በርካቶችን ለሞት የዳረገው የኦሮሚያ – ሶማሌ ግጭት እስከ ትናንት አለመቆሙን መንግስት አስታውቋል
አለማየሁ አንበሴ
አቶ አብዲ መሐመድ፥ እቶ ካሳ ተክለብርሃን እና አቶ ለማ መገርሳ
በኦሮሚያ እና በሱማሌ ክልሎች መካከል የተፈጠረው ግጭት እንደቀድሞ የወሰን ጉዳይ እንዳልሆነ የተጠቆመ ሲሆን፣ ትክክለኛ መንስኤው እየተጣራ መሆኑን ያስታወቁት የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ፤ ግጭቱ እስከ ትናንት አርብ ድረስ በተለያዩ ቀበሌዎች መቀጠሉንና በርካቶች ተገድለው፣ ከ20 ሺህ በላይ ዜጎች መፈናቀላቸውን አስታውቀዋል፡፡
ለበርካታ ቀናት በቀጠለ ግጭት፤ የሠው ሕይወት ጠፍቷል፣ ንብረት ወድሟል፣ ዜጎች ተፈናቅለዋል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ግጭቱ በቅርቡ እንዲገታ ይደረጋል፤ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎችም በመሃል ገብተው የማረጋጋት ስራ ይሠራሉ ብለዋል፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለ ማርያም ደሣለኝ፤ ከሁለቱ ክልል አመራሮች ጋር በግጭቱ ላይ በስልክ ውይይት ማድረጋቸውንና ግጭቱ እንዲቆም ማሣሠቢያ መስጠታቸውንም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡
በአካባቢው ለግጭቱ መባባስና ለሠው ህይወት መጥፋት ምክንያት የሆኑ ለህግ እንዲቀርቡ ይደረጋል ያሉት ሚኒስትሩ፤ የመሳሪያ ትጥቅ የማስፈታት ስራም ይሰራል ብለዋል፡፡
የመከላከያ ሰራዊትና የፌደራል ፖሊስ በግጭቱ መሃል ገብቶ ለማረጋጋት ለምን ዘገየ ተብለው የተጠየቁት ሚኒስትሩ፤ ክልሎቹ ችግሮቹን በራሳቸው ይፈቱታል የሚል እምነት በመጣሉ ነው ብለዋል፡፡
በግጭቱ የሶማሊያ ሪፐብሊክ ኃይሎችና የሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል መሳተፋቸው ተጣርቶ ህጋዊ እርምጃ ይወስዳል ብለዋል – ሚኒስትሩ፡፡ ግጭቱ በታጠቁ አካላት የታገዘ መሆኑን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፤ እነዚህ የታጠቁ አካላት እነማን ናቸው የሚለው ግን እስካሁን ምላሽ አለማግኘቱንና በማጣራት ሂደቱ እንደሚታወቅ ተናግረዋል፡፡ ግጭቱ የህዝብ ለህዝብ አለመሆኑን ግን አስረግጠው በመግለፅ፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ የሁለቱ ክልሎች የመንግስት ኮሚኒኬሽን ኃላፊዎች ጉዳዩን አስመልክቶ በየሚዲያው የሚያስተላልፏቸው መግለጫዎች፣ ግጭቱን ሊያባብሱ የሚችሉ በመሆኑ ከእንግዲህ በኋላ ግጭት አባባሽ መግለጫዎችን ከመስጠት እንዲቆጠቡ ዶ/ር ነገሪ አሳስበዋል፡፡
የኮሚኒኬሽን ኃላፊዎቹ ከዚህ ድርጊታቸው የማይቆጠቡ ከሆነ፣ ህጋዊ እርምጃ እንደሚወሰድም ሚኒስትሩ ጠቁመው፤ በሁለቱም የሚገለፁ አሃዛዊ መረጃዎችንም ገና ያልተጣሩ መሆናቸውንና መንግስት ሁኔታውን አጣርቶ እንደሚገልፅ አስታውቀዋል፡፡
የሶማሌ ክልል ግጭቱን አስመልክቶ ለቪኦኤ በሰጠው መግለጫ፤ በአወዳይ ከተማ 50 ሠዎች መገደላቸውን ሲገልፅ፣ የኦሮሚያ ክልል በበኩሉ፤ በአወዳይ ከተማ 18 ሰዎች መገደላቸውን፣ ከነዚህ ውስጥ 12ቱ የሶማሌ ተወላጆች፣ ቀሪዎቹ የኦሮሞ ጃርሶ ጎሣ አባላት መሆናቸውን አስታውቋል፡፡
የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ቃል አቀባይ አቶ አዲሱ አረጋ ትናንት ምሽት ባሰራጩት መረጃ፤በሰሞኑ ግጭት ከተፈናቀሉት ከ22ሺ በላይ ዜጎች በተጨማሪ አጠቃላይ የድንበር ግጭቱ ከተከሰተበት ከ2009 ጀምሮ 416ሺ807 ዜጎች መፈናቀላቸውን አስታውቀዋል፡፡
በአወዳይ የደረሠውን ግጭት ተከትሎ፣ ከሶማሌ ክልል ከ21 ሺህ በላይ ዜጎች ተፈናቅለው በጭናቅሠን፣ ባቢሌና ሐረር ከተሞች ተጠልለው እንደሚገኙ የኦሮሚያ ክልል ቃል አቀባይ አቶ አዲሱ አረጋንና ምንጮቹን ጠቅሶ ቪኦኤ ዘግቧል፡፡
የሱማሌ ክልል የመንግስት ኮሚኒኬሽን ሃላፊ አቶ ኢንድሪስ አህመድ በበኩላቸው፤ “ሰዎች ከአካባቢው የተፈናቀሉት በግዴታ ሳይሆን በፍቃዳቸው ነው፤ ጥቃት አልተፈፀመባቸውም” ብለዋል፡፡ ምንጮች በበኩላቸው፤ የግዳጅ ማፈናቀል መፈፀሙንና በዜጎች ላይ ድብደባና እንግልት እንደደረሰባቸው ለመገናኛ ብዙኃን ተናግረዋል፡፡
የሱማሌ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ሃላፊ አቶ ኢንድሪስ አህመድ፤ በአወዳይ ከተማ የደረሰውን ግድያ ተከትሎ ባስተላለፉት መግለጫ፣ የኦሮሚያ ክልል መንግስትን “የአሸባሪነት አላማ አራማጅ” በሚል የፈረጀ ሲሆን የኦሮሚያ ክልል ቃል አቀባይ በበኩላቸው፤ ፍረጃውን አጣጥለው፣ ከአንድ ክልልን ከሚያስተዳድር አካል የማይጠበቅ ነው ብለዋል፡፡
የሶማሌ ክልል መንግስት ኮሚኒኬሽን ሃላፊ ለቪኦኤ በሰጡት መረጃ፤ በአስራ አንድ የሶማሌ ወረዳዎች፣ ማንነታቸው ባልታወቀ አካላት በተሠነዘሩ ጥቃቶች፣ ከሁለት መቶ አስራ ሶስት ሰዎች በላይ ህይወት ማለፉን አስታውቀዋል፡፡ ይሄን ተከትሎም የሶማሌ ክልላዊ መንግስት፣ ለ5 ቀናት የሚቆይ ብሄራዊ የሃዘን ቀናት በክልሉ ማወጁንም ለማወቅ ተችሏል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ ፣የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን የግጭቱን መነሻና የደረሰውን ጉዳት የሚያጣራ ቡድን ከትላንት በስቲያ ሐሙስ ወደ አካባቢው መላኩንና ማጣራት መጀመሩን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደምሰው በንቲ ለአዲስ አድማስ አስታውቀዋል፡፡
ሰሞኑን የሁለቱ ክልሎች የመንግስት ኮሙኒኬሽን ኃላፊዎች በማህበራዊ ድረ-ገፆቻቸው የሚያሰፍሯቸው የእርስ በርስ ውንጀላዎች አስደንጋጭና ግጭቱን የሚያባብሱ መሆናቸውን አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ፡፡ ክልላዊ መንግስታቸውን ወክለው መልዕክት የሚለዋወጡ እንደማይመስሉና ኃላፊነት የጎደሏቸው እንደሆነም ተገልጿል፡፡
ምንጭ፡ አዲስ አድማስ
The world loves Ethiopian pop star Teddy Afro. His own government doesn’t.
By Paul Schemm
Tewodros Kassahun (Teddy Afro) Photo Credit: Ethionewsflash.
ADDIS ABABA, Ethiopia — Monday marked the first day of the new Ethiopian year, but it hasn’t been much of a holiday for Teddy Afro, the country’s biggest pop star.
First, the government informed him that his New Year’s concert was canceled. Then, on Sept. 3, police broke up the launch party for his successful new album, “Ethiopia,” in the middle of the sound check at the Hilton Hotel, claiming Teddy hadn’t received permission to hold the event.
“Asking for a permission to organize an album launch is like asking a permit for a wedding or birthday party,” Teddy wrote on his Facebook page. “This is unprecedented and has never been done before because it is unconstitutional.”
But government disapproval certainly isn’t anything new for Teddy: This year was his third straight aborted New Year’s concert. And even as “Ethiopia,” which briefly hit No. 1 on Billboard’s world music chart, could be purchased or heard on virtually every street corner in the capital, Addis Ababa, after its May release, Teddy’s songs were nowhere to be found on state radio and TV. An interview with a public TV network was even canceled at the last minute, prompting the resignation of the journalist involved.
At first glance, there seems to be nothing controversial about Teddy Afro, born Tewodros Kassahun, and his traditionally influenced pop songs about love, unity and the glory of Ethiopia. His tunes have earned him a rapturous audience both at home and among the vast Ethiopian diaspora.
If anything, Teddy is quite the patriot. He’s just the wrong kind of patriot.
Teddy’s music has increasingly focused on extended history lessons glorifying Haile Selassie, the last emperor of Ethiopia, who was overthrown by a communist coup in 1974, as well as the great kings of the 19th century. The title track of his 2012 album, “Tikur Sew,” for example, celebrated Emperor Menelik II and his defeat of Italian troops invading Ethiopia in 1896 — complete with a music video that was practically a war movie.
But those rulers came from the Amhara people, the ethnic group that has historically dominated the country and, according to other Ethiopian peoples, brutally repressed its rivals. “Wherever he faced fierce resistance, Menelik responded with the most barbaric and horrific forms of violence,” read a 2013 statement by activists from the Oromo people, who led a boycott campaign of the Heineken-owned brewery Bedele after it sponsored Teddy’s concerts.
Teddy’s celebration of historic Amhara rulers is dramatically different from the nationalism of the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front, which is dominated by a political party from the Tigrayan people. The government promotes Ethiopia’s ethnic diversity and uses “unity through diversity” as its slogan. Teddy’s songs — and his criticism of rising ethnic division in Ethiopia — seem like challenges to its vision of the country.
The government is also particularly sensitive at the moment. The ruling party has carefully crafted a narrative of progress and development for the country, created partly in response to the bitterness that followed Ethiopia’s 2005 elections. It was the country’s first free and fair vote, and the results were heavily disputed. Hundreds died in the ensuing unrest, and — whether intentionally or not — a then-newly released song from Teddy became part of the soundtrack of the protests.
Now the government’s narrative is starting to fray. The country’s largest ethnic group, the Oromos, recently spent a year and a half protesting its alleged marginalization, saying that government development plans seemed to leave Oromo areas behind. Hundreds of people died at the hands of security forces during protests, and the situation calmed down only after a 10-month state of emergency was called in October 2016. The Amhara region also saw protests against the government in the same period, during which some people attacked Tigrayans as “usurpers.”
Teddy “is instigating a quarrel during a very sensitive time for them,” said Seyyoum Teshome, an independent political analyst who has had run-ins of his own with the government.
Ethiopia’s government has been repeatedly criticized — albeit in fairly muted terms — by the United States and other countries for suppressing dissent. The Parliament is entirely under the control of the ruling party, and some of the most prominent opposition leaders, especially Oromos, are in prison. And while Teddy has insisted that he has nothing to do with politics, it appears that the government isn’t willing to take any chances on his music.
Source:-The Washington Post