አንድነት ፓርቲ እሁድ “የነፃነት ቀን ቀርባለችና ወደ አደባባይ ውጡ” በሚል ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል
-የሰልፉን ቅስቀሳ ተከትሎ የፓርቲው ወጣት አመራሮች ታስረዋል
.አንድነት ፓርቲ የጠራው የነገው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ተጠናክሮ ቀጥሏል
አንድነት ፓርቲ ለነገ እሁድ ጥር 17 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢህአዴግና በምርጫ ቦርድ በኩል ፓርቲው ወደ ምርጫ ውድድር እንዳይገባ የሚደረገውን እንቅስቃሴና ድርጊት በመቃወም የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ በፓርቲው አባላትና ደጋፊዎች ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፉን ተከትሎ ዛሬ ጥር 16 ቀን 2007 ዓ.ም. የፓርቲው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት አብርሃም፣ ምክትል ኃላፊው አቶ ንዋይ ገበየሁ፣ የኤዲቶሪያል ቦርድ ኃላፊው አቶ ሰለሞን ስዩም እና የፓርቲው የአዲስ አበባ ወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ አቶ ስንታየሁ ቸኮል እና ሌሎች አመራሮች አቶ ያሬድ አለማየሁ፣ አቶ ሲሳይ ጌትነት፣ አቶ ማቲያስ ሐረጉ በፀጥታ ይሎች መታሰራቸውና ወዳልታወቀ ስፍራ የተወሰዱ ሲሆን፤ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት አቶ አስራት አብርሃም፣ አቶ ንዋይ ገበየሁ፣ አቶ ሰለሞን ስዩም እና አቶ ስንታየሁ ቸኮል መፈታታቸውን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡
ፓርቲው ሰልፉን እንዲጠራ ያስገደደው ምርጫ ቦርድ ከሀገሪቱ የምርጫ አዋጅ ህግ አግባብ ውጭ በአንድ ወር ውስጥ ለ3ኛ ጊዜ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲጠራ በመወሰኑ ሲሆን፤ ቅሬታ ነበረን በሚል ጥያቄ ካቀረቡት ዋነኞቹ አቶ አየለ ስሜነህ እና አቶ ኢሳይያስ ቱሉ ምርጫ ቦርድ እና ባልፈለግነው መንገድ ፓርቲውን ለሁለት ለመክፈል በመሞከሩ፣እኛ ደግሞ አንድነት አንድ ነው እንዲከፈልም ስለማንፈልግ ተመልሰን ወደ ዋናው ፓርቲያችን ቢሮ ተመልሰናል ብለዋል፡፡ ይሁን እንጂ ምርጫ ቦርድ ከዚህ ቀደም አንድነት ጥር 4 ቀን 2007 ዓ.ም. በጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ እንዲታዘብ ጥሪ ሲደረግለት እነ አቶ አየለ ስሜነህ ሌላ ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ደብዳቤ ስላስገቡ ቦርዱ ሁለት ቦታ ለመታዘብ ወኪል መላክ እንደማይችል በጥር 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ለፓርቲው ደብዳቤ መፃፉ ታውቋል፡፡
አቶ አየለ ስሜነህ በበኩላቸው እኛ ጠቅላላ ጉባኤ አልጠራንም፣ የነበርነው የአንድነት ፓርቲ አባላት ከ15 አንበልጥም፤ ነገር ግን የፓርቲው አባላት ያልሆኑ ከ60 በላይ ሰዎች በስብሰባችን ላይ ተገኝተዋል፣የሆቴል አዳራሽ ኪራይ ማን እንደከፈለ አናውቅም፣ ተከፍሎላችኋል እዛ ሆቴል ሂዱ እንባላለን፣ይሄ ሁሉ ስላላማረን እና ፓርቲያችን አንድነት አንድ ስለሆነ ወደ ፓርቲያችን ተመልሰናል ሲሉ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡
ምርጫ ቦርድ ጥር 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ለፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔ እንዲታዘብ ለቀረበለት ጥሪ እነ አቶ አየለ ስሜነህም ጠርተውናል ሲል በፃፈው ደብዳቤ ማስታወቁ አይዘነጋም፡፡ አቶ አየለ ስሜነህ በበኩላቸው እኛ ምንም ዓይነት ጠቅላላ ጉባኤ አልጠራንም፣በመካከላችን የነበረው ጥቂት አለመግባባት እንዲፈታ ስንል እንጂ ከፓርቲው ህልውናም ሆነ አሰራር ጋር ቅሬታም ሆነ ጠቅላላ ጉባኤ ይጠራ የሚል ጥያቄ አላቀረብንም ሲሉ አስታውቀዋል፡፡
በአሁን ወቅት ጥያቄ ነበረን ያሉት አቶ አየለ፣ ያለንን ጥያቄ በፓርቲያችን ውስጥ ሆነን እንፈተዋለን፣ ወደ ውጪ ይዘን መውጣታችን ትክክል እንዳልነበረና እኛ ባላሰብናውና ባልፈለግነው መንገድ ፓርቲው ላይ በእኛ ስም አደጋ ለመፍጠር እየተሰራ እንዳለ ስንገዘነብ ተመልሰናል፣ መጀመሪያም ቢሆን ፓርቲው አልተከፈለም፣ እኛም ጥያቄ አቀረብን እንጂ ከፓርቲው አልወጣንም ሲሉ አክለዋል፡፡ አቶ አየለ ስሜነህ ለጋዜጠኞች የሰጡትን መግለጫ ለራሱ ለምርጫ ቦርድ ግልባጭ ማድረጋቸውንም አስታውቀዋል፡፡ ይሁን እንጂ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ አቅርበው የነበሩት አቶ አየለ ስሜነህ ወደ ፓርቲው መመለሳቸውን ቢያሳውቁም፤ ምርጫ ቦርድ ግን በነ አቶ አየለ ስሜነህ ስም ሌላ አካል እያደራጀ መሆኑን በመጥቀስ ፓርቲው ድርጊቱን ለማውገዝ የሰልፍ መጥራቱን ይፋ አድርጓል፡፡ ፓርቲው ድርጊቱን የኢትዮጵያ ህዝብም እንዲረዳውና እንዲያወግዘው ለነገ እሁድ ጥር 17 ቀን 2007 ኣ.ም. የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፉን መጥራቱን ፓርቲው አስታውቋል፡፡ ከዚህ በኋላ ፓርቲው ህዝባዊ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ በመላ ሀገሪቱ ማካሄድና ነውጥ አልባ የነፃነት ትግሉን አጠናክሮ ከመቀጠል ውጭ ለ3ኛ ጊዜ ጠቅላላ ጉባኤ እንደማይጠራ ማሳወቁ አይዘነጋም፡፡ ወደ ፓርቲያቸው ስለተመለሱት አቶ አየለ ስሜነህ እስካሁን ባይዘግብም ፓርቲው እንደተከፈለ አድርገው ከሬዲዮ ፋና እና ከኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በተደጋጋሚ ከሚያቀርቡት በስተቀር ምርጫ ቦርድ እስካሁን የሰጠው ምላሽ የለም፡፡
የነገው የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ መነሻ አዲስ አበባ ቀበና መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን ፊትለፊት ከሚገኘው የፓርቲው ዋና ፅህፈት ቤት ሲሆን፤ የሰላማዊ ሰልፉ መነሻ ሰዓት ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት መሆኑንም ታውቋል፡፡
የሰልፉ መዳረሻ ቦታ አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ጀርባ እና ዋናው ፖስታ ቤት ፊትለፊት በሚገኘው ኢትዮ-ኩባ አደባባይ መሆኑን ፓርቲው አስታውቋል፡፡
በተመሳሳይ ቀንና ሰዓት (እሁድ ጥር 17 ቀን 2007 ዓ.ም.) የተቃውሞ ሰልፉ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በደብረ ማርቆስ፣ በአርባምንጭ አካባቢ ከምባ ወረዳ፣በጂንካ እና በሸዋ ሮቢት እንደሚደረግ በፓርቲው ብሔራዊ ምክር ቤት በመወሰኑ በክልሎችም የሰላማዊ ሰልፍ ቅስቀሳ ቀጥሏል፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ ቀኑ እንዲራዘም የመንግስት አካላትና ዲፕሎማቶች ጥረት ቢያደርጉም፤የአንድነት ፓርቲ ምክር ቤት ዛሬ ባደረገው አስቸኳይ ስብሰባ መብታችንን ከእንግዲህ ለምነን አናገኝም፣ የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፉም በታቀደለት መሰረት ይቀጥል ሲል መወሰኑን ፓርቲው አስታውቋል፡፡
ፓርቲው ከላይ ከተጠቀሱት 5 ከተሞች በተጨማሪ በተከታታይ በሌሎች የሀገሪቱ ከተሞችም የተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፉ እንደሚቀጥል ይፋ አድርጓል፡፡
በአዲስ አበባ ኮልፌ የሚገኙ የአባት ጡረተኛ አርበኞች መኖሪያቸው እንዲፈርስ ተደረገ
በአዲስ አበባ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 09 እና 10 ውስጥ ከኃይለስላሴ ዘመን ጀምሮ በቀድሞ መንግስት በተሰጣቸው ካምፕ ውስጥ ሲኖሩ የነበሩ ከ500 በላይ የአባት ጡረተኛ አርበኞች ቤታቸው በመንግስት እንዲፈርስ በመደረጉ ከነቤተሰቦቻቸው ሜዳ ላይ መበተናቸውን ገለፁ፡፡
በተለምዶ ኮልፌ ልኳንዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የሚገኘውንና ከጥንት ጀምሮ የአባት ጡረተኞችና የአርበኞች መኖሪያ የሆነውን የወታደር ካምፕ ቦታው ተከልሎላቸው የሰሩት ራሳቸው አርበኞቹ መሆናቸውን ነዋሪዎቹ የገለፁ ሲሆን፤ ፈጽሞ ባላሰቡበትና ባልተዘጋጁበት ሁኔታ መኖሪያ ካምፓቸው ያለ ምንም ተለዋጪ ማረፊያ መሳሪያ በታጠቁ ወታደሮች እንዲፈርስ መደረጉ እንዳስደነገጣቸው መናገራቸውን የኢሳት ዘገባ አመልክቷል፡፡ ነዋሪዎቹ ውሳኔውን በመቃወም እስከ ፍትህ ሚኒስቴር ድረስ አቤቱታ ቢያቀርቡም ሰሚ እንዳላገኙ ተጠቁሟል።
ካምፕ የሚገነው ቤታቸው ፈርሶ ሜዳ ላይ ከተበተኑትና የላስቲክ ድንኳን ሰርተው ከተጠለሉት ነዋሪዎች መካከል የኤች አይ ቪ/ ኤድስ ህመምተኞችና በርካታ ህጻናት እንደሚገኙበት ኢሳት በዘገባው አስታውሷል። የአካባቢው መስተዳድር አካላት ነዋሪውን ሊያነጋግሩ ሲመጡ የአርበኞቹ ልጆች ባንዲራ እያውለበለቡ አባቶቻቸው በሞቱላትና ወደነሱ ባስተላለፉዋት ሀገራቸው የመኖር መብት ሊነፈጉ እንደማይገባና ያለ አማራጭ መኖሪያ ሜዳ ላይ መውደቅ እንደሌለባቸው አቤቱታ ቢያቀርቡም፤ የመስተዳድሩ አካላት ወጣቶቹ ባንዲራ በመያዛቸው ቁጣቸውን በመግለፅ ያለምንም መፍትሔ መመለሳቸውን ነዋሪዎቹ በሀዘን መናገራቸው ተጠቁሟል። አሁንም ነዋሪው የመንግስት ያለህ፣ያገር ያለህ እያለ ተማፅኖውን እያሰማ እንደሚገኝ የጥር 7 ቀን 2007 ዓ.ም.የኢሳት ዘገባ አመልክቷል።
የተቀዋሚ ፓርቲዎች ምርጫ ቦርድ ያቀረበውን የፋይናንስ ክፍፍል ቀመር ውድቅ አደረጉ
የገዥው ፓርቲ ቀኝ ዕጅ ተደርጐ የሚወሰደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ለፓርቲዎች የሚሰጠውን የፋይናንስ ድጋፍ ክፍፍልን አስመልክቶ በምርጫ ከሚወዳደሩ ሀገር-አቀፍ ፓርቲዎች ጋር የጠራው የውይይት ሀሳብ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ውድቅ ተደረገ፡፡ ቦርዱም ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል፡፡
በግዮን ሆቴል ጉባዔ አጠቃላይ ከ25 በላይ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ቦርዱ ፍትሐዊ ያለውን የፋይናንስ ክፍፍል ቀመር አቅርቧል፡፡ በዚህም መሠረት ለእኩልነት መስፈርት 10% ፣ የፓርላማና የክልል ም/ቤት መቀመጫን መሰረት ያደረገ የፍትሐዊነት መስፈርት 55%፣ ባቀረቡት የእጩዎች ብዛት 25% እና የሴት እጩዎች ብዛት 10% በሚል ቀመር ቢያቀርብም ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ መልኩ እና በኢህአዴግ እንደ አጋር የሚታዩ ፓርቲዎች ሳይቀር በሙሉ ድምፅ “ኢህአዴግን ዳግም ለማንገስ የተሰራ ቀመርና የቦርዱን ገለልተኛነት ጥያቄ ያጋለጡ” በማለት ከፍተኛ ትችትና ተቃውሞ እንደቀረበበት አንድነት ፓርቲን ወክለው በቦታው የተገኙት አቶ ዳንኤል ተፈራ፣ ገልፀዋል፡፡
አንድነት በመወከል ስብሰባው ላይ የተሳተፉት የአንድነት ተወካይ አቶ ዳንኤል ተፈራ፣ እንደገለፁት “ስብሰባው ላይ ምርጫ ቦርድ ላይ የቀረበበት ውግዘትና ያቀረበው ቀመር ከኢህአዴግ ተወካይ በስተቀር የሚደግፈው ማጣቱ እንዲሁም ስርዓቱን ኢህአዴግ ይደግፍኛል ብሎ የሚተማመንባቸው ፓርቲዎች ከጉያው እየወጡ እንደሆነ የሚጠቁም አጋጣሚ ነው” ሲሉ ገልፀዋል፡፡ አያይዘውም ተሳታፊዎች ምርጫ ቦርድ ስብሰባዎችና ሀሳቦችን ከዜና ማድመቂያነት ባለፈ በተግባር ለውጦ እንዲያሳይ እና ሀገራዊ ግዴታውን እንዲወጣ በርካታ ማሳሰቢያዎች የቀረቡ ሲሆን ዳግመኛ በታሪክ ቅሌት እንዳይወድቅ ከአድሏዊ አሰራር ራሱን እንዲያላቅቅ ምክርም ተለግሶታል፡፡
በተለይም ፓርላማና የክልል ም/ቤት ባለ መቀመጫ በሚል የተመደበውን ገንዘብ በኢህአዴግ ለማስረከብ መዘጋጀቱ ተቀባይነት እንደሌለውና እንደገና ራሱን እንዲፈትሽ አብዛኛው ተሳታፊ ገልፆል፡፡
ቦርዱ ቀመሩን የሰራሁት ከ111 ሀገሮች ተሞክሮ ወስጄ ነው ቢልም፡፡ ተሳታፊዎቹ የሌሎች ሀገሮች ተሞክሮ እና የኢትዮጵያ ተሞክሮ የሚለያይ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ገዥ ፓርቲ ለዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ የማይጨነቅ፣ ተቃዋሚዎችን ለማጥፋት የሚሰራና የይስሙላ ምርጫ የሚያደርግ በመሆኑ ለንፅፅር የሚቀርብ አይደለም ስለዚህ ከኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ ተነስተን ቀመሩን እናውጣ በማለት ምርጫ ቦርድ ያቀረበው የፋይናንስ ክፍፍል ቀመር ውድቅ ተደርጐበታል፡፡
በምርጫ ቦርድ የቀረበውን የፋይናንስ ድጋፍ ክፍፍል ተገቢ ነው የሚል ድጋፍ የሰጠው የኢህአዴግ ተወካይ ብቻ ሲሆን ሌሎች ተሳታፊዎች ተቃውሞ በማሰማትና ቀመሩን ባለመቀበል ኢህአዴግ ብቻውን የቆመበት ስብሰባ ነበር ሲል የአንድነት ፓርቲ ተወካይ አቶ ዳንኤል ተፈራ ተናግሯል፡፡ በመጨረሻም ቦርዱ የቀረበበትን ተቋም ከግምት አስገብቶ የፋይናንስ ክፍፍል ቀመሩን አስተካክሎ እንደሚቀርብ ይጠበቃል፡፡
ምንጭ፡ ፍኖተ ነፃነት
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ለአዳሩ ሰልፍ የእውቅና ደብዳቤ አስገባ
- ቦታው መስቀል አደባባይ እንዲሆን ወስኗል
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ከህዳር 27/2007 ዓ.ም እስከ ህዳር 28/2007 ዓ.ም ለሚደረገው የአዳር ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬ ህዳር 18/2007 ዓ.ም ለአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የእውቅና ደብዳቤ አስገባ፡፡
ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል የገባው ደብዳቤ በሰማያዊ፣ መኢዴፓ እና ኢብአፓ ተፈርሞ የገባ ሲሆን የእውቅና ደብዳቤውንም ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲና የትብብሩ ሊቀመንበር፣ የከንባታ ህዝቦች ሊቀመንበርና የትብብብሩ ም/ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርጌሎ፣ አቶ ግርማ በቀለ ከኦሞ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅትና የትብብሩ ፀኃፊ እና የመኢዴፓ ሊቀመንበርና የትብብሩ ገንዘብ ያዥ አቶ ኑሪ ሙደሲር አስገብተዋል፡፡የትብብሩ አመራሮች ወደ ሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍሉ በሄዱበት ወቅት የአቶ ማርቆስ ተወካይ ለሆኑት አቶ ፈለቀ አበበ ደብዳቤውን ለመስጠት ጥረት ቢያደርጉም ተወካዩ ‹‹የከንቲባ ጉዳዮች ጽ/ቤ ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው የለም፡፡ እሱ ካልመራበት መቀበል አንችልም›› በሚል ደብዳቤውን አልቀበልም እንዳሏቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ አመራሮቹ ወደ አቶ አሰግድ ቢሮ ቢያቀኑም እንዳላገኙዋቸው ጨምረው ገልጸዋል፡፡
ሆኖም የትብብሩ አመራሮች ደብዳቤ መስጠት እንጂ ደብዳቤ ማስመራት የሰራተኞቹ እንጂ የእነሱ ስራ እንዳልሆነ በመግለጽ ደብዳቤውን ዛሬ ህዳር 18/2007 ዓ.ም ታመዋል የተባሉት የአቶ ማርቆስ ተወካይ የሆኑት አቶ ፈለቀ ቢሮ በአራት ምስክሮች ፊት አስቀምጠው መምጣታቸውን አስረድተዋል፡፡ አመራሮቹ የእውቅና ደብዳቤውን አቶ ፈለቀ ቢሮ አስቀምጠው ከመውጣታቸውም ባሻገር በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት በፈጣን መልዕክት (ኢ ኤም ኤስ) በሪኮመንዴ ቁጥር eg157416502et መላካቸውን ገልጸዋል፡፡
የአዳር ሰላማዊ ሰልፉ ህዳር 27 ከጠዋቱ 3 ሰዓት ተጀምሮ ህዳር 28 ከቀኑ 6 ሰዓት ላይ እንደሚጠናቀቅ የሚጠበቅ ሲሆን ቦታውም መስቀል አደባባይ ላይ እንደሚሆን መወሰኑ ታውቋል፡፡
የትብብሩ አመራሮች የእውቅና ደብዳቤውን ለማስገባት በሄዱበት ወቅት በቦታው የትብብሩ አመራሮች የሚያውቋቸው ደህንነቶች ባለ ጉዳይ በመምሰል ይመላለሱ እንደነበርና ፖሊሶችም ይከታተሉ እንደነበር መግለፃቸውን የነገረ-ኢትዮጵያ ዘገባ አመልክቷል፡፡
The 40/60 Housing Construction plan that Ignored Citizens’ Income and capacity
Bisrat Woldemichael
Shelter is one of the basic necessities to human beings. In the past Derg Regime, any citizen aged 18 years and above can acquire 500m2 plot of land with the least service fee of 50-100 Birr provided he/she is capable to construct; however evidences testify that those incapable are loaned from 7-14 thousand Birr for the apartment construction with 20 Years repayment schedule.
Currently, the citizens are being deprived of land ownership due to the policy that stated “Land belongs to the public & the government” following the proclamation “Land belongs to the government.” To the contrary, it seems that only members of the ruling party are beneficiaries of this system and other citizen are being dislocated from their habitat. Comparatively, the outstanding members of the ruling party are grabbing many houses and urban lands.
Condominium houses Construction
In 2005, the low cost condominium houses construction begun for low income citizens following the new government project. At that time, more than 470 thousand residents were registered in Addis Ababa only but the information disclosed by the city administration shows that only 72 thousand houses were allocated in the last 7 years.
This means that the government handed over houses only to 15% of the registrants in the past 7 years. The remaining registrants remain uncertain for when they will be getting their houses. The city mayor disclosed officially that there is no more registration for condominium houses at this right time.
The New Housing plan
Due to the drawbacks in fulfilling housing needs by Condominium construction, the new housing plan was currently put forward.
This new housing plan, called the 40/60, requires saving of 40% of the housing cost for five consecutive years. The remaining 60% shall be paid within 17 years after handing over of the house completing the 40% payment.
It is disclosed that the project commences in 2012/13 but details are not known yet. As per the general quotation from the city administration, the one bed room house candidate is expected to save 857 birr monthly that total cost is 128,590 birr. The two bedroom house candidate is expected to save Birr 1,337 monthly that costs total birr 200,475. A candidate to three bedroom house is expected to save birr 2,133 monthly that total cost is 320,000 birr.
The city administration disclosed that these houses are intended for the low income groups without clue to the average low income of citizens. I went to the Central Statistics Agency (CSA) to look for the average income of citizens (as low, medium and high) via the ministry of Finance & Economic Development; the office informed me that even if they have data for the last five years, they cannot allow such data before permission from the ministry and approval of the foreign donors. That may be due to the myth, as one official told me in secret, that these offices are accountable to the donors and not to the public at large. I have calculated education level and average salary of government employees and put the fact forward.
The average salary of the lowest scale (guards & Laborers) and one year academic trainees is 800 birr, the master’s levels get 2500 birr and doctorate degrees get 3500 birr respectively. The above employees have such monthly deductions as income tax, pension funds, contribution for Abay Dam, EPRDF membership contribution which totals ranges from 15-20%.
Residents’ status
Economists’ device that employees free from any addiction could save up to ¼ of his/her salary. The saving for emergencies and long term investments including house rent fees.
As mentioned above, the highly paid doctorate degree graduate shall save only to the maximum of 700 birr; as testified by an economist in Addis Ababa University. Accordingly, a highly paid doctorate degree employee is expected to save birr 857 to get the least one bedroom house but unfortunate to save such amount monthly.
However, I would like to notify that the above calculations did not include the farmers and business people.
Generally, some residents in Addis Ababa City mention that they doubt the 40/60 housing plan fits the citizens’ capacities. Therefore, it is not clear up to now that, which the target beneficiaries will be.
Even though housing construction is very important, the target citizens and responsible government bodies are not known yet; some residents in Addis Ababa who need house told me that housing construction is a dire need but due to ambitious government expenditures, they suspect the plan is designed to compensate the lack of finances. They reasoned that besides the current inflation and high cost of living, they cannot pay the monthly saving amid the plan failed to consider citizens’ capabilities that lacks transparency and questioning the success of the projects.
Update፡ The above “40/60 housing project” article posted on March 2013. But after 3 months the Ethiopian government city construction and development ministry, within alternatives based on the city residence income automatically changed the project into 10/90, 20/80, 40/60 and 50 % saved before registration in the form of as an association. Finally, the new housing project implemented on June 20, 2013 because of failures of earlier 40/60 project.





