ፍርድ ቤቱ ባለፈው ውድቅ ያደረገውን ጉዳይ ዛሬ ያለምንም ይግባኝ ማፅደቁ ተሰማ
ዛሬ ግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም. የነበረው የፍርድ ቤት ውሎ አዲስ ክስተትን ይዞ ብቅ ማለቱ ተሰምቷል፡፡ ባለፈው ሚያዚያ 2006 ዓ.ም.ተጠርጥረው ከታሰሩ 3 ጋዜጠኞች እና 6 ብሎገሮች መካከል ዛሬ እሁድ ግንቦት 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀጠሮ የነበራቸው በፍቃዱ ኃይሉ፣ አቤል ዋበላ እና ማህሌት ፋንታሁን ቀደም ሲል የማዕከላዊ ፖሊስ ጉዳዩን ወደ ፀረ-ሽብርተኝነት የክስ ጉዳይ ለመውሰድ የጠየቀው በፍርድ ቤቱ ውድቅ ተደርጎ የነበረ ቢሆንም፤ ዛሬ በሌላ ተቀያሪ ወንድ ዳኛ እዛው ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ባለፈው በነበረው ቀጠሮ ውድቅ የተደረገው በፀረ-ሽብርተኝነት ክስ ፖሊስ የጠየቀው ተጨማሪ 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡ በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ በዛሬው ውሎ የነበፍቃዱ ፣ አቤል እና ማህሌት ሂደት ለሰኔ 22 ቀን 2006 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በጉዳዩ ላይ ጥያቄ ያቀረብንላቸው ተከላካይ ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንን፤ ከህግ አኳያ ፖሊስ ጉዳዩን ወደ ፀረ-ሽብርተኝነት ጠይቆ ውድቅ ተደርጎበታል፣ ስለዚህ በነበረው ውሳኔ ፖሊስ ቅር ከተሰኘ ይግባኝ ማለት እንጂ በተመሳሳይ ችሎት እና ጉዳይ ላይ በፍርድ ቤቱ ውድቅ የተደረገ ጉዳይ እንደገና ቀርቦ የፖሊስ ጥያቄ ተቀባይነት ማግኘቱ እና ተጨማሪ የ28 ቀናት የምርመራ ጊዜ በሚል መፈቀዱ ከህግ አግባብ ውጭ ነው፤ ይሄንንም ለፍርድ ቤቱ ብናቀርብም ተቀባይነት አላገኘም፤ ስለዚህ የህግ አካሄድ (procedure) ስህተት ታይቶበታል ሲሉ የነበረውን ሂደት ተናግረዋል፡፡ ይህን የክስ ሂደት ፖሊስ ጉዳዩን ወደ ፀረ-ሽብርተኝነት ለመውሰድ ውድቅ ያደረገችው ዳኛ ሴት እንደነበረች አይዘነጋም፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ የነገረ-ኢትዮጵያ ጋዜጠኛ በላይ ማናየ ፖሊስ ፍርድ ቤት ያቀረባቸውን እስረኞች ሲያወጣ፤ ለተወሰነ ጊዜ በጠበቂ የፀጥታ ኃይሎች ለጊዜው ታግቶ እንዲቆይ ከተደረገ በኋላ፤ ለነገ ማዕከላዊ እንዲቀርብ ትዕዛዝ በመስጠት ተለቋል፡፡ ለተወሰነ ጊዜ የተደረገው የጋዜጠኛው እገታ ምክንያት እስካሁን አልታወቀም፡፡
ጋዜጠኞች እና ብሎገሮች ቶርቸር እንደተፈፀመባቸው ተገለፀ
ዛሬ ሚያዚያ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ፍርድ ቤት የቀረቡት በፍቃዱ ኃይሉ፣ አቤል ዋበላ እና ማህሌት ፋንታሁን ከሰዓት በዋለው የአራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡ በፍቃዱ ኃይሉ የውስጥ እግሮ ተደብድቦ ቶርቸር መደረጉን እና አቤል ዋበላም ከፍተኛ ተደጋጋሚ ድብደባ እንደተፈፀመበት ለፍርድ ቤቱ ተከተፈቀደላቸው ቤተሰቦች እና ከተከላካይ ጠበቃቸው አቶ አምሃ መረዳት ተችሏል፡፡ በስፍራው ልክ እንደ ትናንቱ በርካታ ጋዜጠኖች፣ ቤተሰቦች፣ ወዳጆች እና ዓለም አቀፍ ዲፕሎማቶች ተገኝተው ነበር፡፡ ነገር ግን ከጥቂት ቤተሰብ በስተቀር ጋዜጠናም ሆነ ዲፕሎማት እንዲሁም ጓደኞቻቸው ችሎቱን እንዲታዘቡ አልተፈቀደም ነበር፡፡ናግረዋል፡፡ ማህሌት ፋንታሁን በችሎት ላይ ከማልቀስ በቀር ቃላት መናገር እንዳልቻለች በችሎቱ
ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ የተፈፀመውን ቶርቸር ለማስተባበል መሞከሩን እና እነ በፍቃዱ ኃይሉና አቤል ዋበላን ውሸታቸውን ነው፣ እነኚህ የድርጊቱ ዋና አቀናባሪ ናቸው ሲል መናገሩን ከችሎት ታዳሚ ቤተሰብ መረዳት ተችሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ፖሊስ የያዘበትን ምክንያት ሲያስረዳ ከአሸባሪ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ከምርጫው በፊት አመፅና ሽብር ለመፈፀም 5 ጊዜ ውጭ ሀገር ስልጠና ወስደዋል፣የመገናኛ ብዙኃን መሳሪያ ኮምፒዩተር ገዝተዋል ማለቱን ጠበቃቸው አቶ አምሃ ለመገናኛ ብዙኃን ገልፀዋል፡፡ ይሁን እንጂ ፖሊስ አሸባሪ ያላቸውን እና ስልጠና የሰጡትን ድርጅቶች ስም እንዲጠቅስ ሲጠየቅ አልጠቅስም፣ አሁን ከጠቀስኩኝ ተባባሪዎቻቸው ያመልጡኛል ሲል ለፍርድ ቤቱ መናገሩን መረዳት ተችሏል፡፡
ከዛሬ ጀምሮም የቅርብ ጥቂት ቤተሰብ ብቻ ማዕከላዊ ሄዶ እንዲጎበኛቸው የተፈቀደ መሆኑን በመግለፅ ለእሁድ ግንቦት 10 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት ተለዋጭ ቀነ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ የትናንትናው የነ ተስፋዓለም ወልደየስ፣አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሳዬ፣ ዘለዓለም ክብረት፣ ናትናኤል ፈለቀ እና አጥናፍ ብርሃን ችሎት ለቅዳሜ ግንቦት 9 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት መቀጠሩ ይታወሳል፡፡
Nine Ethiopian Journalists and bloggers were arrested
The journalists and bloggers were arrested by Ethiopian government on April 25-26, 2014. The journalists Asmamaw Hailegiorgis, Tesfalem Woldeyes and Edom Kssaye from Addis Guday and Addis Standard magazine respectively arrested. As the same time, 7 Ethiopian zone 9 bloggers and activists were also arrested.
The bloggers and activists Befekadu Hailu, Atnaf Birhan, Mahlet Fantahun, Natnael Feleke, Abel Wabela and Zelalem Kibret arrested at Maikelawi criminal investigation bureau of Addis Ababa police but still no charge at court related with them.
በሐረር የተከሰተው ተደጋጋሚ የእሳት አደጋ ጥያቄ ማስነሳቱን ቀጥሏል
በታሪካዊቷ ሐረር ከተማ ባለፈው ካቲት 30 ቀን 2006 ዓ.ም. በሸዋበር የንግድ ሱቆች ላይ በተደጋጋሚ የደርሰው የእሳት አደጋ የከተማው ነዋሪና የአካባቢው የንግድ ማኀበረሰብ ላይ ከፍተኛ ጥርጣሬ በመፍጠሩ ጥያቄ ማስነሳቱ ዛሬም ቀጥሏል፡፡ ሁለት ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ሶስት ጊዜ ሱቆቻቸው የተቃጠለባቸው እና አሁንም ለከፍተኛ ኪሳራ የተዳረጉም እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የከተማው የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በተደጋጋሚ ስለሚነሳው የእሳት አደጋ ምክንያት አደጋው የደረሰባቸው መንግስት ተገቢውን ጥበቃ አላደረገም በሚል ሰልፍ ከመውጣታቸው ጋር ተያይዞ መንግስት አደጋው ለደረሰባቸው ነጋዴዎች ምን እንዳሰበ በጋዜጠኛ ተጠይቀው፤ ሰልፍ የወጡት የጎዳና ተዳዳሪዎች ናቸው፣እርምጃ እንወስድባቸዋለን ማለታቸው ይበልጥ ቁጣመቀስቀሱን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡ ምንም እንኳ እስካሁን የእሳት አደጋው መንስኤ ተጣርቶ ይፋ ባይሆንም እንደምንጮች ገለፃ ከሆነ ከተፈጠረው እሳት አደጋ ጀርባ የመንግስት እጅ ሳይኖርበት አይቀርም በሚል የህዝብ ግንኙነቷን መልስ ዋቢ በማድረግ ነዋሪዎቹ ጥርጣሬ እንዳላቸው ጠቁመዋል፡፡
በከተማው የንግድ ሱቆች ላይ በተደጋጋሚ እየተከሰተ ስላለው የእሳት አደጋ ጋር በተያያዘ የጠየቅናቸው አቶ አብዱላሂ እንዳሉት ከሆነ፤ አደጋውን የክልሉ ባለስልጣናት ሆን ብለው እንዳደረጉትና መሬቱን ለራሳቸው ሰዎች ለመስጠት አስበው ሊሆን እንደሚችል ጥርጣሬ እንዳላቸው ጠቁመዋል፡፡ ለዚህም በምክንያትነት ያነሱት ከአንድ ሺህ ዓመታት በላይ ያስቀጠረችና እና በዓለም ቅርስነት በዩኔስኮ የተመዘገበች ታሪካዊ ከተማ ያውም በንግድ ሱቆች ላይ ተደጋጋሚ የእሳት አደጋ መከሰቱ ከመንግስት ሌላ እጅ ይኖራል ተብሎ አይታሰብም፣ ይህም በከተማው ወደፊት ኢንቨስት ለማድረግ የሚፈልጉ ዜጎችንም ሆነ የውጭ ባለሃብቶች የሚያበራታታ አይደለም ብለዋል፡፡
በአደጋው እስካሁን በቁጥር ተለይቶ ባይታወቅም እጅግብዙ ንብረቶች መውደማቸውም ተጠቁሟል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የክልሉ ርዕሰ መስተዳደር አቶ ሙራድ አብዱላሂ በአደጋው ንብረቶቻቸው ለወደመባቸው ነጋዴዎች መንግስት በጀት መመደቡን ማስታወቃቸው የተነገረ ሲሆን፤ አንዳንድ ነጋዴዎች ግን ስለተግባራዊነት ጥርጣሬ እንዳላቸው አልሸሸጉም፡፡
በሆሳዕና ከተማ የመብራት ኃይል ገመድ ተበጥሶ የሰው ህይወት አጠፋ
በደቡብ ክልል ሆሳዕና ከተማ የኤልክትሪክ ገመድ ተበጥሶ የ13 ዓመት ልጅ ህይወት ማጥፋቱ ተገለፀ፡፡ አደጋው የደረሰው በጎፈር ሜዳ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ቦቢቾ በተባለ ቀበሌ ሰኞ መጋቢት 8 ቀን 2006 ዓ.ም. ጠዋት ለረጅም ጊዜ ምሰሶው ሊወድቅ የደረሰ የኤሌክትሪክ ገመድ ተበጥሶ አንድ የ13 ዓመት ልጅ ከመኖሪያ ቤቱ ወደ ትምህርት ቤት እየሄደ ሳለ በደረሰ አደጋ ወዲያው ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል፡፡ 
አዲስሚዲያ ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች እንደገለፁት ከሆነ ምሰሶው በመንገድ ጥገና ቁፋሮ ምክንያት በመላላቱ የኤሌክትሪክ ገመዱ ረግቦ እንደነበርና ይህንንም በመፍራት በተደጋጋሚ ለከተማው መስተዳደርና በከተማው ለሚገኝ የመብራት ኃይል ዲስትሪክት ቅሬታ ቢያቀርቡም ሰሚ ባለማግኘታቸው አደጋው መድረሱን አስታውሰዋል፡፡ ከሟቹ ልጅ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ መብራት ኃይል ኮርፖሬሽን ላደረሰው የቸልተኝነት አደጋ ምን ምላሽ እንዳለው ለማጣራት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወደ ሆኑት አቶ ምስክር ነጋሽ ደውለን ለማጣራት ብንሞክርም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ሊሆኑ አልቻሉም፡፡