ከኮለኔል መንግስቱ እና ከአቶ መለስ ለኢትዮጵያ ሕፃናት አባት በመሆን ፋውንዴሽን ሊመሰረትለት የሚገባው ማነው?
”ጎዳና ቤቴ’
ሰኔ 25/2012 እአአቆጣጠር በቢቢሲ ድህረ ገፅ ላይ በወጣ አንድ ዘገባ መሰረት ኢትዮጵያ በአመት 5ሺህ በላይ ሕፃናት በማደጎነት ወደ አሜሪካ ብቻ እንደሚሄዱ እና አሜሪካ ከዓለም ላይ በማደጎነት ከምትወስደው ሕፃናት ኢትዮጵያውያን ሕፃናት ከ አምስቱ አንዱ እንደሆኑይገልፃል።(http://www.bbc.co.uk/news/world-africa-18506474)
ከኮለኔል መንግስቱ እና ከአቶ መለስ ለኢትዮጵያ ሕፃናት አባት በመሆን ፋውንዴሽን ሊመሰረትለት የሚገባው ማነው?
ቅዳሜ ጧት
” አቡነጎርጎርዮስ የዝዋይ ገዳም መስራች አንድቀን የመንፈስ ልጆቻቸውን እያስተማሩ ኮለኔል መንግስቱ ከአዋሳ ሲመጡ ጎራ ይላሉ።ወደ ገዳሙ ውስጥ ሳይገቡ ገና አጥሩን ሲመለከቱ በረጅሙ ታጥሮ ይመለከቱ እና ‘ይሄ መነኩሴ ይህን ይህል ቦታ አጥሮ አገሩ ታድያ ምን ተረፈ’ ይሉ እና አንዱን ወታደር አቡነ ጎርጎርዮስን እንዲጠራቸው ይልኩታል። አቡነ ጎርጎርዮስ መልክቱ እንደደረሳቸው ‘አሁን ትምህርት ላይ ነኝ ደግሞስ ፈላጊ ይመጣል እንጂ ተፈላጊ እንዴት ይሄዳል?’ ብለህ ንገረው ብለው መልሰው ይልካሉ።ኮለኔል መንግስቱ እንዲህ አይነት ድፍረት በመስማታቸው ምንም ሳይሉ ወደ አዲስ አበባ ይመለሳሉ። በቀጣዩ ቀናት አቡነ ጎርጎርዮስ ኮለኔል መንግስቱን ቅሬታቸውን ለመንገር ይመጣሉ።ቅሬታቸው ሌላ ነበር።እንደገቡ አቡነ ጎርጎርዮስ በቁጣ ”ለመሆኑ ሕፃናት አምባ የምታሳድጋቸው ልጆች አምላካቸውን ካላወቁ አውሬ እንደሚሆኑ ታውቃለህ?” ይሉታል ይደነግጣል። ”ምን ይደረግ?” ይላቸዋል።”ለእኔ ፍቀድልኝ እኔ የማደርገውን አውቃለሁ ” ይሉታል። ከድጋፍ ደብዳቤ ጋር ይልካቸዋል።
ምንጭ ፡- ከጉዳያችን ብሎግ የተወሰደ
የነ አቶ አንዱዓለም አራጌና ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ክስ ውሳኔ በድጋሚ ተቀጠረ
በእነ አንዱዓለም አራጌ የክስ መዝገብ ለፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ይግባኝ የጠየቁት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አቶ አንዱዓለም አራጌ እንዲሁም እውቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ አቶ ናትናኤል መኮንን፣ አቶ አንዱዓለም አያሌው፣ ሻምበል የሺዋስ ይሁንዓለም፣አቶ ዮሐንስ ተረፈ፣አቶ ክንፈሚካኤል ደበበ እና አቶ ምትኩ ዳምጤ ውሳኔ ለዛሬ መጋቢት 30 ቀን 2005 ዓ.ም. ተቀጥሮ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ 6 ኪሎ የሚገኘው የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የይግባኙን የመጨረሻ ውሳኔ ይሰጣል ተብሎ ቢጠበቅም ውሳኔውን ሳይሰጥ ለአምስተኛ ጊዜ ለሚያዚያ 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ተቀጠረ፡፡
ፍርድ ቤቱም ውሳኔውን ሊሰጥ ያልቻለበትን ምክንያት ሲገልፅ የክሱን ሂደት ገና መርምሬ አልጨረስኩም በሚል ተጨማሪ ቀነ ቀጠሮ መስጠቱን አስታውቋል፡፡ በወቅቱ የፍርድ ቤቱ ዳኞች ሽመክት አሰፋ፣ በላቸው አንሺሶ እና ዳኜ መላኩ ተሰይመው ሲሆን ከከሳሽ በኩል አቃቤ ህግ ብርሃኑ ወንድማገኝ እንዲሁም ከተከላካይ ጠበቆች አቶ አበበ ጉታ፣ አቶ ደርበው ተመስገን እና አቶ ሳሙኤል አሰፋ ተገኝተዋል፡፡ ተከሳሾችም በሰዓቱ የቀረቡ ቢሆንም የነበረው በበርካታ ያልተለመደ የጦር መሳሪያ አጀብ አዲስ ያልተለመደ ክስተት ቢሆንም በተለይ የአቶ አንዱዓለም አራጌ በከፍተኛ ደረጃ መጎሳቆል የችሎት ታዳሚዎችን ሐዘን ውስጥ ከቶ ተከሳሾቹ የውሳኔ ፍርዱ ሳይሰጥ ከቀኑ 6፡30 ሰዓት ወደ የመጡበት እስር ቤት ተመልሰዋል፡፡
ማፈናቀሉ እስከመቼ?
ብስራት ወልደሚካኤል
ህወሓት/ኢህአዴግ በህይወቱ ከሚፈራውና ከሚጠላው ነገር አንዱ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ዜጋ ማየትና መስማት ነው፡፡ ምክንያቱም የድርጅቱ አባላት በባህሪያቸው በውሸት፣ በተንኮልና በዕውቀት አስተሳሰብ አድማስ ደካማ ስለሆኑ የዜጎችን አንድነትና ብሔራዊነት ስሜትን አጥብቀው ይጠላሉ፤ ይህንንም በማሰራጨት የማሃይሞችን ርካሽ ፖለቲካ አራምደውበታል፣እያራመዱም ይገኛሉ፡፡ የዚህ ዋነኛ ተባባሪ ደግሞ በህወሓት የሚነዱት ብአዴን፣ ኦህዴድ እና ደኢህዴን ናቸው፡፡ በዚህም መሰረት የሀገሪቱን አንድነትና ደህንነት አደጋ ላይ በመጣላቸው ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በዝምታ ሊያልፍ ስለማይገባ እስካሁን ለፈፀሙት ሁሉ አስፈላጊውን ሰነድ በእጃችን ማስገባት፣ ድርጊቱን የፈፀሙትንና ተባባሪዎቹን ስም ዝርዝር ከነ ሙሉ አድራሻቸው መያዝ፣ ጉዳት የደረሰባቸውና ሚደርስባቸው ዜጎችን መርዳትና መንከባከብ እንዲሁም ወንጀለኞችን በተለያዩ ማኀበራዊ ሚዲያዎች(Facebook, blog, twitter,….) ጨምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን በማጋለጥ ለህግ እንዲቀርቡና ተጠያቂ እንዲሆኑ ማድረግ የሁላችንም ኢትዮጵያዊያን የውዴታ ግዴታ መሆን ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ዛሬ በሰፊው የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ላይ በህወሓት/ኢህአዴግ እየደረሰ ያለው ግፍ በተመሳሳይ መልኩ ነገ በሌሎችም ላይ ይደርሳል፤ ከዚህ በፊትም ደርሷልና፡፡
ስለዚህ በቅርቡ በደቡብ ክልል ቤንች ማጂ ዞን ጉራፈርዳ ወረዳ ለረጅም ጊዜ ሀብት ንብረት አፍርተውና ተዋልደው የኖሩ የአማርኛ ተናጋሪዎችን የማፈናቀል ስራ የተሰራውን መረጃ በሚመለከት ፣
አሁን ደግሞ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ያሶ ወረዳ እንዲፈናቀሉ የተደረጉት የአማርኛ ተናጋሪ ወገኖቻችን ለሞት.ለስቃይና ለመከራ እንዲደረጉ የተደረገበትን ምክንያት በዝርዝር በማጣርት መረጃውን ይፋ በማድረግ ሁሉም ዜጋ በጋራ ሊያወግዝና የተፈናቀሉትም ወደነበሩበት ስፍራ በክብር እንዲመለሱ ለማድረግ በሀግር ውስጥም ሆነ በውጭ ያሉ ኢትዮጵያዊያን በጋራ መስራት ይጠበቅብናል ብዬ አስባለሁ፡፡ ለዚህም በሀገር ውስጥ ያሉ የሚዲያ ባለሙያዎች፣ ፖለቲከኞች፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማት ወደስፍራው በመሄድ አስፈላጊውን ጥናት በማድረግ መረጃውን ለህዝብ ይፋ ማድረግና የድርጊቱ ፈፃሚዎችም በአስቸኳይ ለህግ እንዲቀርቡ አስፈላጊውን ሁሉ ማድረግ፣
በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ይህን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለዓለም አቀፉ ማኀበረሰብ በማጋለጥ ለኢህአዴግ የሚደረገው የለጋሾች ድጋፍ ለሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሚውል ማረጋገጥና ድጋፉ እንዲቋረጥ ከማድረግ በተጨማሪ መረጃውን ለሚሰበስቡ ሀገር ውስጥ ላሉ ሀገር ወዳድ ሰባዓዊ ባለሙያዎች የገንዘብ፣ የቁሳቁስና የሙያ ድጋፍ ማድረግ፣
በተለይ ወንጀሉ የሚፈፀምባቸው የአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ወገኖቻችን ወኪል ነኝ የሚለውን ብአዴን/ኢህአዴግ አባላት ጉዳዩን አጥብቀው በመጠየቅ ለድርጅቱ የሚያደርጉትን ድጋፍ ሙሉ ለሙሉ በማቋረጥ ለህዝብ እና ለሀገር ያላቸውን ወገንተኝነት ማረጋገጥ፣ ከፓርቲውም በይፋ በመልቀቅ ህዝባዊ ዓላማ ያለውን ትግል መቀላቀልና የወንጀል ተባባሪ አለመሆናቸውን በተግባር በማሳየት ከነገ ተጠያቂነት እራሳቸውን ነፃ ማድረግ፣
የሌላው ማኀበረሰብ ኢትዮጵያዊያን ድርጊቱን በጋራ በማውገዝ አሁን እየተፈፀመ ያለው ዘግናኝና አሰቃቂ ወንጀል ወደ ሌሎችም መዛመቱ ስለማይቀር “ማፈናቀሉ እስከመቼ?” በሚል ሁሉም በጋራ በመንቀሳቀስ በራሱ ተስፋ የቆረጠውን ዘረኝነት አገዛዝ እርቃኑን በማስቀረት ኢትዮጵያዊ አንድነታችንን በማፅናት የዜጎች ሰብዓዊ መብት በሙሉ መከበሩን ለማረጋገጥ የዜጎች ከሀገራቸው መፈናቀል፣ መሰደድ፣ በግፍ መታሰርና መገደል ማብቃት አለበት እላለሁ፡፡ አለበለዚያ ነገ ሁላችንም ከሀገራችን መፈናቀላችን አይቀሬ ስለሆነ ዛሬውኑ ቆም ብለን በማሰብ ማድረግ ያለብንን መወሰን ያለብን ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም ማንም ኢትዮጵያዊነታችንን ሲፈልግ ወስዶ እንካችሁ፤ ሳይፈልግ ዜግነታችሁን እኔ የምሰጣችሁ ስፍር ብቻ ነው ሲሉ መፍቀድ ባርነትን ከመምረጥ ውጭ ምን ትርጉም ልንሰጠው እንችላለን? እኔ በበኩሌ ባርነትን በፍፁም አልመርጥም፣ አልደግፍምም፡፡
! …. የኢህኣዴግ ኣጀንዳና የኣማራ ተወላጆች መፈናቀል …..!
አብርሃ ደስታ
(ከመቀሌ)
በዚ መሰረትም ‘የሌላ’ ክልል ተወላጆች በ’ሌላ ክልል’ መሬት የማግኘት መብታቸው ሲነፈጉ ይታያል። የኣማራ ተወላጆች ብዙ ግዜ ኑሮኣቸው ከመሰረቱበት ቀያቸው በኃልና በግፍ ሲፈናቀሉ እያየን ነው። በቡድን መብት መሰረት የኢትዮዽያ ሕጋዊ ዜጎች በገዛ ሀገራቸው መኖርያ መሬት ሲከለከሉ ማየት እጅግ ያሳዝናል። በሌላ በኩል በስልጣን ያለ ድርጅት (የራሱን ዜጎች እያፈናቀለ) መሬ ታችን ተቀባይነት በሌለው መንገድ ለዉጭ ዜጎች ሲቸረችር ይታያል። ዜጎቻችን በገዛ መሬታቸው ባዕድ ሁነዋል ።
የሚገርመው ደግሞ ‘መሬት ኣይሸጥም ኣይለወጥም’ ከሚል ግራ የተጋባ ፍልስፍና መሬታችን ለውጭ ዜጎች የሚሰጠው በነፃ ሊባል በሚችል ሁኔታ መሆኑ ነው። (በነፃ የሚሰጥበት ምክንያት መሬት ተሸጠ እንዳይባል ነው)። የኣማራ ተወላጆች ከቀያቸው መፈናቀል የገዢው ፓርቲ የተሳሳተ ፖሊሲና ለህዝብ ያለው ንቀት የሚያሳይ ነው። ዜጎችን በማባረር (‘ሕጋዊ ያልሆኑ ኗሪዎች’ በሚል ስም) መሬት ለውጭ ዜጎች ሲሰጥ እነዚህ የሌላ ሀገር ዜጎች እንዴት ‘ሕጋዊ’ ሆኑ???
ሰዎች ከቀያቸው በሃይል (በግፍ በዘርሓረጋቸው እየተለዩ) ሲፈናቀሉ (ሲባረሩ) የከፋ የሰብኣዊ መብት ጥሰት ነው። ዜጎቻችን (ወገኖቻችን) ሲፈናቀሉ የሚደርሳቸው ኢኮኖሚያዊ፣ ማሕበራዊና ስነልቦናዊ ቀውስ (Helplessness) መገመት ኣይከብድም። ሁሉም ኢትዮዽያ ሊተባበራቸው ይገባል፤ መንግስት ይህን ተግባሩ እንዲያቆም ተፅዕኖ ማድረግ ኣለብን።
እኛም እየተፈናቀሉ ካሉ ሰዎች ጎን መሰለፍ ያለብን ይመስለኛል። ምክንያቱም (1) ወገኖቻችን ናቸው። እኛ ኢትዮዽያውያን ያልደረስንላቸው ማን መጥቶ ይረዳቸዋል? (2) ዛሬ በኣማራ ተወላጆች እየተፈፀመ ያለው ግፍ (ኣሁንኑ ካልቆመ) ነገ በእያንዳንዳችን እንደሚፈፀም ማወቅ ይኖርብናል። (3) የማፈናቀል ተግባሩ የብሄር ፖለቲካ ችግር ኣባብሶ የጥላቻ ፖለቲካ ስር ሰዶ የኢትዮዽያ ሀገራችን ኣንድነት የሚፈታተን ይሆናል።
የስርዓቱ ደጋፊዎች ይህንን ችግር ተረድታቹ በገዢው ፓርቲ Pressure ፍጠሩ ፤ ኣለበለዝያ ግን ችግሩ ሁሉም ዜጋ ይነካል። በተለይ የትግራይ ተወላጆች በግልፅ ተቃውሞኣችንን ማሰማት ኣለብን። ህወሓት /ኢህኣዴግ ከተግባሩ እንዲቆጠብ ማድረግ ወይ ተግባሩ እንዲያቆም በመቃወም ከነዚህ ተፈናቃዮች ጎን መሰለፍ ኣለብን። ምክንያቱም እነዚህ ተፈናቃዮች ብዙ ችግር እንደሚደርስባቸው የታወቀ ነው። ቂም መያዛቸው (በገዢው ፓርቲ ቅር መሰኘታቸው) ኣይቀርም። ገዢው ፓርቲ (ኢህኣዴግ) የህወሓት ስራ መሆኑ ይታወቃል። ህወሓት ስልጣን መያዝ የቻለው በትግራይ ህዝብ ትግል ነው (ህወሓት ህዝቦች ማፈናቀል ወይ መጨቆን እንዲችል ለማብቃት ባይሆንም)።
ስለዚ የኣማራ ተፈናቃዮች በህወሓት ተግባር ምክንያት በትግራይ ህዝብ ቅር ሊሰኙ ይችላሉ። እንዲህ ከሆነ ደግሞ ዛሬ በኣማራ ህዝብ እየተፈፀመ ያለው ግፍ ነገ በትግራይ ህዝብ መደረጉ ኣይቀርም። ግለሰዎች በስልጣን ለማቆየት ሲባል በሰለማዊና ንፁህ ዜጎች ግፍ እየተፈፀመ ዝም ብሎ መመልከት ተገቢ ኣይደለም።
ስለዚ ተቃውማችን ማሰማት ኣለብን። ደሞ የትግራይ ተወላጆች በኣማራ ክልል የሉም? የደቡብ ክልል ወይ ኦሮምያ ወይ ሌላ ክልል ተወላጆች በኣማራ ክልል የሚኖሩ የሉም ? የማፈናቀሉ ተግባር ካልቆመ መጨረሻው ምን ሊሆን ነው? ስለ ሌሎች ስናስብ ስለራሳችን እያሰብን ነው፤ ሌሎችን ስንተባበር ራሳችን እየተባበርን ነው። ተግባራችን ስንቃችን ነው።
ለዜጎች ቅድምያ እንስጥ!
It is so!!!
ከቤንሻንጉል አማርኛ ተናጋሪ ዜጎችን በግፍ የማፈናቀሉ ሂደት ተጠናክሮ ቀጥሏል
ጉዳዩን እያስፈጸሙ ናቸው የተባሉትን የወረዳውን አስተዳዳሪ አቶ ታደሰ ሻምበልን በስልክ አግኝተናቸው ነበር፡፡ እራሳችንን አስተዋውቀን ጥያቄያችንን ልንጀምር ስንል አቶ ታደሰ ስልካቸውን ጆሮአችን ላይ በመዝጋታቸው ዜናው ሚዛናዊ ለማድረግ አልቻልንም፡፡
ምንጭ ፍኖተ ነፃነት

