፣ “መሥራት አልቻልኩም፤” ሲሉ ከሓላፊነታቸው ለመልቀቅ፣ ለመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት በቃል ጥያቄ ማቅረባቸው ተሰማ፡፡

ፓትርያርኩ ጥያቄውን ያቀረቡት፣ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ሕግ አውጭና ወሳኝ አካል ከኾነው ቅዱስ ሲኖዶስ እና ከሥራ አስፈጻሚው የጠቅላይ ቤተ ክህነት አስተዳደራዊ አካል ጋራ ያላቸው ግንኙነት ከፍተኛ ውጥረት ውስጥ እንደገባ እየታየ ባለበት ወቅታዊ ኹኔታ ውስጥ ነው፡፡

“መፍትሔ ሊሰጠኝ ይገባል፤” በማለት በሓላፊነታቸው ለመቀጠል እንደተቸገሩ በቃል ለከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት መናገራቸውንና በቅርቡም በጽሑፍ እንደሚያሳውቁ ነው፣ ምንጮች የጠቆሙት፡፡
በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ የፓትርያርኩ ሢመትና ርደት ጉዳይ የሚወስነው ቅዱስ ሲኖዶስ ኾኖ ሳለ፣ ጥያቄያቸውን ለባለሥልጣናት ማቅረባቸው፣ በቅዱስ ሲኖዶስና በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዘንድ በአስከፊ ኹኔታ እያጡ የመጡትን ተደማጭነትና ተቀባይነት በተጽዕኖ ለመመለስ፣ ከአማካሪዎቻቸው ጋራ የወጠኑት መኾኑን እንደሚያሳይ ተነግሯል፡፡

የቅዱስ ሲኖዶሱ፣ የመጀመሪያ ዓመታዊ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባ፣ ከነገ በስቲያ፣ ጥቅምት 12 ቀን እንደሚጀመር እያወቁ፣ ከሓላፊነት ለመልቀቅ ጠይቀዋል፤ መባሉ ይህንኑ ጫና የማሳደር ስልታዊነቱን እንደሚያረጋግጥ ነው የተገለጸው፡፡

ከማኅበረ ቅዱሳን ጋራ በተያያዘ የሚያቀርቡት የእግድ አጀንዳ፣ በቅዱስ ሲኖዶሱ አካላት(ቋሚ ሲኖዶስ እና ምልአተ ጉባኤ) ውድቅ መደረጉ፤ ቡድን ፈጥረው እየመከሩ ለጠቅላይ ጽ/ቤቱ የሚያስተላልፉት መመሪያ መሸራረፉ ሕመም እንደኾነባቸው ነው የተስተዋለው፡፡

የማኅበሩ የቴሌቭዥን ፕሮግራም ሥርጭት፣ ከቋሚ ሲኖዶሱ ውሳኔ ውጭ እንዲታገድ ያስተላለፉት መመሪያ ተፈጻሚነት ሲያጣ፣ ከአጠቃላይ ጉባኤው 36ኛ ዓመታዊ ስብሰባ ተሳትፎ እንዲታገድ ወደ ማዘዝ ቢሸጋገሩም፣ እንዳሰቡት ሳይሳካላቸው ቀርቶ፣ በተፃራሪው፣ የማኅበሩ የማዕከልና የአህጉረ ስብከት ሥራዎች በጉልሕ እንዲስተጋቡ ምክንያት ኾኗል፡፡

በአጠቃላይ ጉባኤው መክፈቻ ምሽት፣ የማኅበሩ ተወካዮች እንዳይሳተፉ በማድረጋቸው፣ “የእኛን ሥልጣን ማወቅ አለባቸው፤ ሥልጣናችንን መረዳት አለባቸው፤” በማለት ከእነብፁዕ አባ ሩፋኤል፣ ብፁዕ አባ ማርቆስ እና ብፁዕ አባ ቶማስ ጋራ ውሎውን የገመገሙ ቢኾንም፤ በቀጣዩ ቀን፣ ማኅበሩ ከአህጉረ ስብከት ጋራ በመቀናጀት ያከናወናቸው ተግባራት በድምቀት እየተነገሩ በመዋላቸው፣ በጋራ መግለጫውና ቃለ ጉባኤው ላይ፣ የቴሌቭዥን ሥርጭቱ ሕገ ወጥ እንደኾነና እንዲዘጋ የሚጠይቅ አንቀጽ በጣልቃ እንዲገባ አርቃቂዎቹን አዝዘዋል፡፡ ሐሳቡን የተቃወሙ የአርቃቂ ኮሚቴው ሦስት አባላት፣ “የማኅበር ተላላኪዎች” ተብለው በሰብሳቢው የተዘለፉ ሲኾን፣ ሥርዋጹም በግድ እንዲገባና በድፍረት እንዲነበብ ተደርጓል፡፡

በአጠቃላይ ጉባኤው ያልተነሣ ጉዳይ በቃለ ጉባኤው የውሳኔ ሐሳብ ተብሎ መስፈሩ አግባብነት እንደሌለው ወዲያውኑ ከጉባኤተኛው ተቃውሞ የተሰማበትና በምክትል ሰብሳቢው ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁም ክፉኛ ቢተችም፣ ርእሰ መንበር የኾኑት ፓትርያርኩ ግን ሕገ ወጥነቱን ነው የተከላከሉት፡፡ ስሕተቶችን በፍጥነት እያረሙ፣ የአጠቃላይ ጉባኤውን ሒደት በጥብቅ እየተቆጣጠሩ፣ ማኅበሩን የማስወገዝና ሥልጣናቸውን የማግነን ምክራቸውን ያፈረሱባቸውን ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁን፣ የመዝጊያ ንግግር እንዳደርግ ስለ ፈቀዱልኝ አመሰግናለሁ፤” በማለት በማጠቃለያ ቃለ ምዕዳናቸው በአሽሙር መናገራቸውም ተሰብሳቢዎችን ፈገግ አሰኝቷል፡፡

የቤቱን ፈገግታ ያከሰመው፣ የፓትርያርኩ ክብረ ነክ ንግግር ግን ወዲያው ነበር የተሰማው፡፡ “ተናግሮ አናጋሪ የትላንቱ ሰውዬ” ያሏቸውን ብፁዕ አቡነ ፋኑኤልን በመዝለፍ፣ ለአጠቃላይ ጉባኤውም ለመንበረ ፕትርክናውም ክብር በማይመጥን ንግግር፥ ደጋፊዎቻቸውን ሳይቀር አሳፍረዋል፡፡ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት በእጅጉ አዝነዋል፤ ቁጣቸውን በግልጽ ያሳዩም ነበሩ፡፡

ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል፣ ፓትርያርኩ በሚሰጧቸው ሕገ ወጥና ረብሕ የለሽ መመሪያዎች እንዲጠነቀቁ፣ የቤተ ክርስቲያን ልጆችን አቅርበው ማነጋገርን እንዲያስቀድሙ ነበር ምሳሌያዊ ምክር የሰጡት፤ ቅዱስ ሲኖዶሱንም ያሳሰቡት፡፡ እንደተለመደው ግን፣ በዚያው ዕለት ማምሻውን፣ በተጠቀሱት ክፉ አማካሪዎች፣ ምሳሌያዊ ምክሩ በአሉታ እየተተነተነ የፓትርያርኩ ቁጣ እንዲጋጋም መደረጉ ተጠቅሷል፡፡

“አቡነ ፋኑኤል፣ በፈንጅና ጭስ መስለው የተናገሩትን [አማካሪዎቻቸው]ይዘው፣ ቅዱስነትዎ የሚጽፉት ደብዳቤ ከዚህ ግቢ ውጭ የማይሠራና አቅም የሌለው እንደኾነ፤ ምንም ቢጽፉ የትኛውም አካል የማያስፈጽመው ነው፤ ነገር ግን መነጋገርያ እየኾነ ብዙ ሰው እያደናገረ ነው፤ ብለው ተርጉመውላቸዋል፤ ይህም ሕመም ፈጥሮባቸው አድሯል፤”

ነውረኛ ንግግራቸው፣ በአጠቃላይ ጉባኤው ተሳታፊዎች ላይ የፈጠረውን ስሜት ቢያዩም፣ ይብሱኑ፣ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤልን ከሀገረ ስብከታቸው እንደሚያግዱ ነው የዛቱት፡፡ በሀገረ ስብከታቸው ተቀባይነት ያጡትና የመባረር ዕጣ የሚጠብቃቸው ብፁዕ አባ ማርቆስ፣ “ሀገረ ስብከቱን ለማኅበረ ቅዱሳን አሳልፎ ሰጥቶታል፤” እያሉ ብፁዕ አቡነ ፋኑኤልን በማሳጣት በቦታቸው ለመተካት የፓትርያርኩን እልክ እየገፋፉ እንደሚገኙ ተነግሯል፡፡ “ምን ሲኖዶስ አለ፤ ሲኖዶስ እኛው ነን፤” በማለት ፓትርያርኩ፣ ሌሎችንም አባቶች እንዲያስተባብሩም እየወተወቱ ናቸው፡፡

ብፁዕ አቡነ ፋኑኤል በበኩላቸው፣ ለተሰነዘረባቸው ውንጀላ ፓትርያርኩን በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ደረጃና በሕግም እንደሚጠይቁ ነው፣ የተጠቆመው፡፡

ቅዱስ ፓትርያርኩ፣ ርእሰ አበው እንደመኾናቸው መጠን፣ ሕገ ቤተ ክርስቲያንን ጠብቀው ለቤተ ክርስቲያኒቱ አጠቃላይ አመራር የመስጠት ግዴታ አለባቸው፡፡ በሕገ ቤተ ክርስቲያኑ እንደተደነገገው፣ በቅዱስ ሲኖዶስ እያስወሰኑና ከጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጅ ጋራ እየተማከሩ መሥራት የሚጠበቅባቸው ቢኾንም፣ ከዚህ ውጭ እየመከሩ የሚከተሉት ቤተ ክርስቲያንን የሚያስነቅፍ አካሔድ፣ ታማኝነታቸውና መንፈሳዊ አባትነታቸው በካህናትና በምእመናን ዘንድ ተቀባይነት እንዲያጣ፤ በባለሥልጣናትም ዘንድ አቅመ ቢስ ተደርገው እንዲናቁ አድርጓቸዋል፡፡ የመንግሥት ሹማምንትን ባገኙ ቁጥር፣ “ማኅበሩን ዝጉልኝ” የሚለው የዘወትር ውትወታቸው በእጅጉ እንዳስናቃቸውና ተደማጭነት እንዳሳጣቸውም ተጠቁሟል፡፡

በቃል አሳውቀውታል፤ የተባለውና በቀጣይም በጽሑፍ እንደሚያቀርቡ የተጠቆመው ከሓላፊነት የመልቀቅ ጥያቄ መነሻዎች ባለሥልጣናቱን እያነጋገረ ነው፣ ተብሏል፡፡ ከሥልጣን ለመልቀቅ ፍላጎት እንዳላቸው ከማሳየት ይልቅ፣ ከመንግሥት ያጡትን ትኩረት ለመመለስ፤ በዚህም፣ በቀጣዩ ሰኞ በሚጀመረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ላይ ጫና ፈጥረው ፍላጎታቸውን ለማስፈጸም፣ ከእኩይ መካሪዎቻቸው ጋራ የወጠኑት ስልት ሊኾን እንደሚችል ተጠቁሟል፤ “ትቼላችሁ እሔዳለኹ፤” እያሉ ማንገራገራቸው ዐዲስ እንዳልኾነ በማስታወስ፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ኾኖ የተሾመ አባት ከመዓርጉ የሚወርደው፡- ሃይማኖትን የሚያፋልስ፣ ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የማይጠብቅ፣ ቤተ ክርስቲያንን የሚያስነቅፍ ተግባር ፈጽሞ ከተገኘ፤ በተሾመበት ቀን የፈጸመውን ቃለ መሐላ ካልጠበቀ፤ ታማኝነቱና መንፈሳዊ አባትነቱ ተቀባይነት ያጣ ከኾነና ይህም በተጨባጭ ተረጋግጦ በቅዱስ ሲኖዶስ ሲወሰን እንደኾነ በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 33/1(ሀ)፣ (ለ) እና (ሐ) ተደንግጓል፡፡

ምንጭ፡ ሐራ ተዋሕዶ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የተፈረደበትን ፅኑ እስራት ጊዜውን አጠናቆ ወጣ

የቀድሞው ፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ተፈርዶበት የነበረውን የ3 ዓመት ፅኑ እስራት አጠናቆ በጣ። ጋዜጠኛው የእስር ጊዜውን ካጠናቀቀ ሁለት ቀናት ቢያልፉትም፤ ዛሬ ጥቅምት 5 ቀን 2010 ዓ.ም. መለቀቁ ታውቋል።

journalist-temesgen-desalegn

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ    ፎቶ_ ከማኅበራዊ ገፅ
ጋዜጠኛው ከመታሰሩ በፊት በባለቤትነት እና በዋና አዘጋጅነት ከሚያስተዳድረው ፍትህ ጋዜጣ በተጨማሪ፥ በልዕልና ጋዜጣ፥ በአዲስ ታየምስ እና በፋክት መፅሔቶች ላይም በቋሚነት ይፅፍ እንደነበር ይታወቃል።

ጋዜጠኛ ተመስገን ለእስር የተዳረገውም ቀደም ሲል በፍትህ ጋዜጣ በፃፋቸው ፅሑፎች እንደነበር ቀርቦበት የነበረው የክስ ሰነድ ያስረዳል።

በኢትዮጵያ ምንም እንኳ ጋዜጠኛ ተመስገን የተፈረደበትን የእስር ጊዜ አጠናቆ ቢወጣም ፤ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ እና ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬን ጨምሮ ሌሎች ጋዜጠኞች እና ብሎገሮች አሁንም ድረስ በእስር ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል።

በኢትዮጵያ የፀረ አገዛዝ ህዝባዊ ተቃውሞዎች ዳግም ተቀሰቀሱ

በኢትዮጵያ 2010 አዲስ ዓመት ህዝባዊ ተቃውሞዎች ዳግም ተቀሰቀሰ። በተለይ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ከተሞች በገዥው መንግሥት ላይ ዳግም ህዝባዊ ተቃውሞች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ተከትሎ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች በወሰዱት ወታደራዊ የኃይል ርምጃ 8 ያህል ሰዎች መገደላቸውን መረጃዎች አመልክተዋል።

ባለፈው ህዳር 2008 ዓ. ም. ጀምሮ ክዓመት በላይ የዘለቀው የኦሮሚያ፥ አማራ እና ደቡብ ክልል በተለይም ኮንሶ አካባቢ የተከሰተውን ህዝባዊ የፀረ አገዛዝ ተቃውሞ ተከትሎ ሀገሪቱ ለ10 ወራት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ስር እንደነበረች ይታወሳል። ይሁን እንጂ በአስችኳይ አዋጁ ጊዜ ህዝባዊ አመፁ የተረጋጋ ቢመስልም በያዝነው ጥቅምት 2010 ዓ .ም. ዳግም ማገርሸቱ ታውቋል።

የህዝቡ ተቃውሞ ዋነኛ ምክንያት ተደርጎ የተጠቀሰውም ባለፈው መስከረም 2010 ዓ ም በኦሮሚያ እና በኦጋዴን የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ድንበር አካባቢ በተቀሰቀሰ ግጭት በርካታ ሰላማዊ ዜጎች መገደላችውን እና በኦጋዴን የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል አስተዳደርና በክልሉ ልዩ ኃይል ፖሊስ አማካኝነት ከ70,000 በላይ ዜጎች ከሚኖሩበት ቀዬ መፈናቀላቸውን በመቃወም እንዲሁም የታአሰሩ የህሊና እና የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ የሚል ጥያቄም እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

በተለይ ባለፈው መስከረም 2010 ዓ ም በሁለቱ ክልሎች ድንበር አካባቢ በተቀሰቀሰ ግጭት ከሁለትም ክልል በርካታ ንፁሃን ዜጎች መገደላቸው ይታወሳል።

ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ድረስም በተለይ በኦሮሚያ ክልል ባሉ አንዳንድ ከተሞች ህዝባዊ ተቃውሞች መቀጠላቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል።

የመገንጠል ሥነ ሥርዓት በኢትዮጵያ፤ ከሰላም ይልቅ ግጭት አስከታይነታቸው፤

Wuobishet Mulat
ውብሸት ሙላት
(ክፍል አንድ)

ሰሞኑን ዓለምአቀፍ የመገናኛ ብዙኃንን ከተቆጣጠሩ አጀንዳዎች ውስጥ አንዱ የመገንጠል ጉዳይ ነው፡፡ የኩርድስታን እና የካታላን ሕዝበ ውሳኔዎች፣ እንግሊዝኛ ተናጋሪ የሆኑት ካሜሩኖች የመገንጠል እንቅስቃሴ ተጠቃሽ ናቸው፡፡

በኢራቅ፣በስፔንም ይሁን በካሜሩን ሕገ መንግሥቶች ላይ ከአገር መገንጠያ አንቀጽ የላቸውም፡፡ ለነገሩ በቀድሞዎቹ የሶቪየት ኅብረት (ሩሲያ) እና ዩጎዝላቪያ፣አሁን ደግሞ ሴንት ኪትስና ኔቪስ ከምትባል የካሪቢያን ደሴት እና ከአውሮፓ ኅብረት ቻርተር ውጭ የመገንጠያ አንቀጽ ያለው ሕገ መንግሥት የለም፤ከኢትዮጵያ በስተቀር፡፡ የኢትዮጵያው ወደ ሩሲያና ዩጎዝላቪያ የሚቀርብ ነው፡፡ ይሁን እንጂ፣ እነዚህ አገራት ጥቅም እንደሌለው ተረድተው ሲተውት፣ ኢትዮጵያ እንደ አዲስ ተቀብላዋለች፡፡ ሩሲያና ዩጎዝላቪያም ቢሆኑ ግን ሕገ መንግሥታቸው ላይ በተቀመጠው ሁኔታ አለመገንጠላቸውን ልብ ይሏል፡፡

ይህ ጽሑፍ የሚዳስሰው ሕገ መንግሥቱ ሲረቀቅም ሆነ ሲጸድቅ እንዲሁም ኋላ ላይ ፖለቲከኞችም ይሁኑ ምሁራን ብዙም ትኩረት ካልሰጠባቸው ጉዳዮች አንዱ የሆነውን የመገንጠል ሥነሥርዓትን ወይንም ሒደትን ነው፡፡

ሕገ መንግሥቱ ሲረቀቅም ይሁን ሲጸድቅ እጅግ ካጨቃጨቁት ጉዳዮች ዋነኛው አንቀጽ 39 ንዑስ ቁጥር 1 ላይ የተገለጸው የብሔሮች፣ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ያለምንም ገደብ መገንጠልን በሕገ መንግሥቱ የመካተቱ ነገር ነው፡፡በዚህ አንቀጽ ውስጥ የተዘረዘሩት ሌሎች አራት ንዑሳን አንቀጾች ግን ከጅምሩም ትኩረት አልሳቡም፣ወይንም አልተሰጣቸውም፡፡

የመገንጠል መብት ሕገ መንግሥታዊ ዋስትና እንዲኖረው በትጋት የተከራከሩት እና የሚከራከሩት ሰዎች ከሚያነሷቸው ምክንያቶች መካከል ቀዳሚው እና ዋነኛው ብሔሮች፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች በኢትዮጵያዊነት ጥላ ሥር አብረው መኖር ካልቻሉ ያለ ጦርነት ወይንም በሰላም ለሚለያዩበት ሁኔታ ዋስትና ይሰጣል የሚል ነው፡፡

በመሆኑም፣ መገንጠልን የመረጡ ቡድኖች ደረጃ በደረጃ ሊከተሏቸው የሚገቡ አምስት ሥነሥርዓቶች በዚሁ አንቀጽ ንዑስ ቁጥር አራት ላይ ተቀምጠዋል፡፡ ‘የሰይጣን ጆሮ አይስማና’፣ አንድ ብሔር መገንጠል ቢፈልግ እና እነዚህን ሥነሥርዓቶች በመከተል ምንም ዓይነት ጦርነት ወይንም እልቂት ሳይኖር በሰላም የመገንጠልን መብት ሥራ ላይ ለማዋል ማስቻላቸው ግን ፍተሻ ያስፈልጋቸዋል፡፡

ይህ ጽሑፍ እነዚህን ሥነሥርዓቶች ያሉባቸውን እንከኖች በማሳየት የመገንጠል መብትን ሥራ ላይ ማዋል የሚፈልግ ብሔር ቢኖር በሰላም ለመለያየት የማያስችሉ መሆናቸውን ማሳየት ነው፡፡
መገንጠል በዘፈቀደ የሚፈጸም ድርጊት እንዳይሆን በማሰብ ሥነሥርዓቶቹ ቀድመው ተቀምጠዋል፡፡ የመገንጠልን ጉዞ ለሚመርጥ ተጓዥ፣ መንገዱ እንዲህ ነው፡፡

መገንጠልን የሚፈልገው ብሔር ወይንም ብሔረሰብ ወይንም ሕዝብ ምክር ቤት በ2/3ኛ መገንጠሉን ሲደግፍ፣ የፌደራሉ መንግሥት በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሕዝበ-ውሳኔ ሲያዘጋጅ፣ መገንጠሉን አብዝኃኛው ሕዝብ ሲደግፈው፣ የፌደራሉ መንግሥት ሥልጣን ሲያስረክብ፣ እና የንብረት ክፍፍል ሲካሔድ ነው፡፡
እነዚህ የመገንጠያ መንገዶች ናቸውና ተራ በተራ እንያቸው፡፡

የምክር ቤት ውሳኔ፤
=============
በመጀመሪያ፣ መገንጠል የሚፈልገው ብሔር የራሱ ምክር ቤት ሊኖረው ግድ ነው፡፡ ምክር ቤቱም በ2/3ኛ ድምፅ የመገንጠሉን ሐሳብ ካልደገፈ በስተቀር ቀጣዮቹ ሥርዓቶች ምንም ፋይዳ የላቸውም፡፡ በመሆኑም ጥያቄው በዚሁ ተኮላሸ ማለት ነው፡፡

በሴንት ኪትስ እና ኔቪስም (ከኢትዮጵያ 12 ዓመታት በመቅደም የመገንጠል መብትን በሕገ መንግሥቷ ያካተተች ባለ ሁለት ክልሎች አገር ናት፡፡) መጀመሪያ የኔቪስ ደሴት ሕግ አውጭ ምክር ቤት በ2/3ኛ የድጋፍ ድምፅ መስጠት አለበት፡፡ከዚያ በኋላ ይሄው ምክር ቤት በሕዝበ-ውሳኔ ወቅት ለኔቪስ ደሴት መራጮች የሚያቀርበውን አማራጮች ሕዝቡ ድምፅ ከመሰጠቱ ቢያንስ ከዘጠና ቀናት በፊት ማሳወቅ ይጠበቅበታል፡፡

አማራጮቹም፣ ከሴንት ኪትስ ተለይቶ ነጻ አገር መመሥረት፣ ከሌላ አገር ጋር መቀላቀል ወይንም አለመለየት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ በካናዳም፣ ለሕዝበ ውሳኔ የሚቀርበው ጥያቄ ግልጽ መሆን እንዳለበትና ቀድሞ በአገሪቱ ፓርላማ መጽድቅ አለበት፡፡

በኢትዮጵያ፣ የብሔሩ ምክር ቤት ለመገንጠሉ አጀንዳ የ2/3ኛ የድጋፍ ድምፅ ከሰጠ ይሄንኑ ውሳኔ በጽሑፍ ለፌደሬሽን ምክር ቤት ያቀርባል፡፡ የፌደሬሽን ምክር ቤትም ጥያቄው ከደረሰው ጀምሮ በሚታሰብ በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሕዝበ-ውሳኔ ማዘጋጀት አለበት፡፡

በኔቪስ ደሴት ግን ሕዝበ-ውሳኔውን የሚያከናውነው የፌደራል መንግሥቱ ሳይሆን ራሷ ደሴቷ ናት፡፡ የምርጫ ኮሚሽኑም የሚዋቀረው የደሴቷ ገዥ የሚሾመው ሰብሳቢ፣ተቃዋሚ ፓርቲዎችን እና የአገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትርን አማክሮ ሁለት በድምሩ ሦስት አባላት ባሉት የምርጫ ኮሚሽን አማካይነት ይከናወናል፡፡ በኩርድስታንና በካታሎኒያም ቢሆን ኢራቅ ወይንም ስፔን አይደሉም ምርጫውን የሚያስፈጽሙት፡፡
በመሆኑም፣በኢትዮጵያ፣ከፌደሬሽኑ ለሚገነጠል ብሔር የፌደራሉ መንግሥት (የቀሪው አካል) የምርጫ ቦርድ አስፈጽሞት በምን መልኩ ሰላምን ሊያመጣ ይችላል? ቅሬታዎችም ወደ እዚሁ ቦርድ እና ወደ ፌደራል ፍርድ ቤቶች የሚመጡ ከመሆናቸው አንጻር እንደምን ተኣማኒነትና ተቀባይነት ይኖራቸዋል? የፌደራሉ መንግሥት ሊይዝ የሚችለው አቋም እንዳይገነጠሉ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ ምናልባት እንደ ኤርትራ “ተገንጠሉልን፣ሂዱልን” ካልተባለ በስተቀር!

“የማሰላሰያ ጊዜ”፤
===========
ብሔሮች፣ ከኢትዮጵያ ከመፋታታቸው በፊት የማሰላሰያ ጊዜ ባይቀመጥም የፌደራሉ መንግሥት በሦስት ዓመት ጊዜ ውስጥ ሕዝበ-ውሳኔ እንዲያዘጋጅ መደንገጉ ወይንም በጣም አጭር ጊዜ አለመሆኑ መገንጠል የሚፈልገው ብሔርም እንዲያስብበት፣ ቅስቀሳና የማሳመን ሥራ የማከናወኛ ጊዜ በመሆን ሊያገለግል ይችላል፡፡

በተቃራኒው ደግሞ አንድነትን ለሚሰብኩትና የሚደግፉት የማግባባትና የመቀስቀስ ተግባራቸውን በዚህ ወቅት ለማከናወን ዕድል ያገኛሉ፡፡ በመሆኑም፣ይህ እንደ ማሰላሰያ ጊዜ ሊወሰድ ይችላል፡፡
የመገንጠያ ሥነ-ሥርዓት በሕገ መንግሥቷ አብጅታ የነበረችው ሩሲያ ግን ከዚህ የተለየ የማሰላሰያ ጊዜ ነበራት፡፡ የሩሲያ ሪፐብሊኮች(ክልሎች) ለመገንጠል በትንሹ አምስት ዓመት ይፈጅባቸዋል፡፡ ምክንያቱም ሕዝበ-ውሳኔ ተደርጎ በ2/3ኛ ድምፅ ድጋፍ ካገኘ በኋላ በድጋሜ በአምስተኛ ዓመቱ መጨረሻ ላይ የማረጋገጫ ሕዝበ-ዉሳኔ በማከናወን ድምፅ መስጠት ከሚችለው ከሪፐብሊኩ ኗሪዎች ውስጥ 2/3ኛው መገንጠልን መደገፋቸው መረጋገጥ አለበት፡፡

በመሆኑም ሐሳባቸውን ሊቀይሩ ከቻሉም ዕድል ይሰጣል፡፡ ይህ አድራጎት ሽማግሌዎች ባልና የሚስት ለማስታረቅና ለማግባባት የሚጠቀሙበትን ስልት ያስታውሰናል፡፡ ባልና ሚስት ተጣልተው ጉዳያቸው በሽምግልና እንዲታይላቸው ለመረጧቸው ሽማግሌዎች ብሶታቸውንና በደላቸውን ማሰማት ሲጀምሩ ሽማግሌዎች የጠቡን ምንጭ ጊዜያዊነት ወይንም ጥንካሬ ለመረዳት ሁለቱንም ወገኖች “እስኪ ከማሸማገላችን በፊት ጉዳዩን ነት ይንካው” በማለት ይመልሷቸዋል፡፡

“ነት” ማለት፣ ብዙ በገጠር አካባቢ የሚኖር ሰው እንደአንሶላ የሚጠቀሙበት የለሰለሰ (የታረበ) የበሬና የላም ቆዳ ነው፡፡ “ነት ይንካው” ሲባል ባልና ሚስት ጥልና ብሶታቸውን ከማሰማታቸውና ውሳኔ ከማሳለፋቸው በፊት አብረው በአንድ ነት ላይ ተኝተው አድረው በድጋሜ እንዲያጤኑት ለማድረግ ነው፡፡ በንዴት የተፈጠረ፣ በድንገት የተከሰተ ከሆነ ነቱ ላይ ይቀራል፡፡ የመረረና የከረረ ከሆነ አንድ ነት ላይ መተኛት ስለማይችሉም የችግሩን መጠን ለመረዳት ይረዳል፡፡

የሩሲያዎች ሕገ-መንግሥት “ነት ይንካው” የሚለውን አካሔድ የተከተለ ነበር ማለት ይቻላል፡፡ አምርረው በ2/3ኛ ድምፅ ከወሰኑም በኋላ አምስት ዓመት ነት ማሥነኪያ ወይንም ማሰላሰያ ጊዜ ሰጥተዋል፡፡ ከዚህ አንጻር የእኛን ሕገ-መንግሥት ስናየው አፍን ሞልቶ ለማሰላሰል፣” ሽልም ከሆነ መግፋቱን ቂጣም ከሆነ መጥፋቱን” ለማወቅ የሚያስችል ጊዜ እንዳልተሰጠው መረዳት ይቻላል፡፡
የፌደራሉ መንግሥት በሦስት ዓመት ጊዜ ሕዝበ-ውሳኔ እንዲያስፈጽም፣ እንዳያጓትት የጊዜ ጣሪያ ከማስቀመጥ በዘለለ በወሩም ይሁን በዓመቱ ማዘጋጀትን አይከለክልም፡፡
(ይቀጥላል)

Ethiopia’s ethnic federalism is being tested

Violence between ethnic groups has put the country on edge

FOR centuries the city of Harar, on the eastern fringes of the Ethiopian highlands, was a sanctuary, its people protected by a great wall that surrounded the entire city. But in the late 19th century it was finally annexed by the Ethiopian empire. Harar regained a bit of independence in 1995, when the area around it became the smallest of Ethiopia’s nine ethnically based, semi-autonomous regions. Today it is relatively peaceful and prosperous—and, since last month, a sanctuary once more.

In recent weeks thousands of Ethiopians have poured into areas around Harar, fleeing violence in neighbouring towns (see map). Nearly 70,000 people have sought shelter just east of the city. Several thousand more are huddling in a makeshift camp in the west. Most are Oromo, Ethiopia’s largest ethnic group. Its members clashed with ethnic Somalis in February and March, resulting in the death of hundreds. The violence erupted again in September, when more than 30 people were killed in the town of Awaday. Revenge killings, often by local militias or police, have followed, pushing the death toll still higher. In response, the government has sent in the army.

Ethio-conflict map.png

Ethnic violence is common in Ethiopia, especially between Oromos and Somalis, whose vast regions share the country’s longest internal border. Since the introduction of ethnic federalism in 1995, both groups have tried to grab land and resources from each other, often with the backing of local politicians. A referendum in 2004 that was meant to define the border failed to settle the matter. A peace agreement signed by the two regional presidents in April was no more successful.

When the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) swept to power in 1991 after a bloody 15-year civil war, federalism was seen as a way to placate the ethnic liberation movements that helped it to power. The previous regime had been dominated by the Amhara, the second-largest ethnic group (the Eritreans broke away to form a new state). Eventually ethnic loyalties would wither as people grew richer, went the thinking of the Marxist-inspired EPRDF.

But the way federalism was implemented caused problems from the start.New identity cards forced people to choose an ethnicity, though many Ethiopians are of mixed heritage. Territories often made little sense. In the Harari region, a minority of Hararis rule over much bigger populations of Oromos and Amharas, a source of resentment. Boundaries that were once porous became fixed, leading to disputes.

For years the EPRDF sought to dampen the tension by tightly controlling regional politics. But its grip has loosened over time. Local governments have grown stronger. Regional politicians are increasingly pushing ethnic agendas. The leaders of Oromia, the largest region, have drafted a bill demanding changes to the name, administration and official language of Addis Ababa, the capital, which has a special status but sits within Oromia. They have stoked ethnic nationalism and accused other groups of conspiring to oppress the Oromo.

Politicians in the Somali region are no more constructive. They have turned a blind eye to abuses by local militias and a controversial paramilitary group known as the Liyu. The region’s president “has a fairly consistent expansionist agenda”, says a Western diplomat. “He may have spied an opportunity.” The federal government, now dominated by the Tigrayan ethnic group, was rocked by a wave of protests last year by the Oromo and other frustrated groups.

Many complain that the rulers in Addis Ababa are doing too little. They have been slow to respond to the recent violence, fuelling suspicions that they were complicit. “We are victims of the federal government,” shouts Mustafa Muhammad Yusuf, an Oromo elder sheltering in Harar. “Why doesn’t it solve this problem?”

Federalism may have seemed the only option when it was introduced in 1995. But some now suggest softening its ethnic aspect. “In the past the emphasis was too much on ethnic diversity at the expense of unity,” says Christophe Van der Beken, a professor at the Ethiopian Civil Service University. “The challenge now is to bring the latter back.”

Source: The Economist.