Daily Archives: March 10th, 2013

ማስፈራሪያና ዛቻ ያልተበረዘ ንፁህ መረጃን ለህዝብ ከማድረስ አይገታኝም !!

ከበትረ ያዕቆብ

mycountryethiopia@gmail.com

OLYMPUS DIGITAL CAMERAዉድ የሀገሬ ልጆች ከሁሉም በማስቀደም እንደምን ናችሁ ? ደህና ናችሁ ? እንዴት ናችሁ ? ስል የጠበቀ ሰላምታየን ማቅረብ እወዳለሁ፡፡ መቼም እዚች ላይ ምነዉ ሰላምታ አበዛህሳ እንደማትሉ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ምክንያቱም “አሸባሪ ፣ ፀረ ሰላም ፣ አክራሪ”… ወዘተ የሚል ተለጣፊ ስም ለሀገር ወዳድና ለመብታቸዉ መከበር ድምፃቸዉን ለሚያሰሙ ሁሉ በጅምላ እየተሰጠ ዜጎች በሀሰት በሚወነጀሉበት ሀገር ፤ በእያንዳንዷ ቀን እንደ መልካም ተግባር መሰል ዜጎችን ጠልፎ ለመጣል የተንኮል ወጥመድ ሲጠመድ በሚዋልበት ሀገር ፤ በየስራ ቦታዉ ፣ በየመዝናኛ ስፍራዎች ፣ በየመንገዱ… ሲያነፈንፉ የሚዉሉ የወሬ ‹‹ተኩላዎች›› እንደ አሸን በፈሉበት ወቅት ፣ ንፁህ ዜጎች በግዳጅ ያልፈፀሙትን ኃጢያት እንዲናዘዙ በሚገደዱበት ሀገር ፤ በልቶ ማደር በከበደበት ጊዜ አጥብቆ ደህንነትን መጠየቁ ተገቢ ነዉና፡፡ እንደዉም ከዛም በዘለለ ብዙ ቢባል እንኳ የሚበዛ አይመስለኝም፡፡ መቼም እዚህ ላይ ለማለት የፈለኩት ለሁሉም ሰዉ ግልፅ ይመስለኛል፡፡ የሆነ ሆኖ ለሰላምታ ያህል ይህን ካልኩ ወደ ፍሬ ሀሳቤ ልለፍ፡፡

እንደሚታወቀዉ በአለማችን ለጋዜጠኞች አደገኛ ከሚባሉት አገራት መካከል አንዷ አገራችን ኢትዮጵያ ናት፡፡ እንደዉም ግንባር ቀደሟ፡፡ እርግጥ ከላይ ከጠቀስኩት በመነሳት ለምን ለጋዜጠኞች ብቻ ትላለህ ፤ ጠቅለል አድርገህ ለዜጎቻቸዉ አደገኛ ከሚባሉት አገራት መካከል አገራችን ኢትዮጵያ ግንባር ቀደሟ ናት አትልም? ልትሉ ትችላላችሁ፡፡ ሆኖም ያን ያልኩት በዋናነት በፅሑፌ ላነሳዉ ወደ ፈለግኩት ርዕሰ ጉዳይ በቀጥታ ለመንደርደር ያመቸኛል በሚል እንጅ ትክክል ናችሁ፡፡ እናም እንደሚታወቀዉ በሀገራችን ጋዜጠኞች ለብዙ ችግርና ፈተና ይዳረጋሉ፡፡ ለምሳሌ ከሚደርስባቸዉ መጠነ ሰፊ የሚባል ማስፈራሪያ ፣ ዛቻና ወከባ ባሻገር በእብሪተኛና ኃላፊነት በጎደላቸው የደህንነት ሰዎች ሰብዓዊነት በጎደለዉ ሁኔታ ይደበደባሉ ፣ ያለ ምክንያት ለሰዉ ልጅ ቀርቶ ለእንስሳት እንኳን ወደማይመቹ ‘እስር ቤቶች’ ይወረወራሉ ፣ ሲልም ከዚያ የከፋ ነገር ይፈፀምባቸዋል፡፡ እዚህ ላይ ሙያዊ ኃላፊነታቸዉን መወጣታቸዉ እንደ ወንጀል ተቆጥሮ በእነ እስክንድር ነጋ፣ ውብሸት ታዬ እና ርዕዮት አለሙ ላይ የተፈፀመባቸዉ ያለዉ ዘግናኝ ግፍ እንዲሁም በእነ ተመስገን ደሳለኝ ላይ እየደረሰ ያለዉ መከራ ለምሳሌነት ተጠቃሽ ነዉ፡፡ እንግዲህ እኔም ይህችን አጭር ፅሑፍ ቢጤ ለመፃፍ ምክንያት የሆነኝ ከዚህ ከሀገራችን መንግስት ጋዜጠኞችን የማሳደድ አባዜ ጋር በተያያዘ በእኔም ላይ በደህንነት አባሎች እየተፈፀመብኝ ያለ ወንጀል ሲሆን ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ቢያዉቀዉ መልካም ነዉ በሚል እሳቤ አንዳንድ ነገሮችን ለመጠቆም ወድጃለሁ፡፡

ዉድ የሀገሬ ልጆች እንደሚታወቀዉ ከዚህ በፊት በደረሱብኝ የተለያዩ ዛቻዎችና ማስፈራሪያዎች ምክንያት ለደህንነቴ በመስጋት ከምሰራበት መንግስታዊ ካልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ስራዬን ለመልቀቅና መኖሪያዬን ከባህር ዳር ከተማ ወደ አዲስ አበባ ለመቀየር ተገድጄ ነበር፡፡ ይህንንም ያደረግኩት ከባህር ዳር ይልቅ አዲስ አበባ አንፃራዊ ሰላም ያለበትና ለደህንነቴም ቢሆን የተሻለ ነዉ በሚል ተስፋ ነዉ፡፡ እንግዲህ ከዚያ ጊዜ ጀምሮ በዋናነት መሰረቱን ጣሊያን ሀገር ላደረገ www.assaman.info  ለተባለ ድህረ-ገፅ የምሰራ ስሆን ፤ በተጨማሪም በፈቃደኝነት ሀገርን የማገልገል አላማ በማንገብ  www.thedailyjournalist.comበተባለ ድህረ-ገፅ እና እንደከዚህ ቀደሙ የግሌ በሆነዉ www.ethiopiahot.wordpress.com(personal Blog) ላይ እየሰራሁ እገኛለሁ፡፡ ከዚህም ባሻገር ፅሑፎቸን እንደ http://ecadforum.comላሉ የተለያዩ ኢትዮጵያዊ ድህረ ገፆች በመላክ እንዲወጡ አደርጋለሁ፡፡

ይሁንና ምንም እንኳን እዉነቱ የምሰራዉ ስራ ለሀገርና ለወገን የሚበጅ ቢሆንም ሰሞኑን እየደረሱብኝ ያሉት ማስፈራሪያዎችና ዛቻዎች ከበፊቶቹ እየተለዩና እየከበዱ የመጡ ሲሆን ፤ ከእስራት ወደ ግድያም ተሸጋግሯል፡፡ የምንደዉለዉ ከማዕከላዊ ነዉ የሚሉት እነዚህ የደህንነት ሰዎች በፅሑፎቼ ላይ ተገቢ አስተያየት ከመስጠት እና እንዲስተካከል ከመጠየቅ ይልቅ በአምባገነን ስሜት አፋቸዉን ሞልተዉ መፃፍ አቁም ስንልህ ባለማቆምህ “ልናስወግድህ” ነዉ በማለት እየዛቱብኝ ይገኛሉ፡፡ የዛቱትንም በቅርቡ ተግባራዊ እንደሚያደርጉ እየገለፁ ይገኛል፡፡ 

ለምሳሌ በጥር 16 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቀኑ በ7፡51 ሰዓት ላይ በተደረገልኝ የስልክ ጥሪ፡- “ደጋግመን እንድታቆም ነግረንህ ነበር፡፡ አንተ ግን እንኳን ልታቆም እንደዉም ብሶብሃል፤ባለፉት ግዚያት በተደጋጋሚ ይከሰስ ተብሎ አስፈላጊ ዶክመንቶችን በመሰብሰብ አንዳንድ ዝግጅት ስናደርግ ነበር፡፡ በተለይም ከኦጋዴን ጋር በተያያዘ ፅፈህ በለቀቅከዉ ፅሑፍ እና ከዚያ ወዲህ በለቀቅካቸዉ፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ግን በቅርቡ ቶርቸር ምናምን በሚል ሌላ ፅሑፍ ለቅቀሀል፡፡ ስለሆነም አሁን አንተን ማስወገድ የሚለዉን የተሻለ አማራጭ ሁኖ አግንተነዋል፡፡ በማንኛዉም ዓይነት ዘዴ አንተን ማስወገድ፡፡” የሚል ከበድ ያለ ዛቻ ሰንዝረዉብኛል፡፡

በድጋሚ በጥር 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ከቀኑ በ10፡05 ሰዓት ላይ በተደረገልኝ ሌላ የስልክ ጥሪ ደግሞ፡- “ባለፈዉ የነገርኩህን አቅልለህ ወይም እንደ ቀልድ እንዳላየኸዉ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡… ከዚህ በኋላ ከአንተ ጋር የመጨቃጨቂያ ጊዜ የለንም፡፡  …የስራህን ዋጋ በቅርቡ ታገኛለህ…፤ ተዘጋጅ!!” በማለት ዝተዉብኛል፡፡

ከላይ ከተጠቀሱት ዛቻዎችና ማስፈራሪያዎች በተጨማሪ እነዚህ የደህንነት ሰዎች የተለመደዉን “ሽብርተኛ” የሚል የሐሰት ካባ በሙያ ጓደኞቼ ላይ እንደደረቡት ሁሉ በእኔ ላይም ለመደረብ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ በተደጋጋሚ “እያንዳንዷን ስራህን እናዉቃለን ፣ ለማን እንደምትሰራም እንዲሁ ፣ ስለአንተ ከበቂ በላይ ማስረጃ አለን…”  እያሉ ለሐሰት ዉንጀላ መንገድ እየጠረጉ ይገኛል፡፡ በተለይም በጥር 20 ቀን 2005 ዓ.ም. በተደረገልኝ የስልክ ጥሪ ላይ ከንግግራቸዉ በግልፅ እንደተረዳሁት የኢህአዴግ መንግስት “አሸባሪ” ሲል ከፈረጀዉ የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አዉጭ ግንባር(ኦብነግ) ጋር ምንም ሚያገናኘን ነገር በሌለበት ሁኔታ ግንኙነት ያለ ለማስመሰል እየሞከሩ ነዉ፡፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ የግንባሩ በሆነዉ ድህረ-ገፅ ላይ የወጡትን ፅሑፎቼን ለግንኙነቱ እንደ አንድ ማሳያ እንደሆኑ በተዘዋዋሪ እየጠቀሱ ይገኛል፡፡

እዚህ ላይ ግልፅ ማድረግ የምፈልገዉ እነዚህ ፅሑፎች እኔ የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አዉጭ ግንባርን ለመርዳት በማሰብ የፃፉኳቸዉ ወይንም እኔ በቀጥታ ለግንባሩ  የላኳቸዉ አለመሆናቸውን ነዉ፡፡ ይልቁንም የግንባሩ ጋዜጠኞች ከተለያዩ ድህረ-ገፆች ላይ ራሳቸዉ እንደማንኛውም የዓለማችን ጋዜጠኛ የወሰዷቸዉ ናቸዉ፡፡ ሆኖም ግን በእኔ ስለተፃፉና ስሜ ስለተጠቀሰባቸዉ ብቻ ያንን ሊሉ ችለዋል፡፡ ይህም ደግሞ ድህረ-ገፆችና የዜና አዉታሮች መረጃን እንዴት እንደሚቀባበሉ ጠፍቷቸዉ ያደረጉት ነዉ የሚል እምነት የለኝም ፣ እንዴትስ ድህረ-ገፆችን በማናለብኝነት ሲዘጉ ፣ ሲከፍቱ ፣ ኢሜሎችን ያለ ይለፍ ቃል (Password) ሲጎረጉሩ ለሚዉሉት የኢህአዴግ ‹‹ተኩላዎች›› ይህን መረዳት ያዳግታቸዋል?

ዉድ የሀገሬ ልጆች! እኔ ለማንም ኢትዮጵያዊ መጥፎ የምመኝ ፣ የሀገርን ደህንነት ለርካሽ ጥቅም ስል አሳልፌ የምሰጥ ፣ ሽብር ፈጣሪ… አይደለሁም፡፡ እኔ ሀገሬን ፣ ወገኔን የማፈቅር ፣ ለሀገሬና ወገኔ ለሆነዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ሰላም ፣ ፍቅርና ብልፅግናን ሌት ተቀን የምመኝና የምሰራ አንድ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ነኝ፡፡ እኔ አቅሜ በቻለዉ መጠን በሙያዬ ሀገሬንና ወገኔን ለማገልገል ሙሉ በሙሉ ፍቃደኛ የሆንኩና ለዚያም የምንቀሳቀስ ተራ ሰዉ ነኝ፡፡ እነርሱ ሊያስመስሉ እንደሚሞክሩት አይነት ወንጀለኛ ሳልሆን መብቱን በአግባቡ ለመጠቀም የሚታትር ንፁህ ዜጋ ነኝ፡፡ ይህን ሁሉም ኢትዮጵያዊ በግልፅ እንዲረዳልኝ እፈልጋለሁ፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ እነዚህ ኃላፊነት የጎደላቸው የደህንነት ሰዎችም ሆኑ አለቆቻቸዉ አንድ ሊያዉቁት የሚገባ ቁም ነገር አለ እላለሁ፡፡ ይህም እኔንና መሰል ምስኪን ጋዜጠኞችን አሳዶ በመደብደብ ፣ በማሰር ወይም በመግደል የመንግስትን ጉድፍ ከአለም ህዝብ አይን መሸሸግ ከቶም አይቻልም፡፡ እንኳን እነርሱ እንደሚያስቡት ቀርቶ ጊዜያዊ መፍትሄ ሊሆንም አይችልም፡፡ ይልቁንም እያንዳንዱ መሰል እርምጃቸዉ የሚያመልኩትን ፓርቲያቸዉንም ሆነ የገነቡትን አምባገነናዊ አገዛዝ የባሰ መጥፎ ገፅታን እያላበሰዉና በሀገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ ተቃዉሞን እያስከተለበት ይሄዳል፡፡ ይሄም ዞሮ ዞሮ የሚፈሩትን ዉድቀት ያስከትላል፡፡ እዚህ ላይ ምናልባት እነ እስክንድር ነጋን በማሰራቸዉ እየደረሰባቸዉ ያለዉ የፖለቲካ ክስረት እንደ ምሳሌ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ ደግሞም ዱላዉና እስሩ የበለጠ እልህን ይፈጥር ይሆናል እንጅ እኔንም ሆነ የሙያ አጋሮቼን ከምንወደዉ ሙያችን ሊያቆራርጠን ፍፁም አይቻለዉም፡፡

ዉድ የሀገሬ ልጆች! ሀገር እንድታድግ ወይንም በማይጨበጥ ተስፋ ኢህአዴግ አስመዘግበዋለሁ የሚለዉ አይነት የኢኮኖሚ ብልፅግና ታስመዘግብ ዘንድ ሁሉም የሀገሪቱ ዜጋ በየተሰማራበት የሙያ ዘርፉ የሙያዉን ስነ ምግባር አክብሮ በትጋት ሊሰራ ይገባል፡፡ ጋዜጠኛዉ ፣ ዶክተሩ ፣ ኢንጅነሩ ፣ ነጋዴዉ ፣ መምህሩ ፣ ፖለቲከኛዉ… ሁሉም፡፡ ይህ የግሌ አመለካከት ሳይሆን የአለም ህዝብ በጋራ የተስማማበት እዉነት ነዉ፡፡ ከዚህ የእዉነት ሀ፣ ሁ በመነሳትም ባሳለፍኩት የስራ ጊዜያቶች በምወደዉ የጋዜጠኝነት ሙያዬ ለሀገሬ ይበጃል ያልኩትን በታማኝነት ለማድረግ ሞክሬያለሁ፡፡ አሁንም እየሞከርኩ እገኛለሁ፡፡ ለወደፊቱም ሙያዬ ያልተበረዘ ንፁህ መረጃን ለህዝበ ማድረስ እንደመሆኑ ያንን ከማድረግ ምንም አይነት ማስፈራሪያም ሆነ ዛቻ እንደማያቆመኝ በእርግጠኝነት ለመናገር እወዳለሁ፤ ይህንንም እናንተ ዉድ የሀገሬ ልጆች በግልፅ እንድታዉቁልኝ እፈልጋለሁ፡፡

 

The 40/60 Housing Construction plan that Ignored Citizens’ Income and capacity

Bisrat Woldemichael

kuma-demeksaShelter is one of the basic necessities to human beings. In the past Derg Regime, any citizen aged 18 years and above can acquire 500m2  plot of land with the least service fee of 50-100 Birr provided he/she is capable to construct; however evidences testify that those incapable are loaned from 7-14 thousand Birr for the apartment construction with 20 Years repayment schedule.

Currently, the citizens are being deprived of land ownership due to the policy that stated “Land belongs to the public & the government” following the proclamation “Land belongs to the government.” To the contrary, it seems that only members of the ruling party are beneficiaries of this system and other citizen are being dislocated from their habitat. Comparatively, the outstanding members of the ruling party are grabbing many houses and urban lands. 

                        Condominium houses Construction

In 2005, the low cost condominium houses construction begun for low income citizens following the new government project. At that time, more than 470 thousand residents were registered in Addis Ababa only but the information disclosed by the city administration shows that only 72 thousand houses were allocated in the last 7 years.

This means that the government handed over houses only to 15% of the registrants in the past 7 years. The remaining registrants remain uncertain for when they will be getting their houses. The city mayor disclosed officially that there is no more registration for condominium houses at this right time.

                      The New Housing plan

Due to the drawbacks in fulfilling housing needs by Condominium construction, the new housing plan was currently put forward.

This new housing plan, called the 40/60, requires saving of 40% of the housing cost for five consecutive years. The remaining 60% shall be paid within 17 years after handing over of the house completing the 40% payment. 

It is disclosed that the project commences in 2012/13 but details are not known yet. As per the general quotation from the city administration, the one bed room house candidate is expected to save 857 birr monthly that total cost is 128,590 birr. The two bedroom house candidate is expected to save Birr 1,337 monthly that costs total birr 200,475. A candidate to three bedroom house is expected to save birr 2,133 monthly that total cost is 320,000 birr.

The city administration disclosed that these houses are intended for the low income groups without clue to the average low income of citizens. I went to the Central Statistics Agency (CSA) to look for the average income of citizens (as low, medium and high) via the ministry of Finance & Economic Development; the office informed me that even if they have data for the last five years, they cannot allow such data before permission from the ministry and approval of the foreign donors. That may be due to the myth, as one official told me in secret, that these offices are accountable to the donors and not to the public at large. I have calculated education level and average salary of government employees and put the fact forward.

The average salary of the lowest scale (guards & Laborers) and one year academic trainees is 800 birr, the master’s levels get 2500 birr and doctorate degrees get 3500 birr respectively. The above employees have such monthly deductions as income tax, pension funds, contribution for Abay Dam, EPRDF membership contribution which totals ranges from 15-20%.

                 Residents’ status

Economists’ device that employees free from any addiction could save up to ¼ of his/her salary. The saving for emergencies and long term investments including house rent fees.

As mentioned above, the highly paid doctorate degree graduate shall save only to the maximum of 700 birr; as testified by an economist in Addis Ababa University. Accordingly, a highly paid doctorate degree employee is expected to save birr 857 to get the least one bedroom house but unfortunate to save such amount monthly.

However, I would like to notify that the above calculations did not include the farmers and business people.

Generally, some residents in Addis Ababa City mention that they doubt the 40/60 housing plan fits the citizens’ capacities. Therefore, it is not clear up to now that, which the target beneficiaries will be.

Even though housing construction is very important, the target citizens and responsible government bodies are not known yet; some residents in Addis Ababa who need house told me that housing construction is a dire need but due to ambitious government expenditures, they suspect the plan is designed to compensate the lack of finances. They reasoned that besides the current inflation and high cost of living, they cannot pay the monthly saving amid the plan failed to consider citizens’ capabilities that lacks transparency and questioning the success of the projects.

 Update   The above “40/60 housing project” article posted on March 2013. But after 3 months the Ethiopian government city construction and development ministry, within alternatives based on the city residence income automatically changed the project into 10/90, 20/80, 40/60 and 50 % saved before registration in the form of as an association. Finally, the new housing project implemented on June 20, 2013 because of failures of earlier 40/60 project.

 

Opposition Political Parties Showing Reservation to the Ethiopian National Transitional Council (ENTC)

By Betre Yacob.

Ethiopian National Transitional Council (ENTC)Opposition political parties in Ethiopia are said to have been showing reservation to the Ethiopian National Transitional Council (ENTC), which has been working to overthrow the Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) tyrannical regime that has been abusing, oppressing and exploiting its own people.

One ENTC leadership told this writer in an interview that although opposition political parties working in Ethiopia expressed their support to the Council (ENTC) — most of them have so far shown reservation to work together.

“When we formed ENTC, we had anticipated the joining of the other political groups under this umbrella. Hence the structure of the organization was designed in a bi-cameral way where organizations will have one wing with their voices and votes, and the public will be on the other end. To that effect, written invitations were sent to all the organized groups that are struggling for change in Ethiopia. Unfortunately, this did not work out as the opposition parties had some reservations even though they expressed support to the council”, he said.

The leadership, who said that the opposition political parties needed time to feel comfortable to rally behind the idea and join this new organization, said that —recognizing the problem —the general assembly of the council had passed a resolution in July 2012— to mobilize the public and, in the mean time, work closely with the other political parties and civic organizations.

“Accordingly, we are working together with other political parties in defining the roadmap and target around the alternative that ENTC believes yields success. Along with several other political parties and civic organizations, we have formed the “Joint Coordinating Committee of Ethiopian Democratic Forces” to help strengthen the cooperation. This committee is comprised of subcommittees and task forces which help develop the working relationships between the organizations”, he said.

The leadership also said that studying the past history of Ethiopian politics and assessing current political situations in Ethiopia, ENTC believed that along with the struggle for freedom— it was not too early to start thinking and planning of what was beyond.

“We believe that creation of an all-inclusive transitional government will help us have a framework and readiness that is required if the regime falls. In addition to that, having this institution beforehand will force the disparate political groups to work under one umbrella strengthening the struggle, hence two birds with one stone. Currently ENTC is calling for the formation of such an institution”, he explained.

Different political analysts argue that the Ethiopian National Transitional Council (ENTC) has been the first ever and wise development in the Ethiopian opposition politics. They are optimistic that the council will strengthen the Ethiopian struggle for freedom by bringing opposition political parties —which have been so fragmented.

The Ethiopian National Transitional Council (ENTC) was officially established in Dallas, USA on July 3, 2012, by Ethiopians from all over the world. It has been given the objective to overthrow the EPRDF regime and facilitate a peaceful transition of power to opposition political parties through participatory, fair, and democratic election.

Since its establishment, the council have done so many successful activities. For instance, it has managed to organize and mobilize Ethiopians that were part of the silent majority at the grassroots level in different local councils / chapters from all over the world including some in Africa. In addition, it has been doing meaningful works to influence western governments, which are the backbone of the tyrant regime in Ethiopia, to stand for the demand of the Ethiopian people.

%d bloggers like this: